የአዳነች አቤቤ ተቺዎች ኢትዮጵያዊ ከሆናችሁ አስተውሉ – ሰርፀ ደስታ

ሰሞኑን አዳነች አቤቤ ወያኔዎች ከፈለጉ ራሳቸው የጻፉት ሕገመንግስት አለ ያንን ተከትለው መገንጠል ይችላሉ አለች ተብሎ ከፍተኛ ግርግርና የጸረአዳነች ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ እየሰማሁ ነው፡፡ እኔ የሰዎችን ማንነት የማይበት የራሴ የሆነ ምልከታና መስፈርቶች አሉኝ፡፡ ይህች የአዳነች አበቤ የ ንግግር ሐረግ የተመዘዘችወ አደናች ከተናገረቻቸው ብዙ የቁጭትና አልህ ንግግሮች ሁሉ በጥንቃቄ ተጣርታ ነው፡፡ የአዳነች ሙሉ የንግግር መንፈስ ግን የሚነግረን ግን የሴትዮዋን ቆራጥነት፣ እልህና ቁጭት የሞላበት ጀግንነቷን ነው፡፡

አዳነችን ከዚህ በፊት በሰራቻቸው አንዳንድ ነገሮች የምነቅፍባት አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በእነእስክንድር ላይ በአቃቤ ሕግነት ያሴረቸው ወይም ከሴረኞች ጋር የተባበረቸው ከምንም በላይ ከሀዲነትን ሕሊና ቢስነት ነው፡፡ ከዛ በፊት እንዲሁ በገቢዎች ብዙ ስትባል ነበር፡፡ እነዚህ ነውረኛ ድርጊቶች ግን ከአዳነች አቤቤ ከራሷ የውስጥ ማንነት የሚመነጩ ናቸው ብዬ አላምንም፡፡ ከወያኔና ከወያኔ ፈረሶች ጋር ስትሰራ ይልቁንም ደግሞ በኦሮሞ ኦነጋውያ ውስጥ ስትሰራ በእንደነዚህ ያሉ ነውረኛ አሰራሮች መሳተፍ ግድ የሚልበት ጊዜ አለ፡፡ በእኔ እይታ ግን አዳነች አቤቤ ተፈጥሯዊ የሆነ ወይም በልምምድ የራሷ ያረገችው እንዲህ ያለ ነውረኝነት አለ የሚል እምነት የለኝም፡፡ አዳነች ዛሬ የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆነችበትን ሂደትም እኔ የምደግፈው አደለም፡፡ በእርግጥም የዲስ አበባ ከንቲባ የሆነችው እንደ ኦሮሞነት እንጂ እንደ ኢትዮጵያዊነት ብቃቷ ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ ሆኖም ግን አዳነች ከንቲባ የሆነችበት ሂደት በኦሮሞነት መንገድ መሆኑ ከፋ እንጂ ከንቲባነቱን በብቃት ለመወጣት ችግር ያለባት አይመስለኝም፡፡ በእርግጥም አዳነች ከንቲባ ከሆነች በኋላ በከተማዋ የምናያቸው አሰራሮች ይበል የሚያሰኙ ናቸው፡፡

ሰሞኑን ደግሞ አዳነች ከአዲስ አበባ ከንቲባነት ዘለግ ባለ ሁኔታ በቁርጠኝነት የተነሳችበት የጸረወያኔ የአዳነች እልህና ቁጭት የተሞላበት ወኔ ለእኔ እንደውም ግርምት ሁሉ አጭሮብጫል ፡፡ ይህች ሰው ዛሬ ኢትዮጵያ መሪ ባጣችበት ወቅት በሙሉ ሥልጣን የመሪነቱን ቦታ ብትይዝ ኢትዮጵያ በእርግጥም ኢትዮጵያን ትመስል ይሆን ነበር፡፡ ዛሬ ከወያኔ ጋር ከቀን አንድ ጀምረው አብረው የነበሩትን እየታዘብን ነው፡፡ አዳነች ዛሬ እየተንቀሳቀሰች የለችበትን አልህና ወኔ የተሞላበት እንቅስቃሴ እስኪ የትኛው ወይም የትኛዋ ባለስልጣን ሲያደርጉት ታያላችሁ?

ተጨማሪ ያንብቡ:  እንኳን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ዋዜማ አደረሰን!! - ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

በእኔ እይታ አዳነች ዛሬ እየሰራች ያለችውን ይህል እያንዳንዳቸው ግማሹን ያህል እንኳን አስተዋጾ ቢያደርጉ ወያኔ አሁን የደረሰችበት የወረራ መስፋፋት ይቅርና ዶቄት ተብላ ከተነገረላት ትቢያም ባልተነሳች ነበር፡፡ እንግዲህ ይህች ሰው ሰሞኑን ወያኔን እንደሚለው ከፈለጉ ትግራይን ራሳቸው በጻፉት ሕገመንግስት መሠረት መገንጠል ይችላሉ ስላለች ብዙዎች በአዳነች ላይ አፏጭተዋል፡፡ እውነታው ግን የምናያየው የአዳነች ንግግር እነሱ የጻፉትን ሕገመንግስት የሚባል ተፈጻሚ እንዲሆን ከመፈለግ ሳይሆን ይልቁንም የሴትዮዋን በወያኔ ላይ ያላት ጥርት ያለ አቋምና የወያኔ አሸባሪ ኃይል ፍላጎቱ መገንጠል ሳይሆን በኢትዮጵያ ላይ በወሮበላነት የመቀጠል መብቴን ተነጥቄያለሁ ብሎ እየተዋጋ እንደሆነ ለማሳየት የተናገረችው ነው፡፡

አዳነች ከወያኔ ሕገመንግስት ጋር ዝምድናም ያላት አልመሰለኝም፡፡ በባሕሪዋም በድርጊቷም፡፡ አዳነች ይሄ ሕገመንግስት የተባለ ነገር ሲሰራ አልነበረችም፡፡ አዳነች በቅርብ ጊዜ ወደ ላይ የመጣች ሰው ነች፡፡ አመጠጧም ደግሞ ቁርጠኝነት በተሞላበት የተግባር ስኬት እንጂ በፖለቲካዊ ውስልትና አልመሰለኝም፡፡ እንደሚገባኝ አዳነች ትኩረት እያገኘች የመጣችው በለማ መገርሳ ጊዜ ነው፡፡ በብልጠትና በአድር ባይነት አይመስለኝም፡፡ እንዲህ ያሉ ባህሪያት በሴትዮዋ ተፈጥሯዊ ማንነት ላይ አይነበቡም፡፡

የሆነ ሆኖ ዛሬ ወያኔን በቁርጠኝነት እየተዋጋ ያለ ባለሥልጣን አለ ከተባለ እኔ ማየት የቻልኩት አዳነች አቤቤን ብቻ ነው፡፡ አስተውሉ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከንቲባ እንጂ የባህርዳር፣ የሚሌ ወይም በአገር ደረጃ ያለ ግዛት አደለም፡፡ ዛሬ ከወንዱም ከሴቱም አንደም ባለስልጣን በጠፋበት ወቅት አዳነች እየተንቀሳቀሰች ያለችው እንደ አዲስ አበባ ከንቲባ ብቻ ሳይሆን እንደ ጦር መሪ፣ የደህንነት ሹምና የአገርን ክብር የማስጠበቅ ታላቅ ሥራ ላይ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ግርማ የጅብጥላ፤ ስምን ከሲመት መለየት የማይችል ብአዴናዊ እንኩቶ  

አሁንም አላለሁ አዳነች በኦሮሞነት የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆነችበትን ሂደት አጥብቄ እኮንናለሁ፡፡ አዳነች ግን በኢትዮጵያዊነት የአዲስ አበባ ከንቲባ ከመሆን በላይ ማንነት ያላት ሰው እንደሆነች አስባለሁ፡፡ ከብዙዎች ጋር የማንግባባበት ነገር ቢኖር እኔ ስለወደድኩትና የእኔ ብሔር ስለሆነ ብቻ ሥልጣን ላይ ስላለ የምደግፍ የእኔ ያልሆነው ከሆነ ደግሞ የመነቅፍ አደለሁም፡፡ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያኖች እንድትመራ ሕልሜ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያኖች በሁሉም ብሔር ተብለው በተሸነሸኑት አሉ፡፡ ኢትዮጵያነት በወሬ አደለም፡፡ በወያኔ ሕገመንግስት፣ በወያኔ ሰንደቅ፣ በወያኔ ሥርዓትና አሰራር እዲሆሁም አስተሳሰብ እየመሩ ወያኔን በአፋቸው እያወገዙ የሚቆምሩበን ቁማርተኞች እየታዩን አይመስለኝም፡፡ እንደነ አዳነች አቤቤ ያሉ ደፋሮችና እልኸና ቆራጦች ግን መሬት ላይ ያለውን እውነት እንዲህ ደፍረው ሲናገሩት በደቦ ለማውገዝ ቀዳሚ ነን፡፡ በዚህ መልኩ ነጻነት የሚመጣ አይመስለኝም፡፡ ኢትዮጵያኖች ሆይ እባካችሁ እናስተውል፡፡ የአዳነች አቤቤ ተቺዎች ኢትዮጵያዊ ከሆናችሁ በደንብ አስተውሉ፡፡ የወያኔና አጋሮቹ ሴራ ተባባሪ ከሆናችሁ ግን አስተውሉ አልላችሁም፡፡

አመሰግናለሁ፡፡

ቅዱስ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

አሜን!

                                          ——————————————————-

ሕገ መንግስቱን መሰረት ያደረገው የደብረጺዮንና የአዳነች ሕዝበ ውሳኔ

ትግራይን ሃገር ለማድረግ ካስፈለገ አሰራር አለ ሕግ አለ ….. ትግራይን በሕዝበ ውሳኔ መመስረት ይችላሉ፤ መገንጠል ካሉ ራሳቸው የፃፉት ሕገ መንግስት ላይ የተቀመጠ አንቀጽ አለ፤ በዛ መሰረት መሄድ ነው። – ወይዘሮ አዳነች አቤቤ
ለትግራይ ህዝብ መፃኢ ዕድል ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግ እንፈልጋለን – ዶክተር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል
ወይዘሮዋ እንዳሉት ንግግራቸው ሲጨመቅ ትግራይ የምትባል ሃገር ለመመስረት ይህ ሁሉ እልቂት ማስከተል ለምን አስፈለገ ? ይህ ሁሉ ውድመት መፈጸም ለምን አስፈለገ ? ጦርነትስ ለምን አስፈለገ ? ንቀታቸው እንጂ ለብቻቸን እንሁን ካላችሁ በሚል በርካታ እድሎች ቀርበውላቸዋል። ኢትዮጵያን አፍርሰን ሃገረ ትግራይን እንመሰርታለን ነው የሚሉት፤ ይህን ከፈለጉ በመከላከያ ሰራዊትና በንፁሃን ላይ ወንጀል መስራት ለምን አስፈለገ ? መገንጠል ከፈለጉ ራሳቸው የፃፉት ሕገ መንግስት አለ ፤ በዛ መሰረት መሄድ ነው ብለዋል።
ህወሓት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የ1983 ዓ.ም ዓይነት ሚና ሊኖረው እንደማይፈልግ አስታወቀ። የህወሓት ሊቀ መንበርና በህወሓት የሚመራው የትግራይ ክልል መንግሥት ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል ትናንት በሰጡት መግለጫ፥ የትግራይ ኃይሎች ወታደራዊ ይሁን ሌላ እንቅስቃሴ የመጨረሻ ግብ፥ በትግራይ ላይ ወንጀል የፈፀሙት አካላትን ለፍርድ ማቅረብ፣ ለደረሰው ውድመት ካሣ መጠየቅ እንዲሁም የትግራይ ህዝብ መፃኢ ዕድል ህዝበ ውሳኔ እንዲወስን ማድረግ መሆኑ ተናግረዋል። የወቅቱ የኢትዮጵያ መንግሥት «በውድቀቱ ዋዜማ» ላይ ነው ያሉት ዶክተር ደብረ ጽዮን፣ «የኢትዮጵያን መንግሥት ለመጣል እና ቀጥሎ ያለውን የሽግግር ሁኔታ ለማመቻቸት» ህወሓትን ጨምሮ ዘጠኝ የፖለቲካ ድርጅቶችን የያዘ ግንባር ተመስርቶ እየተሠሰራ ነው መሆኑንም ገልጸዋል።
————————————————

5 Comments

  1. የአዳነች አቤቤን ተችዎችን በተመለክተ የተሰጠው ማሳሰቢያ እና ሥነ ጽሁፉ መልካም ነው ። ወ/ሮ አዳነች ለሰራቸው ወቀሳ ለምትሰራውም ሙገሳ መሰጠቱ እርምት ለመውሰድ ይጠቅማል የሚል ግምት አለኝ።ሆኖም ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የኦሮም ዝርያ በመሆኗ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባነቷን መጥላትህ ታላቁ ዘረኛ መሆንህ አይደለምን? በጽሁፍህ በኢትዮጵያዊነት ብዙ ሥራ እየሰራች መሆኗን እያምንክበት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ መልካም ከሰራች እና ካገለገለች? ብሄሯን መጥላትህ እንዲያው ብሄርተኛ እና ዘረኛ መሆንህ ተረዳሃውን? ምንም እንኳን ጠፍቶ ባይጠፋም በአሁን ሰዓት ለሀገራችን ለኢትዮጵያ የአንድነት እና የህብረት ሰበካ እንጂ የዘረኝነት ስበካ አያዋጣም።እንዲሁም የጠባብነት ህሊናን ማገገም መልካም ነው።
    ዘረኝነት፤ብሔርተኝነ ይውደም

  2. አልፈልግም እያለ ሁሌ አሻፈረኝ የሚልን ህብረተሰብ በግዝትም ሆነ በልመና አብሮ እንዲኖር ማድረግ አይቻልም። ወያኔዎችና አሽቃባጮቻቸው ዓላማቸው ኢትዮጵያን ማዳከምና መገነጣጠል ስለሆነ ይመቻቸው ትግራዋይ ነን የሚሉትም ይገንጠሉ። ምን አልባት ከኤርትራ ጋር ተዛምደው ያው ጫካ እንዳሰቡት ይኑሩ። ግን አሁን ባለው ሁኔታ ኤርትራ ከወያኔ ጋር የመገጣጠም ሃሳብ የላትም። ግን ፓለቲካ አሻጥር አይደል። ምን ይታወቃል?
    በመሰረቱ ከንቲባዋ የተናገረቸው ሳይሰነጠቅ ሳይለጣጠፍ ለሰማው እውነቱን ነው። ከፈለጉ በህገመንግሥቱ መሰረት መገንጠል ይችላሉ። ለዚያ አይደል እንዴ አንቀጽ 39 የተነደፈው። ሁሉ እኔም ልንገጠል እኔም ሃገር ልሁን ሲል ወያኔ የሃገሪቱን ሃብትና ንብረት ለ 30 ዓመት ሲሟጥ ኑሮ አሁን ትግራይ ገብቶ የትግራይ ህዝብ ተጨፈጨፈ ይለናል። ለመሆኑ የትግራይ ህዝብ መቼ ነው በወያኔ ዘመን ጥያቄ መጠየቅ የተፈቀደለት? ተማረኩ የተባሉት ህጻናት የሚናገሩትን የትግራይ ልጆች በውጭና በውስጥ ያሉ ከእውነት ጋር ማዛመድ አቅቷቸው አይደለም በነሲብ አፍቃሪ ወያኔ ስለሆኑ በጭፍን ህዝብ ሲተላለቅ በለው ይላሉ። የጭፍን አምልኮ ጣኦታዊ የሚሆነው ለዚያ ነው። ወያኔ ለትግራይ ህዝብ ጣኦት መሆኑ መቅረት አለበት።
    ከዚህ ሁሉ በላይ ችግራችን በዘር መሰለፋችን ነው። ያ አሰላለፍ ሰውን በሰውነቱ መዝኖ እውነትን እንዳናይ አይናችን ጨፍኖታል። አሁን በአማራና በአፋር ወያኔ እየፈጸመ ያለው በደል ለዘመናት የሚዘልቅ ለትግራይ ህዝብ ሸክም የሚሆን ነው። የበቀለ እህል ሳይቀር ፍሬ እንዳያፈራ የሚያወድሙ እብዶች ናቸው። የሚገርመው ወያኔ በእነዚህ አካባቢዎች የሚፈጽመው በደል አሜሪካኖች ኔቲቭ ኢንዲያንስ ላይ ካደረሱት በደል ጋር ይነጻጸራል። አሜሪካኖች የምግብ እህሎቻቸውን በማውደም፤ እንሳሳቶችን ለማዳና ያለመድ ለምግብ የሚያገለግሉትን ሁሉ ነበር እየነድ ገደል ሳይቀር የሚጨምሩባቸው የነበረው። አይ ያሉትን ደግሞ እንዲህ እና እንዲያ አደረጋችሁ እያሉ የገደሏቸውና ያንጠለጠሏቸው ቁጥር ስፍር የላቸውም። እንዲህ ሰውን ካስበረገጉና ከገደሉ በህዋላ የራሳቸውን ስካንድኔቪያን፤ አውሮፓውያን ሰዎች በማምጣት እንዳሰፈሯቸው ታሪክ አስረግጦ ይናገራል። አዎን ሰው ይሄ እኮ የቆየ ታሪክ ነው ይል ይሆናል አሁን ያለው ሁኔታም ከዚህ አይሻልም። የወያኔ አሰራርም ከዚሁ የክፋት ማሰሮ የተጨለፈ ለመሆኑ ተግባራቸው ያሳያል። ወያኔ ማለት አረመኔ፤ የሰው ባህሪ የሌለው የሰዎች እንስሳ ጥርቅም ማለት ነው። ለ 30 ዓመት ለጦርነት ራሱን አዘጋጅቶ አሁን በሚፋለምባቸው ስፍራዎች የሚረግፈውን የትግራይ ልጆች የተመለከቱ አንድ የወሎ አዛውንት የቃለ መጠየቅ ለሚያረጉላቸው ጋዜጠኞች እኔ አንድ ጥያቄ አለኝ በማለት ” ትግራይ ውስጥ የሰው መፈልፈያ ማሽን አላቸው እንዴ”? በማለት ነበር የጠየቁት። ብንገላቸው፤ ብንገላቸው አያልቁም። ይህ የእብደት ጦርነት ከመክፋቱ የተነሳ አኖሌን ያቆመልን ወያኔ የሴት ጡት እስከ መቁረጥ፤ በሲኖ ትራክ ሰው ላይ እስከመንዳት፤ ሴቶችን በደቦ እስከመድፈር፤ ካህናትን ቀሳውስትንና የመስጊድ መሪዎችንና አምላኪዎችን በጭፍን የረሸነ የሚረሽን ድርጅት ነው። እርቅ ከወያኔ ጋር የማይታሰብ ነገር ነው። እጅ መስጠት እንጂ! ሰው ቆርጦባቸውል። ያ በወታደራዊ ሃይል እናንበረክካለን የሚባለው ጡሩንባም አይሰራም። ከአሁን በህዋላ ወያኔ ቆሞ ይሄዳል ብሎ መመን ማበድ ነው። የጠ/ሚ አብይ መንግስት እንኳን አሸባሪ ካለው ጋር ተደራድሮ ነገሮች ቢያረግብም የትግራይ ህዝብ የሞተና የቆሰለ ቆጠራ ሲያደርግ ወያኔዎችን እየፈለገና እያደነ እንደሚገላቸው አልጠራጠርም። የዚህ ሁሉ የትግራይ ልጆች ደም ተገብሮ የተገኘው ሊጥ ብቻ ነው የሚሆነው። ለዛውም ጊዜ ያለፈበት ሊጥ። እንጀራ የማይወጣ። አይ ግፍ!
    የወ/ሮ አዳነችን ሃሳብ የሚለክፉ ራሳቸው የተለከፉና ለክፈው ለለካፊ የሚሰጡ ሃገር አይቆረስም አይሸረፍም የሚሉ ናቸው። አብሮ መኖር ማለፊፍያ በሆነ ነበር ግን አልፈልግም ላለ ግን አብረህ ኑር አይባልም። ይሂዱ። ያኔ ለሁለት ተከፍለው እርስ በእርሳቸው ይተላለቃሉ። ወያኔ ዝንተ ዓለም አይኖር። እነርሱና አስተሳሰባቸው ሲቀበር እንደገና አብረን መኖር እንችል ይሆናል። በልመና ወይም በማስገደድ የሚሆን ነገር የለም። ተገንጥለው ያለፈላቸው የአውሮፓም ሆነ የአፍሪቃ ሃገሮች የሉም። ያው የጨነቀው እርጉዝ ያገባል አይነት እንጂ! በቃኝ!

  3. ለደግነቱ ‘ማን ላይ ቆመሽ ማንን ታምያለሽ’ የሚባል ከኢዛና ጀምሮ ኣብሮን የተጓዘ ምሳሌ ኣለና፣ እኔም እንደናንተ መንፈሰ ጥላቻ ብቻ ብሆን ኖሮ፣ ‘ተልባ ቢንጫጫ ባንድ ሙቀጫ’ ልል እችል ነበር፣ ግን ሙሶሶዬ ሁሉ ጥላቻዊ ስላልሆነ ይሄንን እንደከጀለኝ እንጂ እንዳላልኩት ኣድርጋችሁ ውሰዱልኝ፣ ኣይተ ተስፋ የሚከተለውን ካንተ ያወረትኩትን ጥቅስ ብቻ እንደ ኣስተዋፅኦ ልውሰድልህ ‘የጭፍን አምልኮ ጣኦታዊ የሚሆነው ለዚያ ነው። ወያኔ ለትግራይ ህዝብ ጣኦት መሆኑ መቅረት አለበት’
    በተረፈ ግን የናንተውን የዲሲ እና የባህርዳርን መሽቀርቀርን ረሳችሁ እንዴ? ለዚያውም ደግሞ ፅላተ ፅዮን ስትደፈር፣ ‘ካልጠገቡ ኣይዘሉ፣ ካልዘለሉ ኣይሰበሩን’ በኋላ ያፈለቅነው ብሂል ስለሆነ ኢዛና ኣያውቀውም ነበር !!

    • ሃሳብህ ግን የት ላይ ነው? ግራ ያጋባል? ነገሬን መዋስህ ላይቀር ሰው እንዲገባው አታረግም ነበር የራስህን እይታ? እሾህን በእሾህ ነውና ነገሩ ሙቀጫውም ተልባውም በለሌበት ሃገር እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ወቀጣ የምታካሂደው? ስለ ምን ጽላት ነው የምታወራው? ማንስ ነው ጠግቦ የዘለለና የተሰበረ። እውነት አፍጣ እዪኝ እያለች ከእውነት ሮጦ የፈጠራ ታሪክ ውስጥ መወሸቅ ምን ይባላል? እኔ የትግራይም ሆነ የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላቷ ወያኔ እንደሆነ ላፍታ አልጠራጠርም። በዘመናቸው ሁሉ የፈጸሙት ክህደትና በደል ሲፈለግ የሚገኝና አሁናዊም እውነት ነው። እውነትን አላይም ለሚል ደግሞ ተንጋጦ እየተመለከተም ሰማይም የለም ማለቱ አይቀሬ ነው።
      እንዲያው ሁሉም ይቅር የዘር ፓለቲካውም የድንበር መስፋፋቱንም ምክንያት እንተወው ብለን በሰውኛ ቋንቋ ራሳችን ብንፈትሽ አሁን ማን ይሙት በ 21ኛው ክፍለ ዘመን ትግራይ አማራ እየተባባለን መገዳደል ነበረብን? እየሆነ ያለው ግን ይህ ነው። ታዲያ አላበድንም የምንል ከዘር ተሰላፊዎች ወገን ሆነን፤ ወንዝ በማያሻገር ቋንቋና ረብ በለሌው እምነትና ሃይማኖት ተጠፍረን የወንድምና እህቶቻችንን ሬሳ ላይ ጨፍረን ለአውሬና ለሰማይ አሞራ ራት የምንጥል የሰው አውሬዎች ነን። አንድ እውቅ ፈላስፋ ” ሙታናቸውን ያከበሩ፤ ራሳቸውን አከበሩ” ይለናል። እኛ ግን የሞተው አማራ ነው ወይስ ትግሬ፤ ኦሮሞ ነው ወይስ ሌላ በማለት ሰዎችን በሞታቸው እንኳን የዘር ሸማ የምናለብስ ደንቆሮዎች ነን። ባጭሩ የትግራይ ህዝብ በወያኔ ክፋትም ሆነ በፍላጎት መገንጠል ከፈለገ ማንም ሊከለክለው አይችልም። ግን ችግሩ ሲኖሩ ልጥቅ ሲለዪ ደግሞ ምንጥቅ ነው። በሁለት ቢለዋ መብላት ይቅር ነው። እውነቱ ይህ ነው።

  4. ሶስቱ ፍራክሽዮኖቻችን፣
    .ወታደራዊው የስልጣኔ ምረሻን የሚያከናውነው ቆልዓ ትግራይ ባንድ በኩል፣
    .በሌላው በኩል ደግሞ Ideenlose schmarotzen ሌባ ወያነዎች፣
    .እንደ Bindeglied ዘላለሙን ማን እንደሚልከውም የማያውቀውና በወሮበላዎች ተገልጋዩ፣ ከፕያሳ ኣካባቢም ወሮበላዎችን ኣስከትሎ ኣፄ ምኒልክ ግቢ ልግባ ብሎ ፈንገል ፈንገል ባዩን ልንበውዛቸውና ልንበታትናቸው ባለፈው 40 ኣመታትም ኣልተሳካልንም፣ ኣሁንም እንዳለ እስካለ ጊዜ ድረስ፣ በተለይ ለራሳችንና እንዲሁም ለሌሎች ችጋር ጠሪዎች እንደሆንን ኣለነው…..!
    በወሮበላዎች ድህነትና ድንቁርና ከመተዳደር ምህረቱን ያውርድልን…!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share