ወያኔ በአብይ አህመድ የተሳሳተ፣ ደካማ አመራር እየተመራ ያለውን የመከላከያ ሰራዊት ሊያሸንፉ ይችላሉ

ወገኖች ስለ ጦርነቱ ትንሽ ልበላችሁና ለዛሬ ላብቃ፡፡

ግርማ ካሳ

የወሎ ክፍለ ሃገር ይባል በነበረው በሁሉም ቦታ ማለት ትችላላችሁ ጦርነት አለ፡፡ ወያኔዎች ደሴን ለመያዝ ሞከረው ውጫሌ ከሽፎባችዋል፡፡ ሆኖም እንደገና በሌላ መነገድ መሞከራቸው አይቀርም፡፡ የቀድሞ ወሎ ታላላቅ ከተሞችን ሰቆጣ፣ አላማጣ፣ ኮረም፣ ቆቦ፣ ላሊበላ፣ ወገልጤና፣ ጋሸና፣ ሃራገበያ የመሳሰሉትን ወያኔዎች ይዘዋል፡፡

የወሎ ሕዝብ የአብይ አህመድ መንግስት ፊቱን አዙሮበታል፡፡ በፌዴራል መንግስቱ ተክዷል፡፡ ሕዝቡ አቅም ባይኖረውም፣ ባለው ሁሉ ወያኔን ለመመከት ተነስቷል፡፡ ወያኔዎች በመከላከያ ውስጥ ካለው ሳቦታጅ፣ ካላቸው የከባድ መሳሪያ የበላይነትና ከፍተኛ የታጣቂዎች ቁጥር የተነሳ በአንዳንድ አካባቢዎች በለስ ሊቀናቸው ይችላል፡፡

ከአንድ አመት በፊት መከላከያ መቀሌን ይዞ ነበር፡፡ ግን አሸንፎ እንዳልነበረ አሁን ሁላችንም የተረዳን መሰለኝ፡፡ አሁንም እንደዚሁ ነው፡፡ ሕዝብን ማሸነፍ አይቻልም፡፡ በወልዲያ፣ በቆቦ ተቆጣጠርን ባሉበት ቦታ ብዙ ወታደሮቻቸው በሽምቅ ውጊያ እያለቁ መሆናቸውን እነርሱም ያውቁታል፡፡ወያኔዎች ሕዝቡ እንዲደግፋቸው ካላደረጉ በቀር መቆየት አይችሉም፡፡ ህዝቡ ደግሞ ስለ ወያኔ ምን እንደሚያስብ የሚታወቅ ነው፡፡

ምን አልባት የወሎ ሕዝብ በአብይ አህመድ ብልጽግና ትልቅ ክህደት ስለተፈጸመበት፣ ወያኔዎች ደግሞ “እኛ ችግራችን አብይ አሀመድ ጋር ነው” የምትል ጨዋታ ስላላቸው የተወሰኑ ስዎች ማታለል ይችሉ ይሆናል፡፡ ግን እርሱም ቢሆን ያንን ያህል በሰፋ መልኩ የሚያስኬድ አይደለም፡፡

ደግሜ እላለሁ ወያኔ በዶር አብይ አህመድ የተሳሳተ፣ ደካማ አመራር እየተመራ ያለውን የመከላከያ ሰራዊት ሊያሸንፉ ይችላሉ፡፡ ልክ ያኔ የደርግ ስራዊት እንዳሸነፉ፡፡ ነገር ግን ያኔ ሕዝብ አልተዋጋቸውም፡፡ ዘመቻ ዋለልኝ ብለው በወሎ በኩል ዘመቻ ቴዎድርስ ብለው በጎንደርና ጎጃም በኩል አዲስ አበባ የገቡት እየሮጡ ነው፡፡ በብዙ ቦታ በሰላም አሳልፉቸዋል፡፡ አሁን ግን የተለየ ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ሕዝብ እየተዋጋቸው ነው፡፡ ሕዝብን ደግሞ ማሸነፍ አይችሉም፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ውጊያዎችን ቢያሸንፉም ጦርነቱን አያሸንፉም፡፡ ጀነራል ደጎል፣ በናዚ ጦርነት ወቅት፣ ” La France a perdue une battaille ! Mais la France na pas perdu la guerre” (ፈርንሳይ አንድ ዉጊያ ተሸንፋለች፣ ጦርነቱን ግን አልተሸነፈችም” እንዳለው፣ አሁን አንዳንድ ቦታ ውጊያ ወያኔ ብታሸንፍም፣ ጦርነቱን ማሸነፍ አትችልም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራን መደራጀት የሚያማቸው የኢትዮጵያን ትንሣኤ የማይሹ ፀረ - ኢትዮጵያ ሃይሎች ናቸው! (ሐይሉ አባይ ተገኝ)

6 Comments

  1. ታየ ደንዳ የሰላም ሚንስቴር የህወአቱ አብረሀም የመከላከያ ሚኒስቴር ታከለ ኡማ ሚኒስቴር። ብርሀኑ ነጋ ሚኒስተር አገኘሁ ተሻገር አባዱላ ሌንጮ ለታ አማካሪ። አረጋዊ በርሄ ዋና ሰው ..ብርሀኑ ጁላ ዋናው አዝማች…..በሆነበት የኦሮሞ ጉልት ጦር ቁጭ ብሎ በሚስቅበት አገር እንዴት ነው ጦርነት የምናሸንፈው። ሲጀመር ጦርነቱን ፋይናንስ የሚያደርጉት እነ አብይ መሰሉኝ ጥላችሁ ሂዱ እያሉ። ለነገሩ በነብስ ወከፍ ይዋደቃል እንጅ የፋሽስት ትግሬ ጦር ዳግም አዲስ አበባን አይረግጥም።

  2. ይህ ጦርነት ድንገት በዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን መምጣት የተከፈተ ግጭት አርገው የሚወስድ ፓለቲከኞች ስተዋል። ወያኔ ለዘመናት አቅዶ፤ ተዘጋጅቶ፤ የውጭና የውስጥ ሃይሎችን ገዝቶ ነው ውጊያውን የከፈተው። አላማው አንድ ነው። እኛ የበላይ ያልሆንባት ኢትዮጵያ ትፍረስ ታላቋ ትግራይንም እንመሰርታለን ነው ግባቸው፡ አሁን የሚያሳዪት ጭካኔ ድሮ በጫካ እያሉ ሲፈጽሙት ከኖሩት የተለየ አይደለም። የጭካኔያቸው ስፋት አሁን ሌላውንም እየላሰው በመሆኑ ነው ኡኡታው የበዛው። ከከተማ እስከ ገጠር ቀድሞ ይፈጽሙት የነበረው ዝግናኝ ድርጊት አሁን በስፋትና በእንስሳትም ላይ ሳይቀር በውስጥ አሻጥሮኞቻቸው እየተመቻቸ መስፋፋቱ የበለጠ ህዝባችን ለመከራና ለችጋር አጋልጦታል። ሰው እንደ በግ ተጎትቶ የሚታረድባት ሃገር ይሄም ያም የድረሱልኝ ጥሪ ማሰማቱ ሰሚ የለውም።
    ጉራና ፉከራ ተግባር አይሆንም። ወያኔ ቆርጦ ተነስቶ ይህንም ያንም እየቀጠቀጠ ነው። የክፋታቸውን ጥግ ወደ ጎን አድርጎ ወታደራዊ ስራቸውን ለተመለከተው ወያኔን አለማድነቅ አይቻልም። ቀጠቀጥናቸው፤ ተደመሰሱ፤ ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር አለቁ እየተባለ ጆሮአችን ያደነቆረው የሃበሻው ቱልቱላ ዛሬ ደሴ ለመድረስ ጥቂት ሲቀራቸው ምን ያወሩን ይሆን? ህዝቡን ወያኔ መጣባችሁ እኛም ልንወጣ ነው ውጡ የሚሉት እነማን ናቸው?መከላከያው አይደለም እንዴ? ለምንስ ወያኔ ቤቶችን ሰው ሞልቶ ማቃጠል ፈለገ? ህዝቡ ቁርጠኝነታቸውንና ቆራጥና አረመኔ መሆናቸው አይቶ ሃገር ጥሎ እንዲሸሽ ነው። ግን የጦርነቱ ሴራ ውስብስብ ነው። እኛ የምናየውና የምንሰማው ላይ ላዪን ነው። አሁን በሰሜን ኢትዮጵያና በአፋር የሚደረገውን ተግባር ባለፉት 30 ዓመታት በአርሲ፤ በሃረር፤ በጂማ፤ በአዲስ አበባና ዙሪያዋ እንዲሁም በቀሩት የሃገሪቱ ክፍል የደረሱትን ዘግናኝ አማራ ጠል ግፎች ላመዛዘነ ያኔም የወያኔ እጅና ተላላኪዎቻቸው ነበሩበት አሁንም አሉበት። የሚበልጡት በሰራዊቱ ውስጥ የተሰገሰጉ የዘር ፓለቲካ አራማጆች የዚህ ችግር ዋናው ፈጣሪዎች ናቸው። ሌላው ቀርቶ ለእርዳታ የመጣ እህል ከተከማቸ በህዋላ ወያኔ መጣ በማለት ስፍራውን ለቀው ወተው የተከማቸው እህል ወያኔ እጅ እንዲገባ የሚያደርጉ በሰው ደም የሚነግድ የመከላከያ አባላት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
    ኢትዮጵያ አትፈርስም ይሉናል እየፈራረሰች እያየን። ጣራው እስኪደረመስ ነው የሚጠብቁት? ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር ይሉናል። የክተት ጥሪ ተደጋግሞ ይታወጃል። ግን ያንድ ሰሞን ግርግር ይሆንና ሌላው ወደ መሸታ ቤቱ ይጓዛል። ጠላ ቤት ሆኖ ይፎክራል። ሲልለት በማያልቀው ስብሰባ መካከል ገብቶ ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል። የወሎ፤ የጎንደር፤ የአፋር አርሶ አደር ግን በከባድ መሳሪያ ቤቱ ይቃጠላል፤ ይገደላል፤ ይፈናቀላል። በቅርቡ አንድ የሥራ ጓደኛዬ (ዶ/ር) ትግሬዎችን እኮ አብይ ጨረሳቸው አለኝ። አይ እየተጨራረስን ነው ብትል አይሻልም ስለው እንደመሳቅ ብሎ እሱማ አፍሪቃዊ ባህሪ ነው በማለት ጫወታችን ትተን ወደ ተገናኘንበት ተግባር ገባን። የሚያሳዝነው በዪቱብ፤ በቲውተር፤ በፌስ ቡክ በሌሎችም ሃገር በቀልና የውጭ ሚዲያዎች የሚናፈሰው ወሬ 99.9% የተጋነነ እና ውሸት ነው። ግን በወሬው ሳቢያ ክፍያ ለማግኘት የማይደረግ ሸር የለም። ደሴን ወያኔ ተቆጣጠረ፤ የኢትዮጵያ አየር ሃይል አውሮፕላን ተመትቶ ወደቀ፤ ዶ/ር ደብረጽዪን ተገደሉ፤ 40 ሴቶች ተደፈሩ ምን የማይባል ነገር አለ? ማን ነው ቆሞ ምስክር የሚሆነው ለዚህ ሁሉ ዘገባ? አዎን እናውቃለን እንኳን በሃበሻው ምድር ሃሰትና ክህደት በበዛበት ይቅርና በሌላው የጦር አውድማም ቢሆን የጦርነት ቀዳሚ ሟች እውነት ራሷ ናት። ግን የሃበሻው ቅጥፈት ከሁሉም ይለያል። አይጣል!
    አሁን አቶ ግርማ ካሳ ወያኔ ሰራዊቱን አሸንፎ አዲስ አበባ ሊገባ ይችላል ማለቱ ያው ጻድቃን በ15 ቀናት ጦርነቱን እንደመድማለን ብሎ የለ። ያው ቀን እየቆጠርን ነው። የአቶ ግርማ ሃሳብ ጭራሽ አይሆንም ብሎ መገመትም አይቻልም። ሊሆን ይችላል። አሁን እንሆ የዶ/ር አብይ መንግስት ተስፋ የቆረጠም ይመስላል። መቀሌ አካባቢን ለሁለተኛ ጊዜ በአውሮፕላን እንደተመታ እያነበብን ነው። ያኔ መቀሌ ሰራዊቱ ገብቶ እያለ የተደበቁና የተነጠቁትን መሳሪያዎችን ሁሉ አግኝቻለሁ አስመልሻለሁ ያለው ያ ሰራዊት እግሬ አውጭ ብሎ ሲወጣ ያለቀው ቤቱ ይቁጠረው። ግን ሁሉ ሽፍንፍን በሆነበት ሃገር ላይ ማን ሞተ ማን ተያዘ የሚለውን ለቤተሰብ እንኳን ማስረዳት አይቻልም። የአማራና የአፋር ህዝብ ከጎኑ ተሰልፎ አይዞህ እያለው፤ የቆሰለን እያከመ፤ የተራበውን ሰራዊት እየመገበ፤ ከጎኑ ሆኖ ወይም ቀድሞ ወደ ፍልሚያ በመግባት ከወያኔ ጋር እየተናነቀና መንገድ እየመራው ድል ያልቀናው ይህ ሰራዊት ወያኔ በህዝቡ ላይ ባይጨክን ኑሮ እስከ አሁን ወያኔ 4 ኪሎ ይገባ ነበር። ወያኔ በህዝቡ ላይ የሚፈጽመው በደል ግን ሰውን በጎበዝ አለቃ እንዲደራጅና እየገደለ እንዲሞት አድርጎታል። ግን ለአመታት የተዘጋጀና የሰለጠነ በታንክና በከባድ መድፍ የታገዘን ሃይል በድንጋይ፤ በድላና በኋላ ቀር ክላሽ ማሸነፍ እንደማይቻል የታወቀ ነው። የፓለቲካው አሻጥር ይቀጥላል። የሚሞተው ይሞታል። የሚፈናቀለው ይፈናቀላል። ወያኔም ለአውሮፕላን ድብደባ የከፋ ምላሽ ይሰጣል። ያው ሲገሉና ሲገዳደሉ መኖር ነው። ሌላውን ጠብቆ ማየት ነው።

  3. ኢትዮጵያ እየተዋጋች ያለችው፣ 30 አመት ለጥፋት ከተዘጋጀው መሰሪ አሸባሪ ኃይል ጋር ነው። ለዚህ ቀን የቀበረውን መሰሪያ ተጠቅሞ እየተዋጋ ነው። በውስጣችን ባሉትና በሆድ አደሮች ጭምር ነው። ለማንኛውም ሙያ በልብ ነው። አለመሸበር ነው። ብዙ ዋጋ ቢያስከፍልም፣ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች። የአመራር ስህተት ሊኖር ይችላል። ምንም ከህዝብና ከመንግስት ጋር መሆን ነው። ወሎ ተክዷል ማለት ግን ተገቢ አይደለም።

  4. በእኔ እምነት የወያኔ ፍሽስት ዘረኛ ቡድን አዲስ አበባን ይቆጣጠራል ማለት ትልቅ ንቀት ነው።የሚዋጉት አማራ ጨቆኝ ነው እያሉ ሲገሉት እና ሲያሳድድት የጅምላ ጭፍጨፉ ሲደሩጉበት ከነበር ህዝብ ጋር ነው።ምናልባት የፊደራል መንግስቱ የምእራባዊያንን ጫና ፈርቶ ፈራ ተባ ቢልም በሌሎች የአማራር ድክመት ጦርነቱንም ቢራዝሙት ኢኮኖሚው እየወደቀ በሄደ ቁጥር ለአብይ መንግስት ህዝባዊ አመጽ አስጌ እንደ ሚሆን ምንም ጥያቄ የለውም። ስለዚህ የፊደራል መንግስቱ ያለ የለለ ሃይሉን ተጠቅሞ በአጭር ግዜ ውስጥ ጦርነቱን ማጠናቀቅ አለበት!!!!

  5. We know that this time for all Ethiopians especially for Amhhar and Afar people is the most challenging and dangerous time,so what we need is that all of us must stand together inorder to over come this challenge and danger , individuals may do fauls but this doesn’t cause us to fight amongst us, everyone should have patience and do all we can to our government and the National Army and also the regional army,soon the victory will be ours may Almighty God help and bless Ethiopians.

  6. NOW ETHIOPIA IS GOING THROUGH A VERY TRYING TIME. BUT VICTORY IS ENEVITABLE. IT IS OBVIOUS THAT THERE ARE TRAITORS AND SECRET AGENTS IN THE GOVERNMENT WHO WHO ARE TRYING TO DESTABILISE THE RESTORATION OF LAW AND ORDER MILITARY CAMPAIGN BY THE GOVERNMENT. IT IS VERY SAD INNOCENT CITIZENS UNDESERVEDILY ARE DYING AND SUFFERING SEVERELY. BY THE REBEL,TRAITOR, MAFIA,, MURDERER, LOOTER, LAND GRABBER, BARBARIAIAN WOYANE JUNTA. THIS BARBARIC JUNTA IS UNLEASHING UNTOLD KILLINGS AND DESTRUCTION .THE IDIOTIC WOYANE IS DIGGING DEEP ITS OWN INEVITABLE GRAVE. NOT DREAMS EVEN IN THEIR NIGHTMARE WOULD THEY EVER BE BACK IN POWER NOR BREAKAWAY TIGRAI WHICH IS PART AND PARCEL OF ETHIOPIA. THIS IS NOT A WISHFUL THINKING BECAUSE THE POLITICAL CHANGE IN ETHIOPIA AND TOTAL DEMISE OF WOYANE IS THE DEVINE WORK OF THE ALMIGHTY GOD. HENCE, WHO CAN WIN AGAINST GOD. NO ONE AT ALL..THE FATE OF WOYANE IS ALREADY PREDETERMINED AND DESTINED TO HELL WHICH WILL HAPPEN VERY SOON. FELLOW ETHIOPIANS TAKE HEART AND BE STRONG FOR THE ALMIGHTY GOD FAVORS ETHIOPIA. OUR MOTHERLAND, ETHIOPIA ?? WILL MARCH IN VICTORY AND RAPID DEVELOPMENT.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share