ወደር የለሹ የወያኔ ቅዠትና የምቀኝነት ጥግ (ድንቁ ሞላ)

tplfስለወያኔ ቅዠት፦

የወያኔ ርዝራዦች ሳያቋርጡ እንደሚለፈልፉት ቢሆን ኖሮ የእነርሱ የፈጠራ ፕሮፓጋንዳ ብቻ ትክክለኛ፣ ትህነግ ብቻ ጀግና፣ አማራ ብቻ የሚሞት፣ የትግራይ ወታደር በጥይት የማይመታ …ወዘተ ነው የሚሉት ቀደዳ መሬት ላይ እውነት ሆኖ በተገኘ ነበር፡፡ይህ በደማቸው ውስጥ ስር የሰደደው የውሸትና የሀስት ቀደዳ ከዱሮ ጀምሮ የተጠናወታቸውና አብሯቸው እድሜ ልክ የኖረ በሽታቸው ነው፡፡ በአጭሩ ትዝብትን የማያውቁ የከንቱ ከንቱዎች ናችው፡፡ የሚገርመውም ጭፍን ለጭፍን እርስበርሳቸው በውሸቱ ላይ ተማምለው ሲመመሰጋገኑና ሲደጋገፉ ማየቱ ነው፡፡ያፈጠጠና ገሐድ የወጣ ውሸትን ሽምጥጥ አድርገው ክደው ጉልበታም እውነት ለማስመሰል በድርቅና ክችች ሲሉ ቅንጣት የማያፍሩ ናቸው፡፡ወያኔዎች ከነርዝራዦቻቸው በደደቢት ፍልስፍና ተመርዘው ባሉበት ተቸክለው ቀርተዋል፡፡ በዚህ ላይ እንደ ታምራት ላይኔና ልደቱ አያሌው አይነቶቹን ሆድ አደሮችና በድፍን አማራው ዘንድ የተተፉትን ልክስክሶች ለምስክርነት ይጠቅሳሉ፡፡ ይህ የሆድሞቹ ምስክርነት ከወያኔ የ27 አመታት እጅግ የቆሸሸ ታሪካቸው ማለትም ከሌብነታቸውና ከውሸታምነታቸው ጋር ሲደመር ወደር ለሌለው እጅግ የወረደ የወያኔ ማንነት ማረጋገጫና በቂ ማሳያ ነው፡፡

ማንም ሊክደው የማይችለውና ነግር ግን ማንም ደፍሮ ሊናገረው የማይፈልገው አንድ እውነት አለ፡፤ይሄውም የሰሜን እዝን በዘር እየለዩ በምሽት የተካሄደን ዘግናኝ ጭፍጨፋን ጨምሮ አሁን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ወያኔ አቅዶ የጀመረበት ዋናው ምክንያት ለም የሆኑትን የራያና ወልቃይት የአማራ መሬቶችን በትግራይ ስር አድርጎ ከኢትዮጵያ በመገንጠል ታላቋ ትግራይን በአገርነት ለመመስረት ባለመው ቅዠቱ መሰረት ነው፡፡ በአፈሯ መሸርሸርና በድርቀት ዑደት ውስጥ የምትኖረው ወጣ ገባዋ ትግራይ ወያኔ በጉልበት ወስዷቸው ከነበሩት የራያና ወልቃይት ለም መሬቶች ውጭ በራሷ ራሷን ችላ እንደአገር መቆም እንደማትችል ወያኔወች ጠንቅቃችሁ ታውቁታላችሁ፡፡ ስለሆነም ላይመለስ የከሸፈው ቅዠታችሁ የአማራ ለም መሬቶችን ሰርቆ ወይንም በጉልበት ከአማራው ነጥቆ መገንጠል ነበር፡፡ይህ ግን ሊሆን አልቻለም፡፤ወደፊትም ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም ለአመታት አያሌ ሰቅጣጭ ወንጀሎችና ከባድ የዘር ማጥፋት የተሰራበት የአማራ ጀግና ህዝብ የግፍ ጽዋው ሞልቶ የወያኔን የጦርነት እብሪት ገና በጧቱ ስላስተነፈሰው ነው፡፡ ስለሆነም ወያኔወች ሆይ፦ተወጣም ተወረደም ለታላቋ ትግራይ የቋመጣችሁለት የራያና የወልቃይት ለም የአማራ መሬትቶች ቅዠት ብቻ ሆኖባችሁ ለዘለአለም ሲያቃዣችሁ ይኖራል እንጅ ከእንግዲህ አታገኙትም፡፡ እርም ይሁንባችሁ፡፡መሬቶቹ ለህጋዊና ታሪካዊ ባለቤቶቻቸው ለአማራ ህዝብ በደም ዋጋ ተመልሰዋል፡፡ ከእንግድህ በኋላም በውጭ አገራት አደባባዮች በመንከባለልም፣ በማለቃቀስም፣ለውጭ አገራት ባለስልጣኖች ክስን በማቅረብም ፣ ከኢትዮጵያ ድሀ ህዝብ የተዘረፈ ዶላርን በመንዛትም… ወዘተ የሚመጣ ቅንጣት ለውጥ የለም፡፡ አማራው በተረኛው ኦሮሙማ ሴራ የአርበኝነት ተጋድሎው ለጊዜው ክፉኛ እየተሰናከለበት ቢሆንም ያን ሁሉ ችሎ፣ አስተንትኖ፣ በስሌት በመጓዝና በረዥሙ በማቀድ ጀግንነቱን ካልካዳችሁ በስተቀር ጠንቅቃችሁ በምታውቁት ነፍጠኛነቱ እስከመጨረሻውና አስተማማኝ ድል ማድረጉ ድረስ ገና ይገርፋችኋል፡፡ ድርድርም በሉት የኢኮኖሚ ማእቀብና ሌላ ሌላም ማስፈራሪያና ሰበብ እንደዚሁም ማንም ሀይል በምንም መንገድ እነዚህን መሬቶች ከአማራው ይዞታነት ወደ ትግራይ ሊያስመልሳችሁ ፈጽሞ አይችልም፡፡የዘለአለም ቅዠት ሆኖባችሁ ይቀራል፡፡
ስለወያኔ ምቀኝነት፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ማን ነው? (ግርማ ሠይፉ ማሩ)

እዚህ ላይ ማለት የሚቻለው አጭር ነገርን ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም ምቀኝነት እንደቅዠት በሀሳብ ሳይሆን በተግባር ይገለጣልና፡፡ ወያኔ የወልቃይትና የራያ ለም የአማራ መሬቶች ተቀባይነት ከሌላቸው ትርኪ ምርኪ የተደረቱ ትረካወቹና ልብወለዶቹ ሌላ የትግራይ ናቸው ብሎ ለመከራከሪያነት የሚጠቅሰው የቦታወቹን ስሞችን ነው፡፤ ምሳሌ፦አማራ ማይጸብሪን ማይጠብሪ ብሎ ሰየመ፣ ጸገደን ጠገደ ብሎ ስሙን ቀየረ፣ ጸለምትን ጠለምት ብሎ ታሪካዊ የትግርኛ ስሙን ቀይሯል ነው የሚሉት፡፡ እነርሱስ የእነዚህን ቦታወች የአማርኛ ስማቸውን ወደትግርኛ ቀይረዉት ከሆነስ??

በኦሮሙማ የተረኝነት ሴራና የፖለቲካ ቁማር አማካይነት ስሌቱ ለጊዜው ተሳክቶና ወያኔወች በለስ ቀንቷቸው በአማራው ላይ ወደርየለሽ ጥቃትና ወረራ እየፈጸሙ ይገኛሉ፡፡ በወረሯቸው አያሌ የአማራ ቦታወች ላይ ሰው ጫካ ገብቶ ሲያጡት ከብቱን ‘ፍጇቸው! የአማራ ከብቶች ናቸው’ እያሉ በመርዝና በጥይት የሚገድሉት ወያኔወች ከዚህ እንሰሳዊ ድርጊታቸው ውጭም በአማራ ላይ ወደርየለሽ ምቀኝነታቸውን የሚያሳይ ሌላ ጉደኛ ማሳያም አለ፡፡

እነርሱ እንደሚሉት ከሆነ አማራ በደሙ ዋዥቶና በቁጥጥሩ ውስጥ አድርጎ አሁን የሚያስተዳድራቸውን ወያኔ የኔ ናቸው የሚላቸውን ቦታወች ስም ማለትም የወልቃይት፣ ራያ፣ ሁማራ፣ ዳንሻ፣ ኮረም፣ አለማጣ፣ ቆቦ ወዘተ ቦታወችን ስም አማራው ከየትኛው የትግርኛ ስም ወደአማርኛ ቀየራቸው?? ምናልባትም እነዚህ ቦታወች የትግርኛ ስማቸው ይህ ይሆን ነበርን?? ወልቃይት – ወልቃይትጺ፣ ሁመራ – ሁመራጺ፣ ዳንሻ – ዳንሻጺ፣ ኮረም ኮረምጺ፣ አለማጣ – አለማጣጺ፣ ቆቦ ቆቦጺ ወዘተ ወይንም እናንተው አስተካክላችሁ ጨምሩበት፡፡ ታሪክም ሆነ የየቦታዎቹ ኗሪዎች(አማራውም ትግራዋዩም) እነዚህን ቦታወች የሚያውቋቸውና የሚጠሯቸው በየትኛው ስማቸው እንደሆነ ማንም ሳይሆን በቦታው ለሽህ አመታት የኖረው ህዝብ ቋሚ ምስክር ነው፡፡አይ ቅሌት!!! ሌላውን ሁሉ ተውት፡፡ እነዚህ ቦታወች በአማራ ስር ሲተዳደሩ የነበሩ ለመሆናቸው የዱሮው የትግራይ ገዥ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም ”እኔ ልጅ ሆኜ ሳድግም ሆነ በኋላ ትግራይን ሳስተዳድር ወልቃይት በትግራይ ስር አልነበረም’’ሲሉ እኤአ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓም በነጻ ህሊናቸው ለአሜሪካ ድምጽ ራዴዮ የሰጡትን ቃለ መጠይቅ በወያኔ ጫና ከ13 ወሮች በኋላ ማለትም ታህሳስ 5 ቀን 2018 በድምጸ ወያኔ ቴሌቪዥን እንዲቀርቡ ተደርጎ ቃላቸውን እንዲያጥፉ የተገደዱ ቢሆንም ይህንኑ ሚዛን አስገብቶ ማዳማጡ ይጠቅማል፡፡ እንደገናም “የትውልድ አደራ” በሚለው ልዑሉ ራሳቸው ቀድመው በጻፉት መጽሀፋቸው ገጽ 130 ላይ ያሰፈሩትን የጽሁፍ ምስክርነት ማንበቡ በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጉልበት ሳይገፋው ዳር እሚደርስ ተስፋ የለም! - በላይነህ አባተ

ለነገሩኮ ውርደት መገለጫቸው የሆነው ወያኔዎች ራስ ዳሽን ተራራን ወደ ትግራይ ክልል አካልለው ለትግራይ ት/ቤቶች መማሪያ መጽሀፍ ላይ አሳትመውት ነበር፡፤ ጣና ሀይቅስ የእነርሱ ይሆንን?? እነርሱን ወራዳውች ማለቱ ብቻ አይገልጻቸውምና የፈለጋችሁትን ስም እናንተው ስጧቸው፡፡ በእኔ በኩል እንዳለችው እንሰሳ “ምቀኞች” ብያቸዋለሁ፡፡

4 Comments

  1. Yes, you said right ! But what and how about the delusional, illusssional and criminal faction of EPRDF controlling the Arat Kilo Palace? Can’t you eye see and your mind observe the other face of cancerous political elites who have committed and continued committing a very serious political crime in the name of democratic change ? Sad!

  2. Tegenaw has raised an interesting issues.
    PM Abiy Ahmed seem to me he is playing dirty political cards. To let his OROMUMA conspired politics stay him in power, he is saying good things only as leap services but practically doing the opposite in action. That will bring more damage to the country and the life of entire people will be miserable. If he is not coming to his sense after the so called a new government is established, then his end will be too catastrophic!!!
    As per the wonderful Amharic Article above “” ወደር የለሹ የወያኔ ቅዠትና የምቀኝነት ጥግ””” by Dinku, I think much of it is well explained & more than that, all is true and the people know it very well. But one more thing must have been mentioned there. About the shameful Oromo Prosperity Party. Is it not worse than TPF??. In just 3 years, Abiy Ahmed’s prosperity OROMO party have doubled and tripled all sorts of crimes TPLF did 27 in years.

  3. ውድ ዘሀበሻወች፦
    መልክቴ አጭር ነው፡፡ እናንተ ጽሁፎችን ስታቀርቧቸው (POST ስታደርጓቸው) የምትሰሯቸው ትንንሽ ስህተቶች ጽሀፊው በላከላችሁ መልኩ ባለመውጣታቸው ይመስስለኛል የተዛባና ያልተሟላ መልእክትን ይዘው ይወጣሉ፡፤ ጽሁፉን POST ስታደርጉት የምትዘሏቸው ቃሎችም ሆኑ አረፍተ ነገሮች አልፎ አልፎ በመፈጠራቸው እነርሱም ጉድለቶችን ስለሚይዙ የጽሁፍም ሆነ የጸሀፊውን መልእክት እጀ ሰባራ ያደርገዋል፡፡
    ምሳሌ ልጥቀስላችሁ፡፡
    1ኛ) ይመስለኛል ማክሰኞ ጥቅምት 2 ቀን 2014 ዓም የዘሀበሻ አማርኛው ድረ ገጽ ላይ ዳግማዊ ጉዱ ካሳ የተባሉት ጸሀፊ “በአእምሮ ህሙማን የሚመራው የአቢይ ግራኝ አህመድ መንግሥት“ በሚል ርእስ በጻፉት ጽሁፍ መጨረሻ ላይ የሚለው (ከታች ያስቀመጥኩት) በአንድ መስመር ላይ ማለቅ ሲገባው በሁለት መስመር ላይ እንዲያልቅ በመደረጉ ጽሁፉን ቆም ብሎና ጊዜ ውስዶ ካላሰቡበት በተቀር ያልተሟላና ማሰሪያውንም የተበላሸ ያደርገዋል፡፡
    ብዙ ሰዎችን እንዳ
    እንዳተፈለፈለ እንቁላል አገማብን፡፡

    ዳግማዊ ጉዱ ካሳ የላኩላችሁን ጽሁፍ መልሳችሁ በጥንቃቄ ብታዩት እንደዚህ ሆኖ ስሜት በማይሰጥ መልኩ እንዳልተቀመጠ ትረዳላችሁ፡፡ ጽሁፉ ወደ እናንተ ተልኮ ሊሆን የሚችለው እንደሚከተለው ይመስለኛል፡፡ መልሳችሁ እዩት፡፡

    ብዙ ሰዎችን እንደተፈለፈለ እንቁላል አገማብን፡፡

    ———————————————————————————————-

    2ኛ) አሁንም ቀኑ ይመስለኛል ማክሰኞ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓም የዘሀበሻ አማርኛው ድረ ገጽ ላይ አቶ ድንቁ ሞላ የተባሉት ጸሀፊ ‘ወደርየለሹ የወያኔ ቅዠትና የምቀኝነት ጥግ” በሚል ርእስ ባቀረቡት ጽሁፍ መዝጊያው ላይ POST ስታደርጉ የዘለላችሁት (ከታች ያስቀመጥኩት) የሚመስል ነገር አለው፡፡ ይህም የጽሁፉን ጉድለት በቀላሉ ያመላክታል፡፡
    በእኔ በኩል እንዳለችው እንሰሳ “ምቀኞች “ ብያቸዋለሁ፡፡
    አቶ ድንቁ የላኩላችሁን ጽሁፍ መልሳችሁ በጥንቃቄ ብታዩት እንደዚህ ሆኖ ስሜት በማይሰጥ መልኩ እንዳልተቀመጠ ትረዳላችሁ፡፡ ጽሁፉ ወደ እናንተ ተልኮ ሊሆን የሚችለው እንደሚከተለው ይመስላል፡፡ መልሳችሁ እዩት፡፡
    በእኔ በኩል እንዳለችው እንሰሳ “ምቀኞች “ ብያቸዋለሁ፡፡

    ውድ ዘሀበሻወች ሆይ፦
    ይህ አስተያየቴ ዘሀበሻ ቤታችን ስለሆነ ለበለጠ ተደራሽነቱ ይረዳል በሚል ንጹህ ስሜት ብቻ መሆኑን እወቁልኝ፡፡ በዚህ መጥፎና ፈታኝ ወቅት ለእምዬ ኢትዮጵያና በተለይም በውጭ አገራት ለምንገኘው የእኔ አይነቱ የተሟላች አንዲት ኢትዮጵያን ለማየት ናፋቂ የሆነ ኢትዮጵያዊ ምትክ የለሾች ናችሁና በርቱልን!!

  4. ውድ ዘሀበሻወች፦
    መልክቴ አጭር ነው፡፡ እናንተ ጽሁፎችን ስታቀርቧቸው (POST ስታደርጓቸው) የምትሰሯቸው ትንንሽ ስህተቶች ጽሀፊው በላከላችሁ መልኩ ባለመውጣታቸው ይመስስለኛል የተዛባና ያልተሟላ መልእክትን ይዘው ይወጣሉ፡፤ ጽሁፉን POST ስታደርጉት የምትዘሏቸው ቃሎችም ሆኑ አረፍተ ነገሮች አልፎ አልፎ በመፈጠራቸው እነርሱም ጉድለቶችን ስለሚይዙ የጽሁፍም ሆነ የጸሀፊውን መልእክት እጀ ሰባራ ያደርገዋል፡፡

    ምሳሌ ልጥቀስላችሁ፡፡
    1ኛ) ይመስለኛል ማክሰኞ ጥቅምት 2 ቀን 2014 ዓም የዘሀበሻ አማርኛው ድረ ገጽ ላይ ዳግማዊ ጉዱ ካሳ የተባሉት ጸሀፊ “በአእምሮ ህሙማን የሚመራው የአቢይ ግራኝ አህመድ መንግሥት“ በሚል ርእስ በጻፉት ጽሁፍ መጨረሻ ላይ የሚለው (ከታች ያስቀመጥኩት) በአንድ መስመር ላይ ማለቅ ሲገባው በሁለት መስመር ላይ እንዲያልቅ በመደረጉ ጽሁፉን ቆም ብሎና ጊዜ ውስዶ ካላሰቡበት በተቀር ያልተሟላና ማሰሪያውንም የተበላሸ ያደርገዋል፡፡

    ብዙ ሰዎችን እንዳ
    እንዳተፈለፈለ እንቁላል አገማብን፡፡

    ዳግማዊ ጉዱ ካሳ የላኩላችሁን ጽሁፍ መልሳችሁ በጥንቃቄ ብታዩት እንደዚህ ሆኖ ስሜት በማይሰጥ መልኩ እንዳልተቀመጠ ትረዳላችሁ፡፡ ጽሁፉ ወደ እናንተ ተልኮ ሊሆን የሚችለው እንደሚከተለው ይመስለናል፡፡ መልሳችሁ እዩት፡፡

    ብዙ ሰዎችን እንደተፈለፈለ እንቁላል አገማብን፡፡

    2ኛ) አሁንም ቀኑ ይመስለኛል ማክሰኞ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓም የዘሀበሻ አማርኛው ድረ ገጽ ላይ አቶ ድንቁ ሞላ የተባሉት ጸሀፊ ‘ወደርየለሹ የወያኔ ቅዠትና የምቀኝነት ጥግ” በሚል ርእስ ባቀረቡት ጽሁፍ አሁንም መዝጊያው ላይ POST ስታደርጉ የዘለላችሁት የሚመስል ነገር አለው፡፡ ይህም የጽሁፉን ጉድለት በቀላሉ ያመላክታል፡፡

    በእኔ በኩል እንዳለችው እንሰሳ “ምቀኞች “ ብያቸዋለሁ፡፡

    አቶ ድንቁ የላኩላችሁን ጽሁፍ መልሳችሁ በጥንቃቄ ብታዩት እንደዚህ ሆኖ ስሜት በማይሰጥ መልኩ እንዳልተቀመጠ ትረዳላችሁ፡፡ ጽሁፉ ወደ እናንተ ተልኮ ሊሆን የሚችለው እንደሚከተለው ይመስላል፡፡ መልሳችሁ እዩት፡፡

    በእኔ በኩል እንዳለችው እንሰሳ “ምቀኞች “ ብያቸዋለሁ፡፡

    ውድ ዘሀበሻወች ሆይ፦
    ይህ አስተያየት ስለምወዳችሁና ስለማከብራችሁ ዘሀበሻም ቤታችን ስለሆነ ለበለጠ ተደራሽነቱ ይረዳል በሚል ንጹህ ስሜት ብቻ መሆኑን ተረዱልኝ፡፡ በዚህ መጥፎና ፈታኝ ወቅት ለዕኛ ምትክ የለሾች ናችሁና በርቱልን!!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share