የአንዳርጋቸው አማራ የለምና የወያኔ ቤታማራን መቆጣጠር – መስፍን አረጋ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ‹‹የመከላከያን ጭራ እየተከተልክ ያሸነፍክ ሲመስልህ … ጀግናው ኃይላችን ትላለህ፣ ስትቀጠቀጥ ደግሞ መከላከያ የታለ ለኔ ወግኖ ሌላ ኢትዮጵያዊን ይውጋ ትላለህ›› በማለት ለአማራ ሕልውና የሞት ሽረት ትግል በሚያደርጉት በአማራ ኃይሎች ላይ ለመሳለቅ መሞከሩ ተዘግቧል፡፡

ለዚህ ትናንት የተናገረውን ዛሬ ለሚቃረን፣ ነገሮች ለተሳከሩበት፣ ያገር መከላከያ የሚቋቋመው ከሕዝብ ጋር ወግኖ ወንበዴን ለመውጋት እንደሆነ ላልተገነዘበ፣ ያነበበው ወይም የሰማው ሁሉ ከሚያስበው ጋር ከተገጣጠመለት ውነት ለሚመስለው፣ አላዋቂነቱ ደፋር ላደረገው መደዴ፣ በዚያ ላይ ደግሞ እጅግ ሲበዛ አለሁባይ (attention seeker) እንዲሁም የነጭ ሽብር አረመኔ ግለሰብ፣ የሚበጀው ንቆ መተው ነበር፡፡

ችግሩ ግን አገራችን እየተመራች ያለችው የአንዳርጋቸው የባሕሪ ወንድም የሆነ የስነልቦና በሽተኛ ግለሰብ፣ በዚያ ላይ ደግሞ አክራሪ ኦነጋዊ እንዲሆን በወያኔ ተጠፍጥፎ የተሠራ የወያኔ ሥሪት ወይም ቅጥቅጥ የሆነ ግለሰብ፣  አንዳርጋቸውና ኦነጋውያን ባረቀቁለት ፍኖትካርታ መሆኑ ነው፣ ግም ለግም አብረህ አዝግም እንዲሉ፡፡

በወያኔ ዘመን ያማራ ትግል ከየት ወደየት የሚል መጽሐፍ የጻፈው አንዳርጋቸው፣ በኦነግ ዘመን አማራ የሚባል ሕዝብ የለም የሚለው፣ አማራ የሚባል ሕዝብ መኖሩን ብቻ ሳይሆን ቁጥሩ ኦሮሞ ከሚባለው ሕዝብ በብዙ ሚሊዮኖች እንደሚበልጥ አሳምሮ ስለሚያወቅ ነው፡፡  አማራ የለም የሚለው ደግም ህልውናውን በአማራነት ላይ የመሠረተውን አብንን አጥፍቶ፣ ይህን የጦቢያን ሰፊ ሕዝብ በብቸኝነት ለመቆጣጠር ነው፡፡

አማራ የለም ለማለት የደፈረው ደግሞ የአማራን ሕዝብ ሆደሰፊነት ስለሚያውቀው ነው፡፡  አለበለዚያማ እንደሱ የኦሮሞ ስም ስለተለጠፈበት ብቻ ኦሮሞ ነኝ ከሚለው ሕዝብ ውስጥ ከዘጠና በመቶ በላይ ኦሮሞ ያልሆነ፣ ከዘር ጭፍጨፋ መልስ ጉዲፈቻ ወይም ሞጋሳ የተደረገ መሆኑ ጠፍቶት አይደለም፡፡  አሮሞ የሚባል የለም ወይም ደግሞ ቁጥሩ መናኛ የሆነ ሕዳጣን ነው ቢል ግን፣ ዐብይ አሕመድ የሚሰፍርለትን ቀለብ ወዲያውኑ አስቁሞ፣ እጅና እግሩን የፊጥኝ አሳስሮ፣ በጀርባው አንጋሎ፣ ዓይኖቹን እያቁለጨለጨና እያጉራራ እንደ በግ አሳርዶ፣ ሬሳውን መንገድ ለመንገድ አስገትቶ፣ በስተመጨረሻ ለውሻ እንደሚያስወረውረው አሳምሮ ያውቃል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፈጣሪ ፊቱን ወደ ሰው ይመለስ ዘንድ ፤ ሰው ሁሉ  ፤ በነገር ሁሉ ፣ እግዛብሔርን ማስቀደም አለበት - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

በዚህ ረገድ ደግሞ የአማራ ሕዝብ ሆደሰፊነቱን በልክ እንዲያደርገው ይመከራል፣ ማርም ሲበዛ ይመራልና፡፡   አንዳርጋቸውን የመሰሉ ጋጠወጦች አደብ የሚገዙት የጋጣችሁትን ወጥ ውስጥ አትመልሱ በመባል ሳይሆን፣ ብትመልሱ ወዮላችሁ በመባል ብቻ ነው፡፡  የተዋሕዶ መዕምንም ስለሐይማኖት ቀናዒነትን ከሙስሊም ወንድሞቹ ሊማር ይገባዋል፣ ነቀፋና ዘለፋ እየቅል ናቸውና፡፡

አንዳርጋቸውና ባልደረቦቹ ኢሕአፔወች መሆናቸውንና፣ ባብዛኞቹ ኢሕአፔወች ዘንድ ደግሞ ወደ ስልጣን የሚያመራ እስከሆነ ድረስ የማይኬድበት መንገድ እንደሌለ ከዘነጋን ጥፋቱ የኛው የራሳችን ነው፡፡  ለስልጣን ሲባል የገዛ ቤተሰብን መግደል፣ ምሁራንን መረሸን፣ ወጣቶችን ማስጨፍጨፍ፣ ሕጻናትን መማገድ፣ ዓላማን የሚያሳካ የውሸት ትርክት መተርከት፣ አገር ማስገንጠል፣ ካገር ጠላት ጋር መመሳጠርና መተባበር፣ በጀርባ መውጋት፣ በማጅራት ማረድ በኢሕአፔወች ዘንድ የተፈቀዱ ብቻ ሳይሆኑ ግዴታወችም ናቸው፡፡

ስለዚህም በአፋር ግንባር የትም እንዳይራመድ የተደረገው ወያኔ፣ የአማራነት እምብርት የሆኑትን ቦታወቸው ባጭር ጊዜ ውስጥ እንዲቆጣጠርና የአማራነት አሻራቸውን እንዲያወድማቸው በአብይ አሕመድ የተመቻቸለት፣ አንዳርጋቸውና ባልደረቦቹ በሚለግሱት ምክር ባይሆን እንጅ ቢሆን አያስገርምም፡፡

ኦነጋውያነን በኦነግነታቸው፣ ወያኔወች በወያኔነታቸው፣ አንዳርጋቸውና መሰሎቹ ደግሞ በስልጣን ጥማታቸው ምክኒያት የአማራን ሕዝብ እስትንፋስ አሳጥተውታል፡፡  ስለዚህም፣ የአማራ ሕዝብ ለህልውናው ሲል መውሰድ ያለበትን ርምጃወች ሁሉ ያለ ምንም ማመንታት ባስቸኳይ መውሰድ አለበት፣ ከራስ በላይ ንፋስ ነውና፡፡

አብናቶቻችን (አባቶቻችንና እናቶቻችን) እንደሚሉት እየየም ሲደላ ነው፡፡  ስለ ሰብኣዊ መብት ከኔ ወዲያ ላሳር የምትለው አሜሪቃ፣ ከጃፓን ጋር የሞት ሽረት ትግል በምታደርግበት ጊዜ፣ የገዛ ዜጎቿን የጃፓን ደም ስላላቸው ብቻ ለጃፓን ያደሉ ይሆናል በሚል ጥርጣሬ ብቻ፣ ሴት፣ ወንድ፣ ልጅ፣ አዋቂ፣ ጨቅላ፣ አረጋዊ ሳትል ልቅምቅም አድርጋ፣ ሐብትና ንብረታቸውን ሞልጫ፣ ጦርነቱ እስከሚያልቅ ድረስ ሰብጉረኖ (concentration camp) ውስጥ አጉራቸው ነበር፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰባተኛው ንጉሥ ጉድ አፈላ! - ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

የአማራ ሕዝብ ለሕልውናው እየተዋደቀበት ባለበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፣ አማራ የለም በማለት የአማራ ጠላትነታቸውን በይፋ ያወጁት፣ የኦሮምያና የቤንሻንጉል አማራወችን መጤ በማለት በአማራነታቸው ብቻ ሲጨፈጨፉ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጣ የተከላከሉት፣ ከቀንደኛው ኦነጋዊ ከዐብይ አሕመድ ጋር በመቆም የኦነገን ዓላማ በቀጠታም ሆነ በተዛዋሪ የሚያራምዱት አንዳርጋቸውና ባልደረቦቹ፣ ጦርነቱ እስከሚያልቅ ድረስ ቢቻል ተሰብስበው መታጎር፣ ባይቻል ደግሞ ወደ አማራ ክልል ዝር እንዳይሉ መደረግ አለባቸው፡፡  ሌላው ቢቀር ግን ተፈናቃይ በመጎብኘትና በመሳሰሉት ሰበቦች ከአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻ ወይም ፋኖ አጠገብ ድርሽ ማለት የለባቸውም፡፡  በተለይም ደግሞ ዜና በመስጠትና በመሳሰሉት ሰበቦች ካንዳርጋቸው ጽጌ ሚዲያወች (ኢሳት፣ ዜና ቲዩብ …) ጋር የሚገናኝ ማናቸወም የአማራ ጦር አመራር፣ ከጠላት ጋር እንደተገናኘ ተቆጥሮ አስፈላጊው እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል፡፡   አለበለዚያ አንዳርጋቸውና ግብራበሮቹ በሱማሌ ወረራ ጊዜ በኢትዮጵያ ጦር ላይ የፈጸሙትን ወንጀል፣ በአማራ ኃይል ላይ እንዲደግሙት መፍቀድ ነው፡፡

የአማራ ጸር የሆነው ወያኔ፣ የአማራ እምብርት የሆነውን ቤታማራን በቀላሉ መቆጣጠሩና የአማራን ሕዝብ እንደ ሕዝብ በገፍ መጨፍጨፉ፣ አማራ የለም ብሎ አፉን ሞልቶ በድፍረት ከተናገረው ከአንዳርጋቸው ጽጌና ከባልደረቦቹ በላይ ማንን ሊያስደስት ይችላል?

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

10 Comments

  1. ውድ ዘሃበሻ አታሚ፣
    ፕሮፌሰር መስፍን አረጋ የሚጽፋቸውን ዘረኛ እና ሴትነትን የሚያጎድፍ ጽሑፎችን ማተማችሁ መብቱ እና መብታችሁ እንደ ሆነ አስባችሁ ይሆናል። የምትለጥፏቸው ጽሑፎች ግን ጥላቻን የሚያስፋፉ፣ ስብእናን የሚያቋሽሹ ከሆነ ተባባሪ ከመሆን አታመልጡም። በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት የተነሳ መቆራቆስ ይኖራል፤ ያለመረጃ ሲሆን ግ ን ስም ማጥፋት ነው፤ ዘሃበሻ ለዚህ ዓይነት ተቋቋመ የምትሉ አይመስለኝም።

    ከዚህ ቀደም እንዳልኩት፣ ፕሮፌሰር መስፍን የአገሩ ልጅ ጄኔራል አሳምነው ጽጌ መገደሉን አስመልክቶ ትልቅ ጥላቻና ቂም በዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ላይ ይዟል። አሳምነው የተገደለው አገር ለማመስ ሥልጣን ላይ ለመውጣት ሲታገል በተደረገው የተኲስ ልውውጥ ነው። ይኸ አማራነትን ወይም ኦሮምነትን አይለይም፤ ጃዋር መሃመድ፣ እስክንድር ነጋ እስር ቤት ገብተዋል። የህወሓት መሪዎች ታሥረዋል፤ ተወግደዋል። እነዚህን ሁሉ ሕዝብ አንቅሮ ተፍቶአቸዋል።

    ፕሮፌሰር መስፍን አረጋ ፊዚክስ በሚያስተምርበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ስለ ሴቶች እና ስለ ዘር ያለው አመለካከት ይፋ ቢወጣ አንድ ቀን አይሰነብታትም። ይህን የሚያጣው አይመስለኝም። ለዚህም ነው ይህን ጨለምተኛነቱን በአማርኛ የሚሞነጫጭረው። ለነገሩ ለሚመለከታቸው ክፍሎች ትርጒሙን መላክ ይቻላልና ራሱን ሠውሮ አይዘልቅም። ለምሳሌ፣ ስለ ዶ/ር ዐቢይ እንዲህ ጽፏል፦ “እናቱን አለመጠን የሚያሞግሰው ዐብይ አህመድ በናቱ ምንነት አለመጥን ስለሚያፍር ይሆናል፡፡ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የብቸነት ኑሮ ትገፋ የነበረቸውን እማወራ (single mother) ሚስቱን አለመጠን የሚክባት ደግሞ በጓዳ የሚያዋርዳት የቤት ቀጋ የውጭ አልጋ ስለሆነ ይሆናል።” (“ግልጽ ደብዳቤ በዐብይ አሕመድ ላይ ተስፋችሁ ላልተሟጠጠ አማሮች”፣ ዘሃበሻ፣ ኦገስት 24/2021)

    ይህን ከላይ የተጠቀሰውን የሚያነብብ ማንኛውም ኅሊና ያለው ኢትዮጵያዊ ነውር ብቻ ሳይሆን ከመስመር የወጣ እንደ ሆነ ማስተዋል አያዳግተውም። ሴት ብቻዋን ታግላ ልጅ ማሳደጓ ይህን ያህል ያሰድባል? ሴቶችን ማዋረድ ተገቢ ነው?

    ዛሬ ደግሞ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማዋረድ ላይ ተሠማርቷል። ሶቅራጢስ ያለውን ላስማማና፣ ጤናማ አእምሮ አሳቦችን ይወያያል፤ ተራ አእምሮ የመንደር ወሬ፣ ታማሚ አእምሮ የሰውን ስብእናን ማጒደፍን።

  2. አለም የሚያሳዝነው ያንተን comment ማውጣታቸው እንጅ ከአለምስ ብዙ ተምረን ነበር።

  3. ከፕሮፌሰር መስፍን አረጋ ማለቴ ነው ይቅርታ በሌለህበት አስተማሪ አደረግሁህ ስለ ድፍረቴ ይቅርታ

  4. አይ አለም አንዳርጋቸውን ተከላከልኩ ብለሽ መከራ ውስጥ ልትጨምሪው ነው። አንዳርጋቸው ምን ብትሸፍኝለት መጽሀፍ ጽፏል በአደባባይ ደስኩሯል ብዙ ስህተት ተነቅሶበታል። ረስተሽው ከሆነ አንዳርካቸው ሎንዶን በየወያኔ የስብሰባ አዳራሽ ወምበር ሲደረድር ስብሰባ ሲጠራ ከርሞ አ.አ ሲገቡ ላደረገው አስተዋጽኦ በምጀመሪያ የፕሮፓጋንዳ ሀላፊ ተደርጎ ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ ለወያኔ አገልግሎቱ ከንቲባ አድርገው ሹመውት ኢትዮጵያን አሁን የገባችበትን ቅርቃር ህገመንግስት አጠናክሮላቸው በቃህ ተብሎ ከእፍኝ ብር ጋር የተሸኘ ከዘመን ዘመን ክጓደኛው ብርሀኑ ጋር ከገምቢ ሀሳብ ይልቅ ጥፋትን ሲተገብር የኖረ ሊለወጥ የማይችል ችሎታ የሌለው ተረት እያወራ ልዩነትን መተዳደሪያው ያደረገ ዜጋ ነው።
    የክፋትሽ ልክ እኛ የምናውቀውን ሀቅ ፕሮፌሰሩ ስለዘገበ ምተዳደሪያው ላይ ያነጣጠረ ማስፈራሪያ ሰንዝረሻል ይህ የመጀመሪያችሁ አይደለም ኢሳት በተባለው ድርጅታችሁ ሐይሌ ላሬቦንም እንዲሁ ልታሸማቅቁት ሞክራችሁ ነበር የወገን ጦር ባደረገው ርብርብ የጠላት ጦር አልቷል እው
    ቀት ላይ ያልተመሰረት ሙግት ስለምትገጥሙ አማራጫችሁ ተንኮል ነው። ብዙ ማለት ይቻል ነበር እስቲ በዚህ እንለፈው።

  5. የአንዳርጋቸው ጽጌ ትክክለኛ ሰብ|ዕና የተገለጸበት ጽሁፍ ነው
    ይህ ግለሰብ ኢትዮጵየ ለሱ መኑም አይደለችም ያ እሪ ብሎ
    ታግሎ ያስፈታወ ህዝብም ለሱ ጉደዩ አይደለም ምክንያቱመ
    እሱ ከኢተዮጵያዊነት አንግሊዛዊነት በልጦበት በዚያ የጸና
    ስለሆነ በሰው ሀገር ፖቲካ ምን አግብቶት ነው
    የሚፈተፍተው??መስፍን አረጋ ምንም ያጠፉት ነገር የለም
    አንደውም ይህን ርካሽ ግለሰብ መግለጽ ካለባቸው በታች
    ቁጥብ ሆነዋል፡፡ አሁንም አንዳርጋቸው ጽጌ ከኢትዮጵያ ጉዳይ
    እጁን ይሰብስበ፡፡

  6. ነገር ማምታት የሃበሻው ዋንኛ የፓለቲካ ስልት ነው። አንዳርጋቸው ጽጌ አማራ የሚባል ህዝብ የለም አላለም። አማራ የሚባል ነገድ የለም። ከሁሉ የተደባለቀ በሃገሩ ጉዳይ የማይደራደር በእምነቱ የጸና ህዝብ እንጂ። አማራን ቅይጥና በራሱ የቆመ ቀደምት ህዝብ ነው ማለት አማራ የሚባል ህዝብ አልነበረም ወይም የለም ማለቱ አይደለም፡፡ የሄደ የመጣው በገዢ መደብ ስምና የጨቆና ቀበር የጫነባችሁ አማራ ነው እየተባለ ሳይወድ በግድ በዘሩ ተሰላፊ የሆነ ህዝብ ነው ማለቱ የዚህን ህዝብ ያለፈና የአሁን ሰቆቃና ትግል ያመላክታል እንጂ እናንተ እንደምትሉት አማራ የሚባል ህዝብ አልነበረም ወይም የለም አላለም።
    ግን አሁን ባለው አስረሽ ምቺው የፓለቲካ ጭቃ ባገኙት ላይ ጭቃውን መለጠፍ የዜና ማሟያ በመሆኑ የአንዳርጋቸው ጽጌ ዘራዊ የሆነ የፓለቲካ መደብና አስተላለፍን መጸየፍ ህሳቤውንና ሰዋዊነቱ ጥላሸት እንዲቀባ ምክንያት ሆኗል። ክወያኔ እስር ቤት ሲፈታ በሆታ የተቀበሉት ሁሉ አሁን በስማ በለው በሚነዛ ወሬ አይንህ ላፈር ማለታቸው የቱን ያህል የፓለቲካው ጎስቋላ አካሎች እንደሆኑ ያመላክታል። እንዲህ ያለው ግትር አስተሳሰብና ያለ መረጃ ሰውን መኮነን ነው ከከተማ ቡጢ ጦር እስከ መማዘዝ የሚያደርሰን። አንዳርጋቸው ጽጌ ከኢትዮጵያ ጉዳይ እጅን ይሰብስብ ማለት እኔ ብቻ አውቃለሁ ማለት ነው። በመሰረቱ ፓለቲካ ንፋስ ነው። ሲፈልግ አቅጣጫ የሚለውጥ ያገኘውን አግበስብሶ የሚሄድ አውሎ ነፋስ፡፡ ለዚህ ዋና ማስረጃው ከ 20 ዓመት ፍልሚያ በህዋላ እግሬ አውጪኝ በማለት ከአፍጋኒስታን የፈረጠጠው የአሜሪካ መንግስት የፓለቲካ ውሳኔ ዋንኛ ማሳያ ነው። የቦንቦች ሁሉ የበላይ (The GBU-43/B Massive Ordnance Air Blast) የተባለውን ወደ 9800 ኪ. ግራም የሚመዝነውን ቦንብ በአፍጋን አማጽያን ላይ ያዘነበው የአሜሪካ የግጭት ፓሊሲ የበተነውን ሳይሰበስብ እንዲፈረጥጥ ሆኗል። የፓለቲካ መሪዎች ድንፋታ ኪሳራ የሚያስከትለው በሚወረረው ሃገር ላይና ለሃገርህ ነው እየተባለ በሚላከው ምስኪን ወታደርና ቤተሰብ ነው። እንሆ ያ ሁሉ የ 20 ዓመት ፍትጊያ በስላቅና በሩጫ የራሱን ዜጎች እንኳን በሙሉ ሳያስወጣ አፍጋኒስታንን ጥሎ ወቷል፡፤ የሃበሻው ፓለቲካም ባለህበት ሂድ ነው። ድልድይ የማይሻገር ፓለቲካ። አፍርሶ ፈረሰብኝ የሚል እኩይ ስብስብ የሚነዳው ፓለቲካ። በእውነት አሁን ወያኔ በአፋርና በአማራ ህዝብ ላይ ያደረሰውን መከራ ያየ ተመልሶ አብሮ ከወያኔና ደጋፊዎቻቸው ጋር መኖር ይችላል? በጭራሽ! ለዚህ ነው ወያኔ መብረቃዊ ጥቃት ሳይሆን የፈጸመው ምትሃታዊ ነው የምለው። ተበተኑ ተደቆሱ፤ ተደመሰሱ፤ የተባሉት እነዚያ ሽንኮች ታንክ፤ አየር መቃወሚያ፤ መድፍ ይዘው አፋርና ደብረ ታቦር እስኪደርሱ ለምን ዝም ተባሉ? አጥንት ያለው እንዲህ ያለ የፓለቲካ ጥያቄ እንደመጠየቅ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲህ አለ ፕ/እከሌ እንዲያ አለ ማለት ገልቱነት ነው። እኔ አንዳርጋቸው ጽጌን አላውቀውም። ግን ወያኔን ለመፋለም የሚችለውን ያበረከተና በግፍ የታሰረ ወገን ነው። ያን ሰው አሁን በእርጅና ዘመኑ መጎንተል የቀን ጅብ መሆን ነው። ተውት እንዳሻው ይራመድ። በቃኝ!

    • ተስፋ ነብስህ ተሰቃየች ለጻፈው ሁሉ መልስ ጽፈህ እንዴት ትችለዋለህ? አንዳርጋቸውን ከኔ በላይ የሚያውቀው የለም አስተያየት ምን ማለት ነው? የአንዳርጋቸውን ጽሁፍና ዲስኩር ከኔ በላይ የተረዳ የለም አካሄድ መልካም አይመስለኝም። እንግዲህ በስናይፐር ተኳሽነት ሳይበር ላይ አስቀምጠውህ ከሆነ ስራ ነው ምን ይደረጋል።

      እስቲ ስለ አንዳርጋቸው አያት ምንሊክ 20000 ቀንድ ከብት ሰሰረቁባቸው የነገረህ ነገር ካለ ጀባ በለን ስማቸው ቡኒ ይባላል በተረፈ በገረደፈ እይታህ ሰውን አትሞልጨው።

  7. ቢረጋ፣ ነቢዩ፣ ከበቡሽ፣ ብርሌ፣
    ዲባቶ መስፍን “ዛሬ ደግሞ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማዋረድ ላይ ተሠማርቷል” ያልኩትን ለአቶ አንዳርጋቸው ድጋፍ አስመሰላችሁት! የአቶ አንዳርጋቸው (ግንቦት 7) ደጋፊ ሆኜ አላውቅም፤ አልሆንምም!

    አንብባችሁ መረዳት ትንሽ ይከብዳችሁ ካልሆነ በስተቀር፣ መልእክቴ ያተኮረው በመስፍን አረጋ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ነው። ዐቢይ አሕመድ ይህን አደረገ፣ ይህን ሆነ፣ ወዘተ። ከዚያ ደግሞ አንዳርጋቸው … ይልቅ ማደነጋገር ትታችሁ ባነሳሁት ነጥብ ላይ ምላሽ ስጡ።

  8. አለም መስፍን አረጋ የጻፈው ስለ አንዳርጋቸው ነው የጻፈውም ስለምናውቀው ጉዳይ ነው እንግዲህ የጽሁፉ የስበት ማእከል አንዳርጋቸው ሁኖ ሳለ የእኔ ጥል ከመስፍን ነው ካልሽ የግል ጉዳይ ያላችሁ ስለሚመስልና በመሀከላችሁ ያለውን ስላልተረዳሁ ጥጌን ይዣለሁ። በተረፈ እየመረጣችሁ መልካም ኢትዮጵያውያንን ለማሸማቀቅ ጥግ ይዘሽ የምትተኩሽና የምታስተኩሽ ከሆነ ውርድ ከራስ ብያለሀ። እስቲ ባዲስ አመት ያሰብሽውን ይሙላልሽ። የሰው ችግሩ ብዙ ነው አሁን ኢትዮጵያዊ ነኝ ያለሰው ለአንዳርጋቸው ጥብቅና ይቆማል?

  9. አለም ጉዳይሽ ምንድነው የፊዚክሱን ሊቅ አጣጥለሽ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎችን ሀሳብ አጣጥለሽ እንዴት ይቻላል። ፕሮፌሰሩ እንዳንች ባያውቅም የአንዳርጋቸውን ደካማ ሀሳብ ብትኖ አሳየን። የአንዳርጋቸውና መሰሎቻቸው ደካማ ሀሳብ ሲተነተን የሀሳቡ አመንጭዎች ለማጣቀሻነት መነሳታቸው ግድ ነው። ስለአረጋዊ በርሄ የጥፋት ስራዎች ስሙን ካልጠቀስኩ አስተያየቴን የተሟላ አያደርገውም። ይህንንም ስም ማጥፋት እንዳትይው።
    እንዲህ አይነት የስብጥር ተኩስ እየከፈታችሁ መልካም
    ኢትዮጵያውያንን ከመድረኩ እያገለላችሁ መድረኩን በነ አንዳርጋቸው ሞልተችሁታል። ይመቻችሁ የኢትዮጵያ መፍረስ ለናንተ ጠቀሜታ ካለው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share