ከዕዉነት ሽሽት…አስከ የት ? – ማላጂ

የዕዉነት ብርኃን በክፉዎች የክህደት መጋረጃ ለጊዜዉ ቢከለልም መንጋት እና ዕዉነት ሆኖ መገለጥ አይቀሬ መሆኑን ከአለፉት ግማሽ ክ/ዘመናት የነበረብንን የህልዉና ችግር እና ስንክሳር ማስታወስ አሁን ስለሚደረገዉ የመጨረሻ ምዕራፍ የህልዉና እና ነፃነት ትግል እና ተጋድሎ ለሚኖረዉ ስምረት እና ዉጤት ፋይዳ ብዙ ነዉ ፡፡

ነገር ግን ከዕዉነት ሽሽት መዳረሻዉ ባይታወቅም ለዘመናት ከመሪር ሀቅ ጋር ያለመገፋጥ እና አድር ባይነት የመከራ ገፍት እና ቀንበር ተሸካሚ ህዝብ በደል እና ዕሮሮ ጊዜ ማራዘም ይሆናል፡፡

ይሁንና ከዕዉነተኛ ቀዳሚ ሁነኛ የታሪክ መስክ መነሳት ይገባል፡፡ የአገር እና ህዝብ ህልዉና ጥያቄ ዉስጥ ሲገባ እና የኢትዮጵያዉያን የህልዉና እና ነፃነት ስጋት እና ትግል ጥሪ ከአንድ ክ/ዘመን በላይ አስቆጥሯል፡፡

ሆኖም የኢትዮጵያ እና ህዝቧ በታሪካዊ ጠላቶች በተለይም በግናባር ቀደምትነት በጠላትነት የሚፈርጀዉ የዓማራ ህዝብ በትግራይ ህዝባዊ ነፃነት ትግል አራማጆች በመመሪያቸዉ ላይ በ1968 .. በማያሻማ ሁኔታ ዘርተዋል ይህንም እንክርዳድ በአሁኑ እያጨድን እንገኛለን፡፡

ለዚህም በት.... የአገር ክህደት እና ኢትዮጵያዉያን ወገኖች ዉርደት ስምምነት (መመሪያ/ማኒፌስቶ) አስቀድሞ የነበር ነዉ ፡፡ የኢትዮጵያ እና ዜጎች ህልዉና እና ነጻነት በይፋ አደጋ ላይ የወደቀበት እና የተዶለተበት የት...ግ የጥፋት እና ሞት መመሪያ ምክነያት የኢትዮጵያዉያን በተለይም በይፋ ሞት ያወጁበት ዓማራ ህዝብ የነጻነት እና ህልዉና ትግል ዘመን ያን ጊዜ ተጀምሯል፡፡

ይህንም የጠላት የጥፋት እና ሞት እወጃ ስምምነት (መኒፌስቶ) መነሻ መዝገብ ለመጥቀስ ያህል ፡

መቅድም ፡ የትግራይ ህዝብ ማለት በትግራይ መሬት ዉስጥ የሚኖሩት እና በተለያየ ምክነያት ከትግራይ መሬት ዉጭ ለሚኖሩ ህዝቦች በመላ ያጠቃልላል ይላል ፡፡ ይህም የትግሉ መነሻ እና መድረሻ ትግራይን እና ትግሬዎችን ማቀፍ ነበር ይህም ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያንን የማይመለከት መሆኑን መረዳት ለፈለገ እና ለቻለ የህልዉና እና ነጻነት በደል እና ትግል አብረዉ መወለዳቸዉን ነዉ ፣

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያ "ኢህአዴግ አስካለ " የመከራ ቀንበር ይኖራል !

የመሬት ወይም የግዛት አስተዳደር በሚመለከት የትግራይ መሬት በደቡብ አሏኃ፤በሰሜን መረብ ወንዝ….ይል እና በምስራቅም ሆነ በምዕራብ ምልክት አልባ እና ወሰን ክፍት አድርጓል፣ ለምን ? ያለ ነበር ፤አለ ለዚህ ነዉ የህልዉና ነፃነት ትግል ያኔ የጥፋት ገለባዉ ሲከመር የትግል ዕሳት ተቀጣጥሏል፡፡

ይቀጥል እና እንዲሁ የትግራይ መሬት ወልቃይት እና ጠለምትን ያጠቃልላል ይልኃል፡፡ በሌሎች የትግራይ አቅጣጫ ለምን አልተገለፀም ……..ለምን ቢሉ ልቅ አድርግ ዝለቅ፣ ዘባርቅ …ነበር ምኞቱ ፡፡

ከዚህም በላይ የህልዉና አደጋ አረም እና እሾክ የተተከለዉ እንደ ት.... ትግል መመሪያ ከ1968 .. ቀድሞ የ፹ ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ እና ይህም ሲደመር (80+17+27) 124 ዓመት ሲሆን ይህም የህልዉና እና ነፃነት ይፋዊ ክህደት እና ጥፋት ዕድሜ እንደነበር መረዳት ይቻላል፡፡ ይህም የ፻ መቶ ፳ ዓመት የት.... ጥላቻ ፅንሰት እና ዉልደት እና መሰረት ዓማራ ማለቱ ዛሬ ሳይሆን ያን ጊዜ የተስማማበት መሆኑን በት...ግ የሴራ ስምምነት መመሪያ የትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ትግል ዓላማ ፀረዓማራ መሆኑን ከማሳየት በላይ ምን ይጠበቃል ፡፡

ይህም በዚህ የጥፋት እና ሞት ዕወጃ የት...ግ መመሪያ ክፍል II () የትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ትግል ፀረ ዓማራ ብሄራዊ ጭቆና እና ፀረ ኢምፔራሊዝም በማድረግ የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ማቋቋም ይሆናል ከሚል በላይ የብሄራዊ ህልዉና እና ነፃነት አደጋ ምልክት እና ማስረጃ ከየት እና ከማን እንዲመጣ እንጠብቃለን ፡፡

ለዚህ ነዉ ዕዉነት እና ሽሽት ቢያንስ የአንድ መቶ ኃያ ዓመት ጊዜ ሲኖረዉ ዕዉነቱን ከመቀበል እና በዕዉነተኛ ኢትዮጵያዊነት ስሜት እና ብሄራዊ አንድነት ከመስራት ይልቅ በሰሞነኛ እና በጠባቂነት አስተሳሰብ የህልዉና እና ነፃነት ተጋድሎዉን ጊዜ በማራዘም የአገሪቷን ሉዓላዊነት እና የህዝቧን ነፃነት ማሳጣት እና ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለ መጥቷል፤ ደርሷል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሙስና ሳያጠፋን እንዋጋዉ (ስንታየሁ ግርማ)

1983 .. ዓም ወዲህ እንኳ ከኢህዴግ ሽግግር ምስረታ ጊዜ ጀምሮ የትግራይን ዲሞክራቲክ ሪፐፕሊክ ለማቋቋም የኢትዮጵያን አንድነት እና ሉዓላዊነት የመናድ እና የማናጋት ጅምር በኢትዮጵያዊነት ጠንከር ያለ ማንነት ያለዉን እና በግንባር ቀደም ጠላትነት የፈረጁትን ዓማራ የማክሰም እና የማዳከም ስልት በማፈናቀል፣ በማግለል፣ በመደለል፣ በመግደል እና በማስገደል የተጀመረዉ የጥፋት እና ሞት ሀሁ… ዘር ፐፑ…ደርሷል ፡፡

እናም ኢትዮጵያዊዉ ነኝ የምንል ሁሉ የህልዉና እና ነጻነት ጉዳይ በተለይም የዓማራ ህዝብ በግፍ እና በገፍ ያልደረሰበት የኢትዮጵያ ክፍል ከሰማንያ ሶስት አስከ ዛሬ ሰልስት የለም፡፡

የህልዉና እና ነጻነት ትግል በኢትዮጵያዊነቱ እና በማንነቱ ምክነያት ለ ፩ መቶ ዓመታት እየደረሰበት ላላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ የሚያጠቃልል መሆን አለበት ፡፡

የህልዉና እና ነጻነት ትግል ያሳስበናል ይመለከተናል የሚል ሁሉ የህልዉና እና ነጻነት አደጋ ትኩሳት የሚሰማዉ በሰሜን ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከዓማራ ክልል ዉጭ ባሉ የኢትዮጵያ ግዛቶች ከትናንት አስከ ዛሬ በግል እና በጀምላ ለሚደረግ ፍጂት ፣ ሞት እና ስደት ሊተኮርበት ይገባል ፡፡

በስል እና ጥሬ በማድረግ ዘላቂ እና አስተማማኝ የህልዉና እና ነፃነት ብሎ ትግል ሳይሆን ከንቱ መግተልተል እንዳይሆን ሊታሰብበት ይገባል ፡፡

ስለ ህልዉና እና ነጻነት የሚደረገዉ ትግል እና ገድል በመላዉ ኢትዮጵያ የዉስጥ ፣የዉጭ እና ጎረቤት የሚስተዋሉ የዜጎች ነፃነት፣ ፍትኅ እና እንዲሁም ከሱዳን ጋር ያለዉ የድንበር ፤ወሰን ጉዳይ ከልዑላዊነት እና ህልዉና አኳያ አብሮ ሊታይ ይገባል

ከዕዉነት በሆነ ባልሆነ መደለል ከራስ ፣ከአገር ፣ ከጠላት እና ወዳጂ፣ ከወሳኝ ቦታ እና ሁኔታ……እንዳሉት ፤እንደተባለዉ ብሎ መሸሽ ….የትም እንደማያደርሰን አዉቀን ከዕዉነት ሽሽት እና ከመወሻሸት ማቆም አለብን፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያ - ብታደርግ የተወገዘች፣ባታደርግም ውጉዝ ነችና ቀበቶዋን ታጥብቅ!

ከነበረበት ቦታ የሚለቅ ቦታ እንጂ ከእዉነት እና ከራስ መራቅ ጭንቅ ማትረፍ እንጂ ዕርቅ አይሆንም ፡፡ ይልቅ አርሱ ለዓመታት ከዕዉነት ሲሸሽ የነበር ኡንም ከራሱ የሚሸሽ የትም አይደርስም ፡፡

የዓማራ ህዝባዊ ህብረት እና አንድነት ለብሄራዊ አንድነት እና ደህንነት አልፋ እና ኦሜጋ ነዉ ፡፡”

 

ማላጂ

አንድነት ኃይል ነዉ ”

1 Comment

  1. ጦርነት ከእኛ በላይ ላሳር ነው የሚሉን እነዚህ ወራሪ የትግራይ ሃይሎች አሁን በየስፍራው ሲሞቱና ሲፈረጥጡ ምን ይሉ ይሆን? የዘረፈውን እቃ ተሸክሞ ሊወጣ ሲል ተይዞ እኔን ያየህ ተቀጣ እያለ የተዘረፈው፤ የተገደለው፤ የተሳደደው፤ የተደፈረው ሁሉ ሲተፋበት ምን ይሰማው? ጉራ ለማንም አይመችም። ተንኮል ራስንም ይጠልፋል። በወያኔ ላይ የሆነው ይህ ነው። ግን አሁንም አልተማሩም። አይማሩም። በነጭ ትክሻ ላይ ቆመው ዛሬም መልሰው ሊገዙን ይሻሉ። ያ ግን እንተላለቃለን እንጂ አይሆንም። የሚገርመው በቅርቡ በመቀሌ ተገኙ የተባሉትን በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዜና የወያኔው የትግራይ ቲቪ ሲዘግብ እንዲህ ብሎታል። “የትግራይ መንግስት ፕሬዚደንት በኢትዮጵያ ካሉት የእንግሊዝ አምባሳደር ጋር ተወያዪ”። እኔ እኮ ሰው ለምንድነው የሚለማመጣቸው? መገንጠል ከፈለጉ ይጓዙ። ዜናው የሚነግረን ሃገር ሆነናል ነው። መንገድን ጨርቅ ያርግላችሁ። ሌባ፤ ዘራፊ፤ ነፍሰ ገዳይና ሃገር ሺያጭ ወያኔ እንኳን ለሃገር ለትግራይ ህዝብም እንዳልጠቀመ ታሪካቸው ይናገራል። አሁን ከየሥፍራው እየፈቱ ወደ መቀሌ የሚያጓጉዙት የፋብሪካ እቃዎች፤ የሆስፒታል አልጋዎች፤ የምግብ ፍጆታዎች፤ የመደበርና ሌሎችም የአገልግሎት መስጫ መኪናዎች ሁሉ የድርጅቱን ሌብነት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ።
    በቅርቡ እናቱ በወያኔ በነፋስ መውጫ በኩል የተገደለችበት ጋር ቁጭ ብለን ስናወራ እንዲህ አለኝ። እቃ መዝረፍና ነቅሎ መውሰድ የጀመሩት እንደገቡ ነው። ለምሳሌ በብር ሸለቆ፤ በጎንደር የመብራት ሃይል ማመንጫውን ጄኔሬተር አይናችን እያየ ነበር የጫኑት። ሌላም እልፍ ጉድ ያኔም ያደርጉ ነበር። ከጅምሩ መገንጠልን እንደ እቅድ ስለያዙት አዲስ አበባ በ 27 ዓመት በመንግስትነትም ሲኖሩ ለውጊያ እየተዘጋጅ ነው የነበረው በማለት የክፋታቸው ጥግ የቆየ መሆኑን አጫወተኝ። የእንግሊዚ የኢትዮጵያ አምባሳደር በአሜሪካ ታዞ ይሆናል የሄደው። ከወያኔ ጋር በምንም ሂሳብ እንግሊዝን የሚያናግራት ጉዳይ አይኖርም። ከድሮው የ IRA – Irish Republican Army ጋር እጅና ጓንት ሆኖ የሰራው ወያኔ ዛሬ በየሃገሮች መዲና ኡ ኡታ የሚያሰሙለት የቀድሞ አጋሮቻቸው እንደሆኑ እናውቃለን። ኖርዌ ሌላው ቱልቱላ ናት። ባልገባቸውና ባልተረድት ነገር ላይ የሚለፈልፉት እነዚህ የነጭ ስብስቦች ለጥቁር ህዝብ ጭራሽ አያስቡም። ለዚያ ነው France 24, CNN, AP, እና ሌሎችም ተባራሪና አባራሪ የወሬ አናፋሾች ያለምንም መረጃ በሬ ወለደ የሚሉን። ግን እነዚህና ሌሎችም የወሸት አራጋቢ የማሰራጫ መስመሮች የታላቁ ሴራ አንድ አካል ናቸው። የውሸት ፕሮፓጋንዳ ነፊዎች። የዋሽንግተን ጥሩንባ አዳማቂዎች። እንዴት ሰው በሌላ ሃገር መንግስት ላይ ሌላ መንግስት ይመሰርታል? የሽግግር መንግስት ማለት ምን ማለት ነው። ማንን ነው የሚያሻግረው? እንዲህ ባለ ሂሳብ ነው አለምን የሚያምሱት። ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ አይነት ፍልስፍና።
    ሌላው ሃገር ቀመስ የወሬ አናፋሾች ደግሞ በየተጠለሉትበት ሃገራትና በመዲናዋ አዲስ አበባ በመደበቅ የሚያማታ ዜና ይሰራሉ። የጠ/ሚሩ ወደ ጦር ግንባር መሄድ ጥቅም የለውም። ይህ ማለት ጠበንጃ ይዞ ይዋጋል ማለት አይደለም። ጠ/ሚሩ የራሱን ፍላጎትና የስልጣን ጥም ለማርካት ነው የዘመተው ወዘተ ይሉናል የከተማው አዋጊዎች። ስታስጠሉ። እስከ መቼ ነው ከራሳቹሁ ጋር እየተላተማችሁ የምትኖሩት። ሃገር ምጥ ላይ በሆነችበት ጊዜ ሃገሬን ወገኔን እወዳለሁ የሚል ሰው እንዲህ አይነት የስላቅ ነገር ይጽፋል? ግን ከታመመ ጭንቅላት የሚፈልቀው የታመመ ሃሳብ ብቻ ነው። ገምቢም ሆነ አፍራሽ ሃሳብ ግን ጊዜን ተመርኩዞ ሲቀርብ አንባቢም ሰሚም ሊያገኝ ይችል ነበር። አሁን ጊዜው በአንድነት የምንቆምበት የውጭና የወያኔን ወረራ የምንፋለምበት እንጂ ለኑዛዜ የምንቀርብበት ሰአት አይደለም። የፓለቲካ አዋቂ ነን፤ ያገባናል የምትሉ ሁሉ ጊዜን አይታችሁ አፋችሁን ክፈቱ።
    ከላይ ጸሃፊው ከእውነት ሸሽቶ እስከ የት ላለው/ላለችው የእኔ መልስ እስከ ገደል ነው። ጽንፈኝነት፤ ዘረኝነት፤ እኔ ብቻ ልኑር ባይነት ዛሬ ላለንበት የትርምስና የመገዳደል ፊልሚያ ላይ ከቶናል። ሰው ሰውን መናቁ ራሱንም መሆኑን ማየት አለበት። ዶ/ር እሌኒ እኔ እኮ ስብሰባው ላይ የተገኘሁት በዚህ በዚህ ጉዳይ ነው በማለት ወደኋላ ልትመልሰን ሞክራለች። ሲጀመር ከወያኔ ገዳይ ሃይሎች ጋር መዶሎት ምን ሲባል ይጀመራል። እንዴት ቤቴ ተፈተሸ ብላ አካኪ ዘራፍ ያለችው የሰው ልጅ ቤቱ መፈተሹ ሳይሆን የተገኘበት ህጋዊ ያልሆነ ነገር ነው ወንጀለኛ የሚያደርገው። ግን በምንም አይነት መስፈርት ዶ/ር ኤሌኒ በስፍራው መገኘት አልነበረባትም። ለዚህ ነው ወያኔና ወያኔ ቀመስ የሆኑ ሁሉ መተት እንደተደረገበት ሰው በግል የማሰብ ችሎታቸው ይቀማል የምንለው። እንደ እንቁራሪት አንድን ተከትሎ መንጫጫት ብቻ ነው። የመንጋ አስተሳሰብ እንዲህ ነው።
    ባጭሩ ወያኔ በትግራይ ውስጥ እያለ ጎረቤት ሃገሮችም ሆነ ክልልሎች ሰላም አይኖራቸውም። ወያኔ የሰላም ጸር ነው። የሞተው ሞቶ የቆሰለው ቆስሎ ጀጋኑ የተባለለት ሁሉ ልቡ ሲተነፍስ ያኔ ሰው ምን አልባት የወያኔን የመከራ ዶፍ አሻፈረኝ ብሎ ሊወቅጣቸው ይችል ይሆናል።፡አይ ካለም ከአጋም የተጠጋ ቁልቁላ ዝንተ ዓለም ሲያለቅስ ይኖራል እንደሚባለው የትግራይ ህዝብና ጎረቤቶችም ከመከራ ነጻ አይሆኑም። ወያኔዎች ከጣሊያን ፋሺዝም፤ ከጀርመኑ ናዚ የሚከፉ አውሬዎች ናቸው። ከባዶ ስድስት እስር ቤት የተረፉትን፤ ሞቶ መነሳት የተባለውን ጽሁፍ በካፒቴን ተሾመ ተንኮሉና ሌሎችንም የወያኔ አባላት የሰጡትን ቃለ መጠይቆች አገናዝቦ የክፋታቸው መጠን ልክ እንደሌለው መረዳት ይቻላል። ሰውን በተኛበት የሚገድል፤ ሲኖ ትራክ የሚነዳ፤ ገድሎ በአስከሬናቸው ላይ የሚጨፍር፤ እራት ጠርቶ አብልቶ በሰንሰልት እጅህን የሚያስር፡በአዲስ አበባ ብቻ የሰሩት ግፍ ይህ ነው አይባልም። የአማራው ጥላቻና የዘር ምንጠራው ጉዳይ ዓለም ያወቀው ነው። የወልቃይት እንባ ብቻ የወያኔን የግፍ ዶፍ ያመላክታል። ከወያኔዎች ጋር ቢፈልጉም አብሮ መኖር አይቻልም። መጥፋት አለባቸው። እርቅ ገለ መሌ የሚባለው ተመልሰው ሃገርም ሆኖ ሌላ እሳት ለመጫር እንጂ ሰላምን በፊትም አያውቋትም ወደፊትም አያውቋትም። ሞት ለወያኔ! በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share