ፍፁም ሰዎች በሌሉበት ምድር : መሪን ፍፁም ሁን ማለት ተገቢ አይደለም (በአልማዝ አሰፋ – ዘረ ሰው)

እኔ በደርግም : በኢህአደግም ሆነ በብልፅግና አስተዳደር ስር ያልኖርኩና የማልኖር: ከዲያስፖራ ሆኜ ከአገርና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፍቅር የተነሳ የታዘብኩትንና የምትታዘበውን በእስተያየት መልክ ማቅረቤ ተገንዛቢ ይሁን:: ያለውን መንግስትና መሪውን ሳሞግሰው በጭፍንነት ሳይሆን : በሶስት አመት ውስጥ ያሳየው አጥጋቢ ስራዎች ላይ ተንተርኩዤና ከበፊቶቹ መሪዎች ጋር በማወዳደር ነው:: ሕይወት ፍፁም ሳትሆን ውጣ ውረድ የሞላባት የጉዞ ሂደት መሆኗን ከተገነዘብን አንዱ ከሌላ መሻሉን ወይም መክፋቱን የምናውቀው በአንፃራዊ ሚዛን ነው:: ትዝብታችን: ድጋፋችን : ቅዋሜያችን ስሜታዊ ሳይሆን ነግሮችን ምክንያታዊ አድርገን ስናቀርብ መግባባትንና መስማማትን እናዳብራለን:: በጭፍንነት ጥላቻ መነዳት ለአገርም : ለሕዝብም ከሚያመጣው ጥቅም ጉዳቱ ይበልጣል:: ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ምንድነው የሚጠቅመው : ምንድነው የሚጎዳው የሚሉትን ጥያቄዎች ሰከን ብለን ራሳችንን መጠየቅ ያስፈልጋል:: ጎሳና ነገድ ዝቅተኛ የሰው ልጆች መግለጫዎች ናቸው:: መጀመሪያ ሁላችንም ሰዎች መሆናችንን ልብ እናድርግ::

 

በተጨባጭነት የሚታይ የለውጥና የብልፅግና ጉዞ ኢትዮጵያ መራመድ የጀመረችበትን ያለፉትን ሶስት አመታት ትተን ከዚያ በፊት ያሳለፈችውን 45 አመታት ስንመለከት : የተወሰነ ልማትና እድገት ቢታይባትም : ሕዝብ በነፃ ሃሳቡን የማይገልፅበት : ተወዳዳሪ የፖለቲካ ድርጅቶች መዋቀር ያልቻሉበት : ጋዜጠኞች ትዝብታቸውን የማይፅፉበት : የፖለቲካ ተንታኞች ከገዢው መንግስት ድጋፍ ውጭ ሂስ የማያቀርቡበት: ጭቆናና ድህነት በዝቶበት ትንሹም ትልቁም አገር ለቆ ነፃነትንና ብልፅግና ፍለጋ በበረሓ በባህር የተሰደደበትና በዚያ ሂደት ሽዎች እህቶቻችንና ወንድሞቻችን በየሜዳው ወድቀው : በባህር ተውጠው ያለቁበት ዘመን ነበር:: እነዚህን የጥቂቶች ባለስልጣኖችና ባለጊዜዎች ምቾት ማራመጃ : የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የመከራና የእስረኝነት 45 አመታት : ካለፉት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተስፋ ጮራ ካበሩት 3 አመታት ጋር ስናወዳድር ልዩነታቸው የጨለማና የብርሃን ነው::

 

ያለፉት ሶስት አመታት ያሳዩን ጥሩም ሆነ መጥፎ ድርጊቶች የሚፈፀሙት በሰዎችና በፍላጎታቸው እንደሆነ ነው:: ሰዎች ልባቸውን በሰው ፍቅር ከሞሉት : ድርጊታቸውም በፍቅርና በእርህራሄ የተሞላ በመሆን ለመላው የአገር ሕዝብ ጠቃሚ ውጤት ያመጣል:: እያንዳንዱ የማህበረሰብ አባል ለእራሱ የሚመኘውን በንፁህ ልቦና ለሌላው ከተመኘ አካባቢውም ሆነ አገር የሰላምና የእንድነት ምሳሌ መሆን ትችላለች:: እንደ እኔ ቢሆን በአለም ውስጥ ድንበርና አገሮች ባልኖሩ ነበር:: እግዚአብሔር ይህችን ምድር የሰዎችና የሌላ ፍጡሮች መኖሪያ አድርጎ እንደፈጠራት: ሰዎችም እንደልባችን ያለመታወቂያና ያለፓስፖርት ከቦታ ቦታ እየተዘዋወርን በነፃነትና በሰላም እንደፈለግነው በኖርን ነበር:: ይህ የእኔ ምኞት ተምኔታዊ አመለካከት ነው:: አይሆንም:: ምክንያቱም ሰዎች ፍፁምነት ስላልተካንን የተንኮልና የሻጥር ምንጮች በመሆናችን ተማምነንና ተሳስበን የመኖር ችሎታችንን ከማዳበር ይልቅ ራስወዳድነትንና መተኖካከስን ስላጎለበትን ነው::

 

የምንኖርበት አለም በድንበር የተከለሉ አገሮች የተደራጁባት ነች:: እያንዳንዱ አገር የእራሱ አስተዳደር ስላለው ከድንበር ውጭ ያለው ጎረቤት ወይም ከሩቅ አገር የመጣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት መብት የለውም:: ከገባም የሚደርስበትን ጥቃት ሳንገነዘብ አልቀረንም:: ከአገሪቱ ተወላጆች መሃል የሚወጡት መሪዎች ለዚያች አገር የወደፊት እድገት : ልማት : ብልፅግና : ሰላም : አንድነትና ሉአላዊነት ኃላፊነት አለባቸው:: አገርን አገር የሚያሰኘው የሕዝብ መኖር ነው:: አገርን የሚያነሳውም የሚጥለውም የሕዝብ ተባብሮ በሰላምና በአንድነት መኖርና ተግቶ በጋራ መስራት ነው:: ሕዝብ በሰላም ሲኖርና እንድነቱን ሲያጠናክር : አገር ሰላምና አንድነት አላት ይባላል:: ሕዝብ በሰላምና በአንድነት ኑሮ አገር እንድትበለፅግ ከተፈለገ መልካም አመለካከትና ቅንነት ያላቸው ግለሰቦች አስተዳዳሪና መሪ መሆን ይገባቸዋል:: ጥሩ መሪ የመጀመሪያ ግንዛቤ ማድረግ ያለበት : የሕዝብ ተወካይና ጉዳይ አስፈፃሚ እንጂ አዛዥና ገዢ እንዳልሆነ ነው:: የኢትዮጵያ ሕዝብ የለመደውና ሲስተዳደር የኖረው በግብዝ አምባገነን መሪዎች ስለነበረ : ዛሬ ያለውን መሪ ለመረዳት ችግር ላይ ወድቋል:: ይህንን ስል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብን ሳይሆን : በጣም ጥቂቶች የሆኑትን ኢትዮጵያን በጎሳ በመከፋፈል ለመበታተንና ለዘመናት በአንድነትና በፍቅር ተከባብሮና ተሳስቦ የኖረውን ሕዝብ በማጋጨት ሰላም የሚያሳጡትን የጎሳ ፖለቲካ አቀንቃኞችንና የፌስቡክና የዩቱብ ሳንቲም ለቃሚዎችን ነው:: ለሕዝብና ለሰው ልጅ መልካም ትምህርትና ጠቃሚ ሃሳቦችን ለሚያካፍሉ በፌስቡክ በዩቱብ በኢንስታግራምም ሆነ በቲክቶክ ሳንቲም ለቃሚዎች እሰየሁ በርቱበት እላለሁ::

 

ጠ/ሚ ዶ/ር አቢይ አህመድን ብዙሃኑ ይረዳዋል:: የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተዳደር የሚያመጣውን ጥቅምና ጉዳት አገር ቤት ውስጥ ያለው የአገሪቱ ተወላጆች በግልፅ ያዩታል:: የሚያስደስታቸውንና የሚያስከፋቸውን ፊትለፊት ይጋፈጣሉ:: ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምኞታቸውና አሳቢነታቸው ቀና መሆኑን በግልፅ ይረዳል:: ለውጡ ሁሉንም የሚፈለግበትን ያሟላል? አያሟላም:: ከበፊቱ ይሻላል? አዎን ይሻላል:: ሕዝብ በመራቡና በመቸገሩ : ልጆቹን ለአረብ አገረ ግርድና እየላከና : ለተሻለ ሕይወት በማለት በችግር ምክንያት ልጆቹ በመሰደድ የበረሃና የባህር ቀለብ ያደረገውን ሕዝብ ትተን : በሙስናና በዝምድና የአገርን ገንዘብ በመስረቅ ሀብት አዳብረው ዛሬ ያ ስርቆት የቀረባቸው ስስታሞች ላይመቻቸው ይችላል:: ለዚህም ነው በተሰረቀው የሕዝብ ገንዘብ የሚንደላቀቁ የወደቀው ስስታም ወያኔ ጁንታ እርዝራዥዎችና አተላዎች ለውጡን የሚቃወሙት:: በምቾት በዲስ : በቦስተን : በዳላስ: በአትላንታ : በሲአትል : በሳንፍራንሲኮ : በቢርትን : በጀርመን : በሲውድን : በኖርወይና በመላው አለም ተቀምጠው የመጣውን ለውጥ ቀልብሰው የተለመደውን ጭቆናና ብዝበዛ ለማካሄድ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ እየነሰነሱ ያሉት:: ሱሚ ይሁንባቸው:: የተጀመረው የእድገትና የእንድነት ለውጥ እንደፀደይ አበባ እያበበ ይሄዳል እንጂ ኢትዮጵያን ደም የመጠጡ ቅማሎች ተመልሰው ራሷ ላይ አይወጡም::

ተጨማሪ ያንብቡ:  "የህዝባዊ አንድነትና ኃይል የወያኔ ሕወሐት ማጥፊያ መድሃኒት"

 

በሰላም የመጣው ለውጥ የክርስትና ስም ብሰጠው : ደርግ “ያለ ምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም: ” ያለውን አነጋገር ለደርግ ሳይሆን : ዶ/ር አቢይ አህመድን ለዚህ ኃላፊነት ላበቃቸው የዛሬ ሶስት አመት ለመጣው ለውጥ ተስማሚ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ:: ያለምንም ደም ራስ ወዳዱን የወያኔ ጁንታን በሰላማዊ መንገድ አስወግዶ የኢትዮጵያን የፖለቲካና የኢኮኖሚ አቅጣጫ ጥሩ መንገድ በማስያዝ ኢትዮጵያን ማስቀደም ታላቅ የስራ ውጤት ተደርጎ መውሰድ የማንም መልካም አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን አመለካከት መሆን ይገባል:: ይህችን አነጋገር ቀንጠብ አድርገው እንዴት ኢትዮጵያ ውስጥ ደም አልፈሰሰም ትያለሽ በማለት ትግራይ ክልል ውስጥ ያለውን አረመረጋጋት : በአማራና በቤንሻንጉል : በሱማሌና በአፋር መሃል ያለውን ግጭት : በኦሮምያ ክልል ውስጥ አልፎ አልፎ የሚታየውን በጠባብ ጎሰኝነትና በነገድ ላይ የተመሰረተ ሰው ግድያ የሚያነሱ አሉ:: እነዚህ አስከፊ ኢሰባአዊ ድርጊቶች ሊካዱ አይችልም:: እየተፈፀሙ ናቸው:: ሆኖም እነዚህ እርስበርስ ግጭቶች ከጀመሩ ቆይተዋል:: መፍትሔው የሁላችንም አስተዋፅኦ ይፈልጋል:: በጭፍን ይህ የዛሬ ሶስት አመት የመጣው ለውጥ ውጤት ነው ማለት ተገቢ አይደለም:: ለውጡ ምቾታቸውን የቀነሰባቸው የወደቀው ጁንታ እርዝራዦችና ተላላኪዎች: ችግሩን አንዳባባሱት አይካድም:: ያንን ለማስተካከልና ለማረም የሚጥረውን መንግስትና መሪ በመውቀስ የሚመጣ መፍትሔ የለም::

 

ፍፁም ሰዎች በሌሉበት አለም : አንድን መሪ ፍፁም ሁን ማለት የሌለውንና ታይቶ የማይታወቅ የሰው ልጅ ባህሪ መፈለግ ይሆናል:: አንዳችንም ፍፁም እንዳልሆንን ከጎናችን ያለው የሰው ልጅ ፍፁም እንዳልሆነ እያወቅን ያልወለድነውን ፍፁም ልጅ እንደመፈለግ ነው:: በእግዚአብሔር ለሚያምኑት የሰው ልጆች : ፍፁም ፈጣሪ ብቻ ነው:: ሰው ከትላንት ዛሬ የተሻለ መሆን ይችላል? ይችላል:: ጥሩ ሰው መሆን እፈልጋለሁ ብሎ ሰው ከተነሳ በእርግጥ ይችላል:: ቀና ቀናውን ላድርግ ካለ ይችላል:: አሁን ያለው መሪ ከበፊቶቹ መሪዎች የተሻለ በመሆን የሕዝቡን ስቃይና ሰቆቃ በመረዳት አጠገቡ ካሉት የስራ ባልደረቦቹ የተሻለ በመሆን እነሱንም እንዲሻሻሉ ስብእናቸው በሰባዊነትና በእርህራሄ የተሞላ እንዲሆን መግፋት ይችላል:: ይህንን የሚያደርግ መሪ ከዚህ በፊት በአገራችን አልታየም:: አሁን ግን ሳናገኝ አልቀረንም:: ማበራታት ተገቢ ይመስለኛል::

 

አዎን! አንዳንዶች በማንኛውም ጊዜ መቃወምን እንጂ መደገፍ የሚባል እይታ የተሳናቸው : የዛሬ ሶስት አመት የመጣውን ለውጥ : የጉልቻ መቀያየር እንጂ ለውጥ አላየሁም በማለት የሚምሉ ምጽአት ጠባቂዎች አሉ:: እነዚህ ብርሃንን ጨለማ : ጨለማን ብርሃን አድርገው ማየትን እንጂ የማስተዋል ብርሃን ብልጭታ አእምሮአቸውን ያልጎበኛቸውን በምንም አይነት ቀና ነገር እዩ ማለት ይከብዳል::ለዚህ ነው  አውቆ የተኛን ሰው ቢቀሰቅሱት አይሰማም የሚባለው:: የአገርን ማንነት ጥያቄ ውስጥ ለመክተትና የሕዝብን አንድነት ከሚያውኩት የጎሰኝነትና የወገናዊነት ፖለቲካ በተጨማሪ : ኢትዮጵያውያን ነን: ለኢትዮጵያ ሉአላዊነትና አንድነት እንቆማለን እያሉ : ግን የመጣውን መንግስትና አስተዳደር በስራውና በድርጊቱ ድጋፍ ወይም ቅዋሜ ከማሳየት : በጭፍን ጥላቻ በመመራት: መሪው የመጣበትን ጎሳና ክልል በመመልከት ብቻ ሲረግሙትና ሲያንቋሽሹ ይገኛሉ:: ለእነዚህ ትልቁ ኢትዮጵያዊነትን የሚያሳዩበት መንገድ : ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ካለው አመራርና እስተዳደር ያገኙት ጥቅም ከሚጎዳው ድርጊት ይበልጣል ወይስ ያንሳል የሚል ጥያቄ በማቅረብ በመጠናዊ ሚዛን ማየት ሳይሆን : መሪውን አንወደውምና ምንም ያድርግ አንደግፈውም የሚል የተዛባ አመለካከት ከመጀመሪያውኑ በጠበበችው ጭንቅላታቸው በማሳደራቸው ነው:: በምኖርበት የዲያስፖራ አሜሪካ ከተማ በሶሻል ሚዲያዎች በሚደረገው ውይይት የታዘብኩት : ጭፍን ድጋፍ ወይም ጭፍን ቅዋሜ ነው:: ድጋፍና ቅዋሜ የዜሮ ድምር ጨዋታ መሆን የለበትም:: አንድ ሰው ድጋፍና ቅዋሜን ማራመድ ይችላል:: ምክንያቱም የሚፈልገው ውጤት ጠቃሚ እንዲሆን ከድጋፉ ጋር ገንቢ ቅዋሜ ማሰማት የሚቻል ስለሆነ:: ያለፉት ሁለቱ ስርዓቶች : የሰሩት 100 በ100 ጥፋት ነው የሚል ካለ ሚዝናዊነት ምን እንደሆነ መርምሮ የመገንዘብና የመዳኘትን ተሰጥኦ ማዳበር ይኖርበታል:: በተመሳሳይ 100 በ100 ጥሩ ሰርተዋል የሚል ካለም ባልተናነሰ መንገድ የግንዛቤንና የዳኝነትን ትርጉም ማጥናት ይኖርበታል::  ምክንያቱም 100 በ100 የፍፁሙነት ምልክት ስለሆነ የሰው ልጆች የሚያሳኩት አይደለም:: ፍፁም ያልሆንን ሰዎች በምንኖርበት አለም ውስጥ: ፍፁም የሆነ መሪና አመራር ይውጣ ማለት : ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ : የሚለውን ምሳላዊ አነጋገር ያስታውሰኛል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሀሳብን አወላግዶ ትርጉም መስጠት ከሀሳብ ነጻነት ሊመደብ አይገባም (ሰመረ አለሙ)

 

አሁን ያለው የዶ/ር አቢይ አመራር ፍፁም ትክክል ነው ለማለት ይከብዳል:: አይደለምም:: ካለፉት አስተዳደሮች የተሻለ ነው? በእርግጥ ይሻላል:: መችስ ፍርጃ ሆኖበት የመንግስት ቁንጮ ላይ ስለተቀመጠ : ሌሎች የመንግስት ተወካዮች በሚያጠፉትና ሕዝብን በሚያጎሳቁሉበት ምክንያት ይወቀሳል:: መወቀስም ይገባዋል:: ምክንያቱም እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንደሚሉት : “The buck stops with him.” እንደመሪ ከስሩ ላሉት ጥፋት እሱ ተጠያቂ ለመሆን የተቀመጠበት ወንበር ያስገድደዋል:: ወዶ መሪ ስለሆነ ይህንንም ወቀሳ በፀጋ የሚቀበል መሪ መሆኑን አሰመስክሯል:: በሶስት አመታት ያከናወናቸው የስራ እቅዶች ለአገሪቷና ለሕዝቧ ብልፅግናና እድገት እንደሚደክም ማረጋገጫ ነው:: በውጭ ጠላቶችና የጠቡትን የእናት ኢትዮጵያን ጡት ለመቁረጥ ከግብፅና ሱዳን ጋር አድማ የሚመቱትን ባንዳዎች ጋር እየተፋለመ የአባይን ግድብ ለማስጨረስ የሚያደርገው ጥረትን በኢትዮጵያዊ ዜግነታችን ከመደገፍ ይልቅ : ያልሆነ አገር አጥፊ : የሕዝብ አንድነትን የሚከናከን ፍሬፈሪሲኪ ቅዋሜዎች ማሰማት አቢይንና አስተዳደሩን አይጎዳም:: የሚጎዳው አገርንና ሕዝብን መሆኑ ለሁላችንም ግልፅ ይሁን::

 

በጣም የሚገርመው የሚቀርቡት ቅዋሜዎች በፖሊሲዎች ላይ ሳይሆን ጎሳና ነገድን የተመረኮዘ መሆኑ ነው:: ዶ/ር አቢይ አህመድ ለኦሮሞዎች ያደላል:: ለኦሮሞዎች ነው ስልጣን የሚሰጠው:: አማራዎችን ይጠላል:: ትግሬዎችን ያስጨፈጭፋል የሚሉት መሰሩተ ቢስ ክሶች ለአገር የሚያመጡት እርስ በርስ መጠላላትን ለማራመድ ካልሆነ እውነትን የተንተራሳ ክስ አይደለም:: ከተሳሳትኩ መታረም እችላለሁና : የዶ/ር እቢይ አህመድ ባለቤት ቀዳማዊት ዝናሽ አማራ ኢትዮጵያዊ አይደለች? እንዴት ብሎ ነው አማራ ኢትዮጵያውያንን የሚጠላው? አንድ ሰው ኦሮሞ ወይም አማራ ወይም ትግሬ ወይም ክርስትና ወይም እስልምና ሃይማኖት ተከታይ ስለሆነ የኢትዮጵያ መሪ መሆን የለበትም የሚል አስተሳሰብ : የኢትዮጵያን ብዙሃነጎሳነቷን አለመቀበልና ወገናዊ መሆን ነው:: ባይሆን ሹመት በጎሳ ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በእውቀትና በችሎታ የተለካ መሆን አለበት ብሎ መከራከር አግባብ ነው:: አለመታደል ሆኖ የኢትዮጵያን ፖለቲካ የምንተነትነው በተነደፉት እቅዶች : በፖሊሲዎችና በአስተዳደር ዘይቤዎች ሳይሆን ጎሳ ላይ በማትኮር ነው:: ይህ እካሄድ የዛሬ ሰላሳ አመት ስልጣን ላይ የወጣው የወሮበላው አረመኔ ጁንታ ስራ ውጤት ነው:: ከዚህ አዙሪኝ ልክፈት ውስጥ መሽከረር እስካላቆምን ድረስ : የሚከተለውንም ትውልድ በክለን አገሪቱን የባሰ እረመጥ ውስጥ በመክተት ሕዝባችንን የችግርና የስቃይ መደነሻ እናረጋዋለን:: ከባህር ማዶ ተቀምጠው በመንግስታት ድጎማ የሚኖሩ የፌስቡክና የዩቱብ እንዲሁም የሌሎች የሶሻል ሚዲያዎች ኪልክ ሳንቲሞች የሚለቅሙት ትህትናና ሰባዊነት የተሳናቸው ትምህርት የጣላቸውን እሳት ጫሪዎችን አንቅረን መትፋት ለአገር ሰላምና : ለሕዝብ አንድነት ይጠቅማል::

 

ሁላችንም ፍፁም አይደለንም:: ሁላችንም ውጣ ውረድ እናሳልፋለን:: በግል ኑሮአችን የሚገጥመን ችግርና መከራ ለእናንተ አንባቢዎች መነገር አይገባውም:: እንኳን አገር ማስተዳደር ይቅርና አንድ ቤተሰብ ማስተዳደር እየከበደ አይደል: ተማምለው በቁርባን የተጋቡት ሰዎች የሚለያዩት? እንዴት 110 ሚሊዮን ሕዝብ ያለበትን አንድ አገር ማስተዳደር እንደቀላል ታይቶ በመሪው ላይ የሚፈረጀው? ስንቱ ነው አራት አባላት ያለው ቤተሰብ ለማስተዳደር ችግር እየገጠመው እንባ የሚረጨው? ይህ መሪ እንደበፊቶቹ ተቃወማችሁኝ ብሎ አላሰረ: አልገደለ:: ማንኛውም ሰው የመኖር መብት በፈጣሪው ቢሰጠውም : ሲኖር የሌላውንም ሰውነትና ሰባዊነት ተረድቶ ማክበር አለበት:: የእገርን ህልውናና የሕዝብን አንድነት የሚያናጋ ከሆነ በሕጉ መሰረት ይጠየቃል:: ይቀጣል:: የመንግስት የመጀመሪያና ዋናው ግዴታና ስራ የአገርን ማንነትና የሕዝብን አንድነትና ደህንነት መጠበቅ ነው:: በዚህ ሂደት ውስጥ ሰዎች ሊጎዱ ይችላሉ:: በዚህም የዋስትና ጉዳት ይከሰታል:: ይህ የኢትዮጵያ ክስተት ብቻ ሳይሆን በማንኛውም የአለም እገር ይፈፀማል:: ምክንያቱም ሰዎች የተለያየ የቆዳ ቀለም : ቋንቋ: ሃይማኖት : ባህል ወይም ልምድ ቢኖረንም መሰረታዊ አመለካከታችን ስለሚመሳሰል : ችግራችንም ተመሳሳይ ነው:: እኛ ዛሬ በጎሳ በነገድና በወጋናዊነት አስተሳሰብ የምንመራበትን የጥላቻ ፖለቲካ የሰለጠኑ አገሮች ቀድመው አልፈው ትኩረታቸው ልማትና እድገት ላይ ነው::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ትንሿ ምሳር ወይም ጥልቆ ትልቁን የኮሶ ዛፍ ገዝግዛ ትጥላለች! - አገሬ አዲስ

 

ደርግና ወያኔን እናመዛዝን ብንል የሚያመሳስላቸው አረመኔነታቸው ነው:: ሁለቱም ለስልጣናቸው ሲሉ ያካሄዱት የሰው ጭፍጨፋ ካከናወኑት ጥሩ ነገሮች ጋር ሲነጥጠር የሰሩትንና ያመጡትን እድገት እንዳናስትውስ ያደርጋል:: የደርግ ቀይ ሽብር “አቢዮት ልጆቿን ትበላለች በሚል ፈሊጥ የጨረሰው ወጣትና ምሁር አገሪቱን 50 አመታት ወደሗላ ጎትቷቷል:: ከደርግ ሊብስ አይችልም በተባለበት ጊዜ ወደ ስልጣን የመጣው በወያኔ የሚመራው ኢሐደግ ኢትዮጵያን ሕዝብ ከመግደል በተጨማሪ በተለይ በእማራ ክልል ውስጥ የፈፀማቸው ሴቶችን እንዳይወልዱ የፈፀመው የሕክምና ማምከን ኢሰብአእዊ ድርጊት ሊረሳ አይችልም:: ከዚያም አልፎ ኢትዮጵያን በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ክልል በመፍጠሩ ሕዝባችንን ለጎሳና ለነገድ ፖለቲካ በማጋለጡ ዛሬ ልዩነቶች እየሰፉ በመሄዳቸው በየክልሉ ሰውን ከአገሩ ከተወለደበት አካባቢና ቦታ ማፈናቀልና መግደል ልምድ ሆኖ ተወስዷል:: የወደቀውና በስብሶ የሟሸሸው ወያኔ ጁንታ እርዝራዦችና ፍርፋሬ ለቃሚዎች : ያለፈው ሕዝብን ማጋጨትና አገርን ለክፍፍል ማጋለጥ አንሷቸው : ዛሬ ከተቀበሩበት ጉድጏድና ዋሻ ብቅ እያሉ ኢትዮጵያ የምትባል አገር አትኖርም:: ትግራይን እንገነጥላለን:: አማራና ኦሮሞን እድሜ ልክ እንዲጋጩና እንዲዋጉ እናደርጋለን:: በአፋርና በሱማሌ ክልሎች መሃከል የማይበርድ የጥላቻ እሳት እናነዳለን በማለት እየፎከሩ ይገኛሉ:: ለዚህም ነው ወያኔ የሰራው ልማት ቢኖርም ከፈፀመው ወንጀልና : ዛሬ እርዝራዦቹ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚያራምዱት ፖለቲካ አኳያ ሲታይ : ሰርቷል ብሎ መናገር አሳፋሪ ነው:: ስለዚህ ወያኔ ከደርግ ጋር ሲወዳደር : የአገር ጠላት : አገር አጠፋ እንጂ አገር መርቷል ተብሎ መቆጠር የለበትም:: የሚያሳዝነው የ2010 (EC 2018) አቢይን ስልጣን ያስጨበጠውን ለውጥ እንደለውጥ የማያዩት በምን መነፅራቸው ይሆን? በተለይ አማራና ኦሮሞ ኢትዮጵያውያን መገንዘብ ያለባቸው : በወያኔ ወጥመድ ውስጥ ገብተው : አማራ ኦሮሞን እንዲጠላ : ኦሮሞ አማራን እንዲጠላ ለማድረግ የሚመታውን ከበሮ አለመስማት አስፈላጊ ነው:: ከሆነም ይህንን ቅኝት የሌለውን ከበሮ በጋራ ማጥፋት እጅግ አስፈላጊ ነው:: አማራና ኦሮሞ ኢትዮጵያውያን የወያኔ መጋለቢያ ድንክ ፈረስ ከመሆን  መጠንቀቅ ይገባቸዋል:: በአማራና ኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ደም የወያኔ እርዝራዥዎችና አተላዎች አይነግዱም:: ትግራይ ኢትዮጵያውያንም በ27 አመት የወያኔ አስተዳደር ያገኘው መከራ ብቻ ስለሆነ የወያኔ ጁንታ እርዝራዦችና ፍርፋሬ ለቃሚዎች የረብሻ መሳሪያ መሆን  አይገባቸውም:: ዶ/ር አቢይ አህመድን ማጠላላት የወያኔ ጁንታ እርዝራዦችና ጠባብ ጎሰኝነትን የሚያራምዱ ፀረኢትዮጵያውያን ቀዳሚ ተግባር ነው:: ለዝህም የአገር መሪ ለአንድ ጎሳ ወይም ነገድ አግዞ ሌላውን ጎሳ ተወላጅ ያስገድላል ማለት ፍርደ ገምድልነት ነው የምለው:: በየክልሉ የሚደረጉት የጎሳና የነገድ ግድያዎች የሚቆሙበትን መንገዶች መፈለግ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ግዴታ ነው::

 

ለአገርና ለመላው ሕዝብ የምናስብ ከሆነ ማድረግ ያለብን : ያለው የዶ/ር አቢይ አህመድ አስተዳደር የሚሰራውን ጥሩ ነገሮች እያሞገስንና እያመሰገንን በርታ እንበለው:: ስህተት የምናላቸውን ድርጊቶች ወይም ፖሊሲዎች ምን እንደጎደላቸው ከማሻሻያ ጋር መጦቀም ገንቢ እርማት ይሆናል:: እያንዳንዳችን ፍፁም ሳንሆን : ሌላው ላይ ሁን ብሎ ጣት መቀሰር አግባብ አይደለም:: ለዚህም ነው ፍፁም ሰዎች በሌሉበት ምድር : መሪን ፍፁም ሁን ማለት ተገቢ አይደለም የምለው::

 

 

ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኖራለች::

23 Comments

  1. Well, it is the right thing to express one’s ideas and positions toward the political behavior and performance of the prime minister and his “comrades in arms “ . But it is absolutely misleading if not politically and morally wrong to try to show that what has happened and is happening in Ethiopia is as simple as what the writer of this piece is trying to .
    1) I have never come across any rational critique blaming the prime minister for not being a political person of absolutism . It is wrong and unproductive to say or write anything simply because we feel that it is okay to unnecessarily exaggerate things and defend the un-defendable .
    2) It is wrong if not both politically and morally self-degrading to try to show that the prime minister is not at the forefront of responsibility and accountability for the very unprecedented politically motivated crime within this very short period of time .
    3) It is a very ruthless idea to say that all the horrifying political crimes have happened because the prime minister is not absolute as a human being ! Absolutely nonsensical !!!
    4) It must be clear that the change the people are trying to make is not a matter of either blaming or praising the prime minister who is the brain child of ethno- centric politics of EPRDF but a matter of changing the system .
    5) It is very infantile and irrational to give unconditional or uncritical credit to him which very painfully ignores the untold sufferings of the people .
    You can worship him , but it is nonsensical to tell the people to do the same .
    Nobody with his or her right mind hate him personally but his political personality and behavior deserve not only to be hated but also to totally be rejected by any peaceful means !

    • YOU: Well, it is the right thing to express one’s ideas and positions toward the political behavior and performance of the prime minister and his “comrades in arms “ . But it is absolutely misleading if not politically and morally wrong to try to show that what has happened and is happening in Ethiopia is as simple as what the writer of this piece is trying to.

      Me: With due respect, what is happening in Ethiopia is simply TRIBAL POLITICS propagated by few protagonists seemingly caring for their tribal clans whose ultimate goal is to suck the blood of the people. WOYANE JUNTA is the epitome of this political game. What did the ruthless fascistic WOYANE JUNTA do good for Tigray Ethiopians? Absolutely nothing positive but extreme suffering which is being manifested today. I know that anti-Abiyists & pro WOYANE Junta activists throw their nonsensical accusations on current government. We may try to make politics as complicated as calculus, but it is not. It is a simple transactional process. When we all realize & wish that what each of us think & do for our benefits should benefit others, our country & it’s people can enjoy peace & consequently economic prosperity ensues.

      YOU: I have never come across any rational critique blaming the prime minister for not being a political person of absolutism. It is wrong and unproductive to say or write anything simply because we feel that it is okay to unnecessarily exaggerate things and defend the un-defendable.

      Me: Presenting PM Dr. Abiy as a despot makes me laugh. This inference of the PM to be absolute ruler, borrowing your own words, is wrong and unproductive to say or write anything simply because we feel that it is okay to unnecessarily exaggerate things and defend the un-defendable .

      YOU: It is wrong if not both politically and morally self-degrading to try to show that the prime minister is not at the forefront of responsibility and accountability for the very unprecedented politically motivated crime within this very short period of time .

      Me: Unless you are challenged with እማርኛ ቋንቋ , there is nothing & nowhere in my commentary that I said the PM isn’t responsible and accountable. In fact, I put it in simple English idiom, “THE BUCK STOPS WITH HIM.” No need for me to say more on this except suggesting to you to read again the commentary.

      YOU: It is a very ruthless idea to say that all the horrifying political crimes have happened because the prime minister is not absolute as a human being ! Absolutely nonsensical !!!

      Me: Do you mean that the PM must be A DESPOTIC RULER to curb the horrifying political crimes perpetrated by ruthless narrow minded tribalistic operatives such as the TPLF remnants, OLF, & others such as the ones in Benshangul, Southern Ethiopia, Afar, & Somali Killels? As human beings, as you touched, nobody is absolute, and we all have flaws. We try to manage our flaws in order to be better human beings from one moment to another
      .
      YOU: It must be clear that the change the people are trying to make is not a matter of either blaming or praising the prime minister who is the brain child of ethno- centric politics of EPRDF but a matter of changing the system .

      Me: You & I need to agree on one element of human functionality that builds or ruins the human beings. As we all human beings feed on praise or blame to sustain in our chosen endeavors & to flourish our individual personalities wrapped up with humanity, a leader or any common citizen of a nation needs constructive criticism to fulfill her/his obligations to the position he holds. Constructive criticism is positive & effective. Blame is its antithesis, and it isn’t productive. Assuming that the PM is the brainchild of of ethno-centric politics of EPRDF is demeaning the humanity of PM. No person is a brainchild of nobody. You can criticize & him for any deranged reasons but describing him the way you did is indication of hatred. You have all the possible rights to disagree with his politics, but not to disparage him as a tool.

      YOU: It is very infantile and irrational to give unconditional or uncritical credit to him which very painfully ignores the untold sufferings of the people .

      Me: If this is your take from my commentary, you need to freshen up your አማርኛ ቋንቋ or to find someone well versed in አማርኛ ቋንቋ to translate it to you in the way you can soak it down. I never gave unconditional or uncritical credit to him. I still believe that he cannot remedy by himself all the malaise & sufferings affecting the Ethiopian people. These never ending crises need your & my inputs to find permanent solutions.

      YOU: You can worship him , but it is nonsensical to tell the people to do the same .

      Me: Again the same shit is manifested in this statement. I now come to realize that you may lack understanding አማርኛ ቋንቋ. I worship only ONE GOD. There is no human being including my own mother who conceived & birthed me in the universe who deserves to be worshipped. Please save the word for DIVINE POWER.

      YOU: Nobody with his or her right mind hate him personally but his political personality and behavior deserve not only to be hated but also to totally be rejected by any peaceful means !

      Me: Politics isn’t a hate & love game. Politics is process of moving ideas around to establish understanding for benefits of the common good of the nation & its people in question not political arguments. But in your world, it has become a hate & love issue. These are types of emotions. Because of these uncontrollable emotions, the political tensions and disorders culminate in disaster which our Ethiopia is currently facing.

      In conclusion, my suggestion is not to engaged in politics emotionally but to be rational & thinking participants.
      Disclaimer: I do not belong neither to any political operation nor party, don’t live in nor intend to live in Ethiopia. I do not have any financial or other types of benefits except few poor relatives who look for my handouts. So, whoever assumes that I am trying to kiss anyone’s behind by my commentary must be irrational douchebag. I am sharing my views to engage my fellow Ethiopians in constructive discussions for betterment of our nation & people in order to see my poor relatives to be self-sustainable in their lives

  2. “ዶ/ር አቢይ አህመድን ማጠላላት የወያኔ ጁንታ እርዝራዦችና ጠባብ ጎሰኝነትን የሚያራምዱ ፀረኢትዮጵያውያን ቀዳሚ ተግባር ነው:: ለዝህም የአገር መሪ ለአንድ ጎሳ ወይም ነገድ አግዞ ሌላውን ጎሳ ተወላጅ ያስገድላል ማለት ፍርደ ገምድልነት ነው የምለው:: በየክልሉ የሚደረጉት የጎሳና የነገድ ግድያዎች የሚቆሙበትን መንገዶች መፈለግ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ግዴታ ነው::”

    አይዞሽ ያንቺ ዓይነት ሚሊዮኖች አሉ። ስለማይናገሩ ነው [silent majority]።

    መደገፍም መቃወምም መብት ሆኖ ሲያበቃ ችግር የሚሆነው የአንቺ ዓይነት ሚዛናዊ አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎች ለማሸማቀቅ ሲሞከር ነው። ሰሎሞን ሹምዬ [በወያኔ ቲቪ የሻይ ቡና ፕሮግራም አዘጋጅ የነበረው] እንኳን “የዩቱብ ገቢ የሚገኘው አብይን በማጥላላት” ነው ብሎ ስድቡን ተያይዞታል። አንድ ቪዲዮ ላይ “non-sense’ እስከማለት ደርሷል። ምን ይብላ? ሻይ ቡና ቢል ስፖንሰር አያገኝማ።
    በምርጫ ብቻ!

    • Sorry for responding in English because I don’t have Amharic Fonts on my computer.

      The silent majority should speak out what it believes the truth rather than being silent observants & spectators. It doesn’t matter what political views the y lean to but need to express. I am not looking for anyone to support my views but engage me in sensible & rational exchange of views and ideas. It doesn’t help a nation in trouble and people in political siege to be for or against. Life isn’t always v black and white but mostly gray, to live in harmony with each other. This is my cup of tea in defining LIFE we live in.
      Stay blessed!!

      • Dear Almaz – It is very simple to have the Amharic Software/Fonts on your devices including your computer. Here are some choices:
        1. https://www.google.com/intl/am/inputtools/try/ – after the page opens near by the keyboard icon click the arrow and change it to Amharic and you can type away as you wish and cut and past it
        2. You can download and install the full version of the Amharic software including the Fonts from https://keyman.com/keyboards/h/amharic/ – This one is the best one!
        3. If you are using PC or an Apple there is an input method for Amharic you can download it directly from their system.
        I am hopeful in the future you will respond in the Amharic language for an opinion that is written in Amharic. Some of the people that respond in English for an Amharic opinion because of their hate of the Language. We should not play into their hands.

      • “Silent majority has to speak out” ላልሽው፣ how? ሲባል – the only way the “silent majority”
        speaks is through a credible election እላለሁ – the mother of ALL tests is coming soon!
        አሁን የመጨረሻው የሞት ሽረት ትግል ላይ ናቸው። ባይሆንማ ዲሲ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ፊትለፊት በአሁኑ ሰኣት የተቃውሞ ሰልፍ ይጠራል እንዴ? ይሰለፉ ግን አቴንሽን ለመሳብ ብለው የማይሆን ነገር እንዳያደርጉ ነው። አለ አይደል ረብሻ ምናምን!
        እኔ ኮሜንት የጻፍኩት ባለሽበት አገር በተወናበዱ ሰዎች ጫና ምክንያት በራስሽ ላይ ጥርጣሬ እንዳይኖርሽ ነው።

        “I am not looking for anyone to support my views but engage me in sensible & rational exchange of views and ideas.”
        ለዚህ ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላወኩም። ተሳስቼ ወይም ሳይገባኝ ከሆነ የጻፍኩት ይቅርታ!
        በምርጫ ብቻ!

  3. ፍፁም ሰዎች በሌሉበት ምድር : መሪን ፍፁም ሁን ማለት ተገቢ አይደለም (በአልማዝ አሰፋ – ዘረ ሰው)

    do you mean Abiy could massacre non amhara and everyone who stand against him ? do you mean all people are genociders and Abiy could do the same ?or you might mean all leaders are corrupted and Abiy could do steal and sell the country ?

    • What you wrote in your comment is absolute malarkey. In fact your penname describes you accurately. Nothing you wrote makes sense to respond intelligently. Individuals like you are the troublemakers pushing Ethiopia into chaos.

      If you want response from me, please indicate the part of my commentary which led you to your nonsensical logorrhea.

      Have a productive & peaceful day!!

      • almaz assefa how much money ar you paid to justify killings of amhara and their stooge ? Are you learning insults in english there ? Who is your mentor ? Did you spent some time with eritreans ? Amhara elites are peacemakers , but they want to annexe Oromia, Welkait and Raya and kimant woreda . Insulting and downgrading is the part of amhara elites campaign and eritreans born to amharas do teh same just like a goat learnt from Donkey.

        • Your comment reminded me a certain quote from a man called Laurence J. Peter. It goes like this: If a cluttered desk is a sign of a cluttered mind, of what, then, is an empty desk a sign?

          I wish we can find readers who can decipher what you wrote so I can understand it.

          ወረዳ መሆን ስልጣኔ አይደለም:: ከጨዋ ቤተሰብ ተወልደህ : እታስፍራቸው:: ቁም ነገር ከሌለህ ጣትህንና ኪይቦርዱን አታገናኛቸው:: ምክንያቱም የሁለቱ ጥምርነ የሞራልና የስብእና ዝቅትኝነትህን ያስገምታል::

  4. እውቁ የትግርኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ ሃጎስ ገ/ህይወት የዛሬን አያርገውና “ንመዘከርታኺ” በተባለው ዘፈኑ ላይ እንዲህ የሚል ቃል ይገኝበታል።
    ከደም ጠብታ መሃል የጣር መንፈስ ይሰማል እያለ ይቀጥላል። ሽንኮችና የፓለቲካ ወፈፌዎች በሚራወጡባት የበልተኽህ አብላኝ ፓለቲካ ለሃገርና ለወገን ዘርና ቋንቋን በተሻገሩ መልኩ ማሰብ ለብዙዎች ተራራን መውጣት ሆኖባቸዋል። ሲጀመር ዘረኝነት በሽታ ነው። የዚህ በሽታ አመጣጡ ደግሞ ጠበንጃ አንጋች ሃይሎች ነጻ እናወጣሃለን የሚሉትን ያን መከረኛ ህዝብ የሚያባብሉበት የዘርና የቋንቋ መላሾ ነው። ዛሬ ምድሪቱ በምጥ ላይ ናት። የዚህ ሽንክና የጨለማ ሥራ አራማጆች ደግሞ የወያኔና የኦሮሞ ሙታን ፓለቲከኞች ናቸው። በስንት ድካም ተዘርቶ፤ አድጎ፤ ታጭዶ የተቆለለን የእህል ክምር በአብሪ ጥይት አቃጥሎ ተራብኩ የሚል የእብዶች ሃገር ነው የሃበሻው ምድር።
    በመሰረቱ ዶ/ር አብይን የሚጠሉና የሚያጥላሉ ሃይሎች በሶስት ይከፈላሉ።
    1. ከፓለቲካው የተገፉ የትግራይ/ኦሮሞና አማራ እንዲሁም የሌሎች ብሄር ተኮር ሃይሎች
    2. ጠ/ሚሩ ወደ ስልጣን ከመጣ በህዋላ ለስልጣን ቋምጠው ሥፍራ ያላገኙ ወይም የተገፉ ሰዎች
    3. በፈጠራና በውሸት ተጋኖ የሚወራውን ወሬ እንዳለ የተጋቱና በተለይም የአማራ መጨፍጨፍ የሚከነክናቸው ናቸው።
    ከእነዚህ ሶስት ነጥቦች የአማራ እልቂት ዛሬም ቢሆን በወያኔ ዘመንም ለመኖሩ ዓሊ የማይባል እውነት ነው። ግን ሰው በሰውነቱ በማይፈረጅበት ሃገር አማራው ለአማራ ብቻ ካለቀሰ፤ ትግሬው ለዘሩ ብቻ ኡኡታ ካሰማ፤ ኦሮሞና ሌላው በዚያው በዘሩና በክልሉ ዙሪያ ብቻ ለመብት ተከራካሪ ሆኖ ከቆመ የሰው ልጅ ስብዕናው የቱ ላይ ነው?
    እኔ ዶ/ር አብይ ሆን ብሎ ሃገር ለማጥፋት፤ የዘር ፓለቲካ ለማራመድ ይጥራል ብዬ አላምንም። ግን በየደረሰበት እንቅፋት እየመታው ደፋ ቀና እያለ ለመሆኑ እማኝ አያስፈልግም። ይህ ደግሞ በውጭና በውስጥ በተቀናጀ መልኩ የተቃጣበት ጥቃት እንጂ ራሱ የፈጠረው አይደለም። እውነት ነው ወያኔን እሽሩሩ ማለቱ የሰሜን እዝን ወያኔ እስከመምታት አድርሶታል። አመራሩን ለቅሞ እስር ቤት ከቶአቸው ቢሆን ኑሮ አሁን ያለበት ሁኔታ የተለየ በሆነ ነበር። ስንት በደል በሃገሪቱ ላይ የፈጸመው ሳሞራ ያው በአዲስ አበባ ዘንጦ አይደል እንዴ እየኖረ ያለው። ግን ጠ/ሚሩ አንድ ያልገባው ነገር አለ። አንዴ የወያኔን ጽዋ የጠጣ እስከ እለተ ሞት ድረስ ወያኔ ነው። ጭራሽ አይታመኑም። ባጭሩ ዓለም አቀፋዊ እይታ የሌለው የዘር ሰካራም ከየትም ብሄር ቢሆን ለሃገርና ወገን ጠንቅ ነው።
    ዛሬ የምዕራባዊያን ጫና በተለይም የአሜሪካ ከሱዳን ጋር መወዳጀት በሃገራችን ላይ ትልቅ ጫና እያደረሰ ይገኛል። አሜሪካ ማለት ሃገር አፍራሽ ማለት ነው። እጃቸው የገባበት ሁሉ ፍጻሜው እንዲያ ነው። 40 ዓመት ሙሉ እነርሱን ሲያገለግል የነበረው የግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ተሽቀንጥሮ በስፍራው የምህንድስናው ዶ/ር መሃመድ ሞርሲን በምርጫ ያስቀመጡት ግብጻውያን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌላ መለዪ ለባሽ አልሲሲን ነው በግድ የተጫነባቸው። ለዚህ ደግሞ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የአሜሪካ እጅ አለበት። ግብጽ ከናስር ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የወታደር መንጋ ሲያምሳት የኖረች ሃገር ናት። የአሜሪካን ዲሞክራሲ እኔ የምልህን አድርግ ሌላውን ጉድለትህን እኛ እንሸፍናለን ያ ካልሆነ ገባተ መሬትህን እናፋጥናለን ነው የሚሉት። አሁን ማን ይሙት በኤርትራና በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ ይጣላል? በወያኔ በሮኬት የተደበደበችው ኤርትራ ራሷን የመመከት መብት የላትም? ኢትዮጵያስ በምድሯ ህግና ደንብ የማስከበር ስልጣን የላትም? የአሜሪካ ፓለቲካ የሚመራው በ (Lobby – a group of people seeking to influence politicians or public officials on a particular issue). በሃገራችን ቋንቋ ይህ ሲተረጎም በቀጥታም ሆነ በእጅ አዙር ጉቦ መስጠት፤ ጀርባዬን እከክልኝና ልከክልህ አይነት ዘመናዊ የሌብነት ስልት ነው። ወያኔ ዘርፎ ባጠራቀመው ገንዘብ ነው ሴናተሮችን ያለ ልባቸው በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርጉ ያደረጋቸው። አልማዝ አሰፋ (ዘረ ሰው) ባሰፈረችው ሃሳብ እስማማለሁ። ጠ/ሚሩ አጨልመው ለማሳየት የሚወድና የሚከጅሉ ሃይሎች ሁሉ የቀን ጅቦችና ከበግ ውስጥ የተደበቁ ተኩላዎች ናቸው። ሃገሪቱ አሁን ባለችበት ገዳዳ (precarious) ጎዳና ላይ ከዶ/ር አብይ የተሻለ ሌላ መሪ እንኳን በቅርብ በሩቅም አይታየኝም። ጠ/ሚሩን የማጥላላቱም ዘመቻ ከፍራቻና የፈጠራ ወሬ ከትንሽ እውነት ጋር ተቀላቅሎ በእነዚህ ሃይሎች የሚለቀቅ የወሬ ጋጋታ ነው። ጠ/ሚሩ ከተመረጠ የተሻለ የስልጣን እይታና ጉልበት (Mandate) ስለሚሰጠው አሁን ያለውን የወያኔና የአረብ ጋጋታ ሁሉ ጸጥ እረጭ በማድረግ ሃገሪቱን ወደ ተሻለ እይታ ያሻግራል ብዬ አምናለሁ። በቃኝ!

  5. በመጀምሪያ ለአልማዝ አሰፋ( የሰው ዘር) ለቀረበው እውነተኛ የትዝብት አስተያየት ምስጋና ይድረስ እንዲሁም ለከድር ሰተቴ እና ለተስፋ ለአልማዝ አሰፋ ለለገሳችሁት መልካም አስተያየት እና የሞራል ድጋፍ ተባረኩ። በበኩሌ የምጨምረው የለኝም።ያለኝ ነገር ቢኖር አልማዝ አሰፋ (የስው ዘር) አይዞሽ ጠንክሪ።

    • Dear I appreciate your kind words, and the moral support from Kedir State & Tesfa. From my stay in Diaspora to my age of Grandma, life has taught me to say what I feel, and learned from my experience to be corrected when I am wrong. Do I fit in the group the ass-kissing, self-enriching, lying, & humanity lacking political operatives? I refuse to. I have lied in my life so many times to advance myself without hurting anyone in the process. I am at the age of repentance for my past sins of selfishness. Even though I cared a lot for my native country, THE COUNTR of 13 MONTHS OF SUNSHINE, & my people, I never engaged myself in this kind of form to voice my views. GOD is Great to keep me healthy, age gracefully, & allow me to have abundance of free time to occupy myself with current issues of Ethiopia. I know that I am dealing with those in the age of my own children or grandchildren if I had started making children in my twenties. It is what it is & I don’t shy away to take the insult, if it comes, and to shoot out one if necessary. But I prefer intelligent discussions which I can learn from. I encourage my peers in my age group tp actively participate in the current affairs of our motherland. Be blessed!!

  6. Writer Alamz, thank you for your response to my comment on your comment. I appreciate the way you tried to explain your words and phrases and sentences as well with some sense of civility.
    Without going back and forth, I do not think the very wordings of your piece requires language skill you are talking about. I read all your wordings and phrases between lines. I do not think it is difficult to understand the whole context of your piece starting from your very topic you chose. Any ordinary reader with his or her rational mind can understand the very gist of the piece.
    Do you really believe that all crimes against humanity, genocide, war crime etc. happened simply because Abyi is not or cannot be an absolute leader, not because he is the very brainchild of the painfully ugly and dangerous politics of ethno-centrism?
    Is he not the leader of the junta faction of EPRDF which ousted its mother junta, TPLF and keeps running the same system in a much more horrifying manner?
    Do you really know the real meaning of junta? Why you just picked this word from his mouth and repeat it just like a parrot?
    Yes, TPLF/EDRDF was a typical junta throughout its political grab. It came to power by hook or crook and stay in power by the political game of using fake elections and by destroying others whenever it felt that they were threats to its power.
    Do you deny that those who controlled the palace with the leadership of ODP/Oromuma are committing unprecedented politically motivated crimes not only against innocent citizens who are trying to challenge its power but also against countless ordinary innocent Ethiopians simply because of their identities (who they are and what is their faith)?
    Is there any other criterion to call a junta is a junta? It is self-evidently clear that as far as the unprecedented crimes we watched for three years is concerned, there is no doubt that Abyi is the leader of the junta faction in the palace.
    Do you really believe that this political system of vicious cycle can get better with the leadership of politicians who are dangerously restless and frustrated because their hands are badly stained with the very blood of so many innocent citizens for three decades?
    Abyi was given a golden chance when he took power. Not surprisingly enough, he terribly failed because the very purpose of his grouping was to oust TPLF and replace it with its own hegemony in a much faster and worse manner without making a systemic change.
    Like it or not, there will never be any significant change let alone the realization of democracy with the leadership of Abyi who is dangerously suffering from the political personality of cynicism, dishonesty, conspiracy, hypocrisy, narcissism (excessive self-aggrandizement), lie, infantility etc.
    That is why I strongly argue that trying to find any clumsy excuse (human beings are not absolute) and trying to make what is terribly bad good does not make sense at all as far as the realization of the very interest of the people (true democracy) is concerned.
    Take it easy! This is the way we need to deal with if the horrible and deadly politics of ethno-centrism of Abyi and his army of cadres should be the thing of the past!!

    • Among all your points you mentioned, the most crucial is the TRIBAL POLITICS which you put as ETHNO-CENTRIC needing serious & honest discussions among Ethiopians. Let me focus on that because it is the mother of all malaise affecting Ethiopia.

      The ugly & divisive ethnocentric politics in Ethiopia didn’t start with EPRDF led by TPLF JUNTA (an ethnocentric political group taking power by force ruled the nation for 27 years. I am not parroting Abiy, but stating the fact. Hope you agree with me on this). Though I am not versed in Ethiopian History, from my limited knowledge, Eritrean movement of secession from Ethiopia advanced the tribal movements & encouraged other narrow minded individuals from different tribes to conspire against the integrity & sovereignty of Ethiopia in the same fashion. Haile Selassie University (currently AAU) Students started student movement for change in 50s (Ethiopian calendar, you might not have been born). This student movement immersed in communist & socialist ideology started fanning & promoting the idea of the rights of nations (in Ethiopian case TRIBES) to secede from mother nation. This idea of secession planted by student movement became the stepping stone to all wannabe tribal chieftains with hope of forming non sustaining dinky nations rather having a United Country. The TPLF JUNTA succeeded in promulgating such a devious ethnocentric politics with formation of 9 territorial divisions, 8 based prominently on languages, & the Southern Ethiopians territory which reflects multiethnic Ethiopia. The ethnocentric politics isn’t the work of Abiy, but it has been the centerpiece of Ethiopian politics for more than 60 years. The Ethiopian population under 50 (I assume that it is the majority) grew up hearing the drumbeat of this divisive ethnocentric political propaganda. The solution doesn’t come by blaming one person or one political party. It needs concerted effort from leaders, government, political operatives, political parties, academicians & citizens at large. It is necessary to educate ourselves about the power of United people. Allowing a nation to disintegrate into mini states won’t benefit anyone involved except exacerbating the situation to the extent of burdening the people of “the-supposed-to-be-neighboring dinky nations”with never ending wars among themselves from generation to generation. How in the hell OROMIA nation can interact & trade peacefully with AMHARA nation knowing what caused the creation of their mini-nations if this reality happens? Who will trade with mini-nation of TIGRAY if it becomes a dinky nation realizing the rhetorics of the fallen TPLF JUNTA remnants & its paid agents wishing the disintegration of Ethiopia? It is easy to postulate something in theoretical settings. But the reality of that would be devastating to all participants. We need to learn from the fate of other nations such as our neighbor Somaliland, across the Red Sea, Yemen, little further Northeast IRAQ & SYRIA. These tragedy filled nations in the verge of disintegration don’t have an excuse of language differences. The people of each nation speak one language. But it didn’t matter to the perpetrators but the thirst & hunger for power blinded the factions without thinking about the devastating consequences to the nations as whole. In our case, the language differences can become justifiable causes for separatists to strengthen their positions as happened in Eritrea. It is commendable to give voice to voiceless from each tribe who are unjustly denied their human, legal, & cultural rights. I understand very well what predicament the AMHARA ETHIOPIANS faced & face due to their long history as backbone of the Ethiopian sovereignty. The main goal of every narrow minded tribalistic ignoramus is to push the AMHARA ETHIOPIANS into tribal camp, and knowingly or unknowingly few AMHARA ETHIOPIANS seem to fulfill the desire of the tribalistic nincompoops. If we really & sincerely feel ETHIOPIAN first, we need to adhere to it rather than being dragged into the juggernaut of tribal political culture. Dying AMHARAS, OROMOS, TIGRAYS, AFARIS, SOMALIS, and other Ethiopians should be identified as Ethiopians first. When we stop to play the tribal game, we can conquer our tribal emotions, and solidify our ETHIOPIAWINET. That is why at this moment when the integrity & sovereignty of Ethiopia is in question, we should stand firmly & unequivocally assert our ETHIOPIAWINET rather than pleasing the instigators & agitators of tribal politics by adhering ourselves to tribal identity.

      TG, anywhere in my commentary I never condoned the atrocities committed on any of our people based on their tribe, language, faith, religion or sexual orientation. It pains me as it pains you and other decent human beings when people are accused, persecuted, displaced, tortured, killed, or disenfranchised for any reason in their own country.
      Let us refer to these victims as ETHIOPIANS rather diminishing them as part of a tribe or a clan.

      I may come back to your other points in another time.

      Thank you for engaging me in this conversation. Hope we both & other readers get something out of our dialogue.

  7. አልማዝ አሰፋ ግሩም ፅሁፍ ነው:: እንደዚህ ያለ ሚዛናዊ አስተያየት ስመለከት በኢትዮጵያ ተስፋዬ እጅግ ልቆ ይገኛል:: ዶክተር ዐቢይ ሰው እንደመሆኑ ስህተቶቹን ነጥሎ ማየት ይቻላል ሆኖም በጦርነት መካከል ሀገራችንን በመምራት ከእሱ የሚወዳደር በታሪካችን እንዳልነበር እኔ በግሌ እረዳለሁ:: ወያኔ የሚባል አረመኔ ባይፈጠር ኖሮ ይህ መሪ ሀገራችንን ዬት ባደራሳት::እጅግ የሚገርመኝ የዐቢይ አብጠልጣዮች የረባ ማሳመኛ ሲያጡ እኛ የእሱን መልካም ስራ የምናደንቀውን ምንም የማናውቅ ጅሎች አድርገው ለማሳመን ሲዋትሩ ድፍረታቸው ያስገርመኛል:: ለማንኛውም በየፌስቡክና ዩቱብ የሚንጫጫው ብዙም ኢትዮጵያን ስለማይወክል የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫው ማን እንደሚወራው ያሳውቀናል::

  8. ዘር ሰው አልማዝ

    ድንቄም ተፍጡምነት ማነጣጠር፡፡ ለሃያ አምስት ዓመት ኢሀድግ ሆኖ እየሰለል ሰው ስያስጠብስና ሲያስገድል የነበረን ወንጀለኛ ወደ ፍጡምነት ማስጠጋት በኢህዴግ ዘመን ባለለቁት ንጡሃን መቀለድ ነውና እግዜር ደጋግሞ ይይልሽ! እግዚኦ እብደት!

    • በእንድ የበሰበሰ ስርአት ውስጥ በአገር ደህንነት አገልግሎት ሃያ አምስት አመት የሰራ ሰው መሪ አይሆንም : ሕዝብ የሚፈልገውን ለውጥ አያመጣም የሚል አመክንዮ ውሃ አይቋጥርም:: መጠየቅና መመርመር ያለበት : ለስልጣንና ለግል ጥቅም በዚያ የኃላፊነት ቦታ ላይ ተቀምጦ ሰው አስግድሏል : አስጨፍጭፏል ተብሎ መረጃና ማስረጃ ከተገኘበት እንኳን አብይ : ወላጄ አባቴም ቢሆን ተጠያቂና ተከሳሽ አደርገዋለሁ:: አንተና መሰሎችህ ቢራ ማጣጫ ያደረጋችሁትን አሉባልታ አቢይንና ኢትዮጵያዊነትን ለማስከበርና ዘለዓለማዊ ለማድረግ ራሱን ለአደጋ ያጋለጠበትን ዓላማ አንዲት ስንዝር አያስተውም:: በርታ በት በጥላቻህ የኢትዮጵያ እንቅፋት!!

      በአስተሳሰብህ ከስምህ ማህከለኛዋን ፊደል ብታወጣ የሚቀሩት ሁለቱ ፊደላት የሚፈጥሩት ቃል የተገለፅክ ይመስላል:: አንዳንዴ የተሰጠ ስም የራስ መሰደቢያ ይመስላል:: የስምህ ማህከለኛዋ ፊደል ተሳስታ ያለቦታዋ የገባች ስለሆነች አንስቼልሃለሁ::

  9. በየዘመኑ ጪራውን የሚቆላ አሽቋላጭ አይጠፋም፡፡
    ለአረመኔውን መለስ እንደ ክፍሌ ወዳጆ ያሉ ከርሳሞች እንዳሽቋለጡ አለፉ፡፡
    ወላሻው ሀይለማሪያም ሲመጣም ብዙዎች አሽቋልጠው አለፉ፡፡
    አሁን ደግሞ እነ አልማዝ አሰፋ ለዚህ ነፈሰ በላ እንዳሽቋለጡ ሊያልፉ ነው፡፡ ክፉ ዓመል፡፡

    • ሽፈራው- የቸኮለ ጅብ ቀንድ ይነክሳል የሚለው ተረት እንዳይተረትብህ ብታስብ ኖሮ የመጀመርያው አንቀፅ ላይ የፃፍኩትን አንብበህ ብታኝከው ኖሮ : አንብቦ ዶማነትህን አታስመሰክርም ነበር:: በባእድ አገር ተንደላቂቄ ልኖር ያስቻለኝ እሽቋላጭነት ሳይሆን እውነትንና ሃቅን መመሪያ አድርጌ ፈጣሪ በሰጠኝ ችሎታ ፀጋ ነው:: አንተና እኔ አቢይን ከዲዬስፖራ ሆነን ወደድነው ወይምጠላነው : ለእራስህ ዝቅ አድርገህና ዋጋቢስ አድርገኸው የምታየውን ማንነት ዋጋ ለመስጠት ካልሆነ ለእሱ ጉዳዩም አይደለም:: የአንተና የእኔ መኖር ለአቢይ ደንታውም አይደለም:: ሊሆንም አይገባም:: ለእሱ አንገብጋቢና ተጨባጭ ጉዳይ የኢትዮጵያን ልዑላዊነት ማስከበርና የሕዝብን ሰላምና አንድነት መጠበቅ ነው:: ስለዚህ እኔ ሰደብከኝ ኮነንከኝ አንተ ለእኔ ሳላስተውለውና ሳልሰማው ያለፍክ ንፋስ ነህ:: ለሚቀጥለው ጊዜ እንደሰው እንዳስተውልህ ከፈለክ የቃላት ጠረባህን ትተህ : ማሰብ ይችላል የሚያሰኝህን አስተያየት አቅርብ:: ስድብ ፈስ ነው:: አፊንጫ አስይዞ ያልፋል:: አህያም መፍሳት ትወዳለችና ሰው መሆንህን ዘንግተህ ከእሷ እንዳትቆጠር ተጠንቀቅ::

  10. በመጀመሪያ ከአልማዝ አሰፋ (የሰው ዘር) በህገራችን ኢትዮጵያ በሦሥት አስተዳሮች የታዘበችውን እውነተኛ አስተያያት እሷን አመስግኘ እንዲሁም ለጽሁፏ የሞራል ድጋፍን ለለገሱላትም አምስግኘ ተቀምጨ ነበር።የነበረው ምስጋናየ እንደተጠበቀ ይሁን።ሆኖም ግን ይህንን አግባብ ያልሆነ ቃል ለመጻፍ የተገደድኩት KILIMANJARO ለተባለው ሰው መሆኑ እንዲታወቅልኝ።
    መጀመሪያ KILIMANJARO የብዕር ስምህን በተራራ መሰየምህ ድክመት በመሆኑ ስምህን “የቆላ ዝንጀሮ” ብትለው መልካም ነው።ምክንያቱም አልማዝ አሰፋ በሦሥቱ አስተዳደር የተፈጸመውን መልካም እና መጥፎ ተገባሮች በማመዛዘን የጻፈችው አስተያየት ለትምህርት የሚበቃ እንጂ የሚያስወቅስ አረፍተ ነገር የለውም።በአንተ በኩል በዚሁ አምድ ላይ አግባብ ያልሆነ አስተያየት የሰነዘርክባት አንሶህ “የኢትዮጵያ አገር አድን ግብረኃይል” የሚባል ድርጂት በዋሺንግተን ዲሲ ኢትዮጵያ ኢምባሲ ላይ በጠራው ሰልፍ አምድ ላይ ደገምከው።በመሆኑም የቆላ ዝንጀሮ የሚፈልገውን በቅጡ ስለማያውቀው ከአንዱ ገደል ወደ አንዱ ሲዘል ውሎ ምንም ሳያገኝ እዚያው ያድራል።ታዲያ ያንተ አስተያየትም ምንም ግኙነት እና የተጨበጠ ነገር የሌለው ከአንዱ ተራራ ወደ ገደል በመሆኑ የቆላ ዝንጀሮ ብየ ሰየምኩ። ስሰይምህም ታጥቦ ባልተተኮሰ ጨምዳዳ እንግሊዘኛ ከመጽፍ በአማረኛ ቋንቋ አትጽፈውም ነበርን? አዎን በአማረኛ ቋንቋ አትጽፈውም ምክንያቱም አማረኛ ቁንቋ በየትኛውም አለም እንደማይጻፍ እና እንደማይነገር የታወቀ፤ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን/ዊት ብቻ የተሰጠ የማይሸጥ የማይለወጥ በመሆኑ እንደ ፌስ ቡክ የማይረባ ሸቀጥ ማራገፊያም ባለመሆኑ መጠቀሙን ትጠላዋለኽ። ቢሸጥ ኖሮማ እንደ አለሌ ወሸ ትፏልል ነበር። በል ደህና ሁን KILIMANJARO( የቆላ ዝንጀሮ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share