October 13, 2019
27 mins read

ከሁለት ቀናት በኋላ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ይወስናል! – ስዩም ተሾመ

103641871 1855312385

ህወሓት መጋቢት 2011 ዓ.ም ወይን በተሰኘው የድርጀቱ የንድፈ ሃሳብ መፅሄት ላይ ባወጣው ባለ 43 ገፅ ፅሁፍ የኢህአዴግ ውህደት ቀጥተኛ የሆነ የህልውና አደጋ እንደጋረጠበት ገልጿል። በዚህ መሰረት ላለፉት ስድስት ወራት በውህደቱ የተደቀነበትን አደጋ ለመመከት ዝርዝር መርሃ ግብር አዘጋጅቶ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። መርሃ ግብሩ በዋናነት ሦስት ዓይነት የተግባር እርምጃዎችን ያካተተ ሲሆን ሦስቱም በተቀናጀ መልኩ ጎን ለጎን የሚተገበሩ ናቸው። በዚህ መልኩ ባለፉት ሰባት ወራት ውስጥ የኢህአዴግን ውህዳት ለማስተጓጎል ያላሳለሰ ጥረት አድርጓል።

ህወሓት በ2011 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ ተግባራዊ ያደረጋቸው ሦስቱ የተግባር እቅዶች የሚከተሉት ናቸው፡- 1ኛ) ኢህአዴግን እንደ አንድ መታገያ መድረክ መጠቀም፣ 2ኛ) ሕገ መንግስታዊ ወይም ህብረ ብሔራዊ የፌደራሊስቶች ግንባር መመስረት፣ እና 3ኛ) ለመጨረሻው ፍቺ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ናቸው። ሰሞኑን የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መቀሌ ላይ ስብሰባ እያደረገ ሲሆን ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ህወሓት የስብሰባውን መጀመር አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ማዕከላዊ ኮሚቴው “በህዝብ ህልውና” ላይ የተጋረጠውን አደጋ ገምግሞ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ተገልጿል። በተጨባጭ በትግራይ ሆነ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የተጋረጠ የህልውና አደጋ የለም። ከዚያ ይልቅ ቀጥተኛ የሆነ የህልውና አደጋ የተጋረጠበት ህወሓትና ህወሓት ብቻ ነው። ምክንያቱም ህወሓት ከሰባት ወራት በፊት ወይን መፅሄት ላይ ባወጣው ፅሁፍ መሰረት የኢህአዴግ ውህደት ቀጥተኛ የሆነ የህልውና አደጋ አንደሆነ ገልጿል። ስለዚህ በሰሞኑ ስብሰባ ማዕከላዊ ኮሚቴው ከላይ የተጠቀሱትን ሦስት ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀምና ውጤት ገምግሞ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። “የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በቀጣይ ቀናት ምን ዓይነት ውሳኔዎች ሊያሳልፍ ይችላል?” ለሚለው ህወሓት የኢህአዴግን ውህደት ለመመከት ያስቀመጣቸውን ሦስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች እና አፈፃፀም በዝርዝር ማየት ያስፈልጋል።

1ኛ) ኢህአዴግን እንደ አንድ መታገያ መድረክ መጠቀም

ህወሓት ውህደቱን ለመመከት ያስቀመጠው የመጀመሪያ አቅጣጫ ኢህአዴግን እንደ መታገያ መድረክ መጠቀም ነው። ኢህአዴግ የአመራር ለውጥ ካደረገበት ግዜ ጀምሮ ህወሓት እንደ አባል ድርጅት በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባዎች ሆነ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቢኔ ውስጥ ተሳታፊ እንደሆነ ይታወቃል። በእርግጥ አብዛኞቹ የህወሓት አመራሮች የተጣለባቸውን ሥራና ኃላፊነት በአግባቡ ከመወጣት ይልቅ የኢህአዴግን ውህደት በማደናቀፍ ተግባር የተሰማሩ ናቸው። በፌደራልና ክልል ደረጃ የሚገኙ የህወሓት አባላትና አመራሮች የኢህአዴግን ውህደት ለመመከት የሚከተሉትን አቅጣጫ አስመልክቶ ህወሓት ወይን በተሰኘው መፅሔት ባወጣው ፅሁፍ ገፅ 38 ላይ እንዲህ ገልፆታል፡-

“በአሁኑ ሰዓት በተነሳው ወሳኝ ጉዳይ ማለትም አንድ ውሁድ ፓርቲን በሚመለከትም እስከ ሄደበት ድረስ ሁለትና ሶስት የሚሆኑ መታገያ አቅጣጫዎች ይዘን እንደ መድረክ እንጠቀምበት፡፡ በዚህ መሰረት አንደኛው የኢህአዴግ ችግር በዋናነት የአደረጃጀት ችግር ሳይሆን የአስተሳሰብ ነው፣ በመሆኑም ይሄንን ማዕከል ያደረገ ትግልና ማስተካከያ ይኑረን፣ የአስተሳሰብ ሪፎርምን ዋናው ጉዳይ እናድርግ በሚል መስራት፡፡ አንድ ውሁድ ፓርቲን በሚመለከት ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ ውህደት የራሱ ሳይንስ፣ መርህና አካሄድ እንዳለው፣ እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይፈፀሙ የሚመሰረት ውህድ ፓርቲ የትም እንደማይደርስ መግለፅ ነው። ስለዚህ ወደዚህ አሰራር መግባትና መጀመር እንደሚያስፈልግ በመግለፅ ህወሓት ደግሞ ለዚህ ዝግጁ መሆኑን ማሳየት፡፡
ከዚህ ጎን ለጎን የያዝነውን አቋም ለመላ አባሎች፣ አመራርና የኢህአዴግ ካድሬ፣ ለመላ የህወሓት አባሎችና አመራሮች፣ ለመላ የኢትዮጵያ ህዝቦች በተለይ ደግሞ ለመላ የትግራይ ህዝብ እንዲሁም ለዓለም ለማሳወቅ በፅሑፎች ላይ የተመሰረተ ውይይት፣ ክርክር፣ በሚድያ በሁሉም ቋንቋዎች ይፋዊ የሆነ ትግል ማካሄድ፡፡
…..በሌላ በኩል ይህ በኢህአዴግ ውስጥ እየቀጠለ አጋር ድርጅቶች የየብሄራቸውና ብሄረሰባቸውን ፓርቲ ይዘው ድምፅ እንዲኖራቸው የሚያስችል መጠነኛ የሕገ ደንብ ማስተካከያ አድርገን “ይግቡ” ብለን ለማንነት ፖለቲካ በዋናነት ደግሞ ራስን በራስ ለመወሰን መብት የሚታገሉ፣ የዜግነት ፖለቲካን የሚቃወሙ ሃይሎችን አንድ ላይ ማሰባሰብ። ይህ ደግሞ የብሄርና የብሄረሰቦች የበላይነት ያለው ግንባር የምናደርግበት እድል የሚያሰፋ አቅጣጫ ይዘን እንታገል።”ከላይ በተገለፀው መሰረት መርሃ ግብሩ ተግባራዊ ከሆነበት ግዜ አንስቶ ህወሓት መስራችና አባል የሆነበትን ኢህአዴግ እንደ መታገያ መድረክ በመጠቀም፤ በአባል ድርጅቶችና አመራሮች መካከል የአቋምና አመለካከት ልዩነት ለመፍጠር ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፣ ውህደቱ እውን እንዳይሆን በኢህአዴግ ካድሬዎች፣ በህወሓት አባላትና አመራሮች፣ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና የዓለም አቀፉ ማህብረሰብ ዘንድ አፍራሽ ቅስቀሳ አድርጓል። ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ የውይይት መድረኮችና ሚዲያዎች ተመሳሳይ እንቅስቃሴ አድርጓል። በመጨረሻም ኢህአዴግን እንደ መታገያ መድረክ በመጠቀም በአዲሱ አመራርና አጋር ድርጅቶች መካከል ልዩነት በመፍጠር ውህደቱን ለማደናቀፍ ጥረት አድርጓል።

103641871 1855312385ህወሓት ይህን ሁሉ አፍራሽ እንቅስቃሴ ቢያደርግም ኢህአዴግ ውህደቱን ለማጠናቀቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ስለዚህ ህወሓት ኢህአዴግን እንደ መታገያ መድረክ ሲያደርግ የነበረው አፍራሽ እንቅስቃሴ የሚፈለገውን ውጤት አላመጣም። ኢህአዴግ ውስጥ የጌራቸው አሰፋ ጉዳይ አስፈፃሚ የሆነው ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ስለ ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ የሰጠው አስተያየት ይህን ያሳያል።

2ኛ) የፌደራሊስቶች ህብረት/ግንባር መፍጠር

የኢህአዴግን ውህደት ለማደናቀፍ ህወሓት የነደፈው ሁለተኛ ስልት ከፌደራሊስት ኃይሎች ጋር ህብረት መመስረት ነው። ወይን መፅሔት በወጣው ፅኁፍ ኢህአዴግን እንደ መታገያ መድረክ በመጠቀም የሚደረገው እንቅስቃሴ ውህደቱን ጨርሶ ሊያስቆመው እንደማይችል ይገልፃል። በመሆኑም ውህደቱ እውን ሲሆን ህወሓት ለብቻው ተነጥሎ እንዳይቀር የፌደራሊስት እና ሕገ መንግስቱን የሚቀበሉ ሃይሎችን በማጠናከር የኢህአዴግ ተቀናቃኝ ግንባር መፍጠር እንዳለበት እንዲህ ሲል አቅጣጫ አስቀምጧል፡-“ሁለተኛው እና ከዚህ ከላይ ከተገለጠው መታገያ አቅጣጫችን ጎን ለጎን በጥብቅ መስራት ያለብንና አሁንም ባለፈውም የወሰንነውንና ስራውም የተጀማመረውን፣ ፌደራሊስት እና ሕገ መንግስቱን የሚቀበሉ ሃይሎችን ጉዳይ ማጠናከር ነው፡፡ …ብሄራዊ አደረጃጀትን የሚያጠፋ የአገር አቀፍ ውሁድ ፓርቲ አደረጃጀት እስከ መካከለኛው ዘመን ድረስ ተቀባይነት የለውም፡፡ ይህ እስከሆነ ድረስ ብሄርን መሰረት ካደረገ አገራዊ ጥምረት፣ ግንባር ወይም ህብረት ውጭ ውሁድ የሚባል ፓርቲ ሊኖር አይችልም፡፡ በመሆኑም በዚህ አገር እስካለን ድረስ ኢህአዴግ እየተቀበረ ስለሆነ ቶሎ ብለን በብሄራዊ ድርጅቶች ላይ መሰረት ያደረገ አገራዊ መድረክ፣ መታገል ይኖርብናል። በመሆኑም ከዚህ ውጭ በኢህአዴግ ስም የሚደረግ የአንድ አገር አቀፍ ውሁድ ፓርቲ ምስረታን ሙሉ በሙሉ ተቃውመን መቆም እና ለህብረ ብሄራዊ ፌደራሊዝም ስኬት መዋጋት ብቻ ነው ያለብን፡፡
…[ይሁን እንጂ] ኢህአዴግን ወደ አንድ ውሁድ ፓርቲ ልቀይረው ነው’ እያለ ያለው ሃይል፣ ከላይ [አንደኛ] የተገለፀውን የመታገያ አቅጣጫ ይዘን ብንዋጋም የተወሰነ ጊዜ ቢሰጠን ነው እንጂ የያዘውን መደብ ይተገብራል፡፡ ያ በሚሆንበት ጊዜ እኛ ወደ ውሁዱ ፓርቲ ልንገባ አንችልም፡፡ [ውህደቱን ብንቀላቀል] ለአብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ ለህዝቦች በተለይ ደግሞ ለትግራይ ህዝብ ትግል ትልቅ ክህደት [ይሆናል]። ኢህአዴግ ሲቀበር የራሳችንን የተሟላ አማራጭ ይዘን ከውህደቱ ራሳችንን አግልለን ነው የምንቀጥለው፡፡ በዚህ ወቅት ቶሎ ግንባር ፈጥረን አማራጭ ፓርቲ ይዘን ልንቆይ ይገባናል፡፡ እነዚህ ሃይሎች ደግሞ ሕገ-መንግስቱን የሚቀበሉ ፌደራሊስት ሃይሎች ናቸው፡፡ ራስህን አግልለህ መቆየት ምናልባት የበለጠ የሚሆንበት ሁኔታ ካለ እየተከታተልን የሚታይ ይሆናል።”ቀደም ሲል አንደኛ ላይ በተገለፀው መሰረት ኢህአዴግን እንደ መታገያ መድረክ በመጠቀም ውህደቱን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት አላመጣም። በተመሳሳይ ህዝባዊ ድጋፍና ተቀባይነት ቀርቶ በግልፅ የሚታወቅ አባላትና አመራሮች የሌላቸውን የይስሙላ “ፓርቲዎች” እና እንደ አየለ ጫሚሶ፣ ትግዕሰቱ አወል፣ በቀለ ገርባ እና የመሳሰሉ ሰዎችን መቀሌ ድረስ በመጥራት የፌደራሊስቶች ግንባር ለመመስረት ያደረገው ጥረት በህዝብ ዘንድ መሳቂያ-መሳለቂያ ለመሆን የዘለለ ውጤት አላመጣም። ስለዚህ ህወሓት ከመጋቢት 2011 ዓ.ም ጀምሮ የኢህአዴግን ውህደት ለማስተጓጎል ሲከተላቸው የነበሩት ሁለት የመታገያ አቅጣጫዎች የሚፈለገውን ውጤት አላመጡም።

3ኛ) ለመጨረሻው ፍቺ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ

ወይን መፅሔት “በኢትዮጵያ አገር አቀፍ የተዋሃደ ፓርቲ ጥያቄ ለምን?” በሚል ርዕስ ባወጣው ፅሁፍ መሰረት ቀደም ሲል የተጠቀሱት የመታገያ አቅጣጫዎች ውጤት ካላመጡ የኢህአዴግ ውህደት ዕውን ይሆናል። በሌላ በኩል የኢህአዴግ ተልዕኮና ዓላማ ከፓርቲው አልፎ የኢትዮጵያን አንድነትና የህዝቦቿን ሰላም ይወስናል። በመሰረቱ እንደ ህወሓት አገላለፅ ኢህአዴግ ከሌለ ኢትዮጵያ እንደምትበታተን እና ህዝቦቿም በጦርነት ምክንያት ለዕልቂት እንደሚዳረጉ ከላይ በተጠቀሰው ፅሁፍ ገፅ 13 እና 29 ላይ በዝርዝር ተገልጿል።

በእርግጥ ይህ ህወሓት መቀሌ ከገባ በኋላ ያስቀመጠው አቅጣጫ ሳይሆን የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ከተመሰረተበት ዕለት አንስቶ ሲመራበት ነበር። በወይን መፅሔት ላይ የወጣው ፅሁፍ “የአብዮታዊ ዴሞክራስያዊ ስርዓት ምንነት” የሚለውን መፅሃፍ ዋቢ በማድረግ የኢህአዴግ ዓላማና ተልዕኮ ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ በተለየ መልኩ የሀገርን ህልውና እና የህዝቦችን መፃኢ ዕድል የሚወስን እንደሆነ ይገልፃል። እንደ ህወሓት አገላለፅ፣ ኢትዮጵያን ከመበታተንና ህዝቦቿን ከመተላለቅ ሊታደጋቸው የሚችለው ኢህአዴግ ብቻ ነው። ስለዚህ የኢህአዴግ ውህደት እውን የሚሆን ከሆነ የሀገሪቱ መበታተን አይቀሬ ነው። በመሆኑም ህወሓት ያስቀመጠው ሦስተኛው አቅጣጫ የመጨረሻውን ፍቺ ለመፈፀም ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ነው፡-“ህዝባዊና አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ የሆነውን ይህን አቋም ይዘን ፊት ለፊት ስንገጥማቸው ወይ ደግሞ ይሄ የመፍትሄ ሃሳብ ሳይሳካ ቀርቶ የአገር መበተን ካስከተለ ባለፉት ፅሑፎቻችንም የለየናቸው ከባድ ጫና፣ ፖለቲካዊ፣ ሕጋዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ከዚያም ከፍ ብሎ የፀጥታ አደጋዎችም ከሁሉም አቅጣጫዎች ሊመጡ ይችላሉ፡፡ በተለይ የመጨረሻው ፍቺ ይህንን ጉዳይ ሊያፋጥነው ይችላል፡፡ አይሆንም ላለ ሁሉም “እምቢተኛ ነው፣ ሀገር በታኝ ነው…” ከሚል ጀምሮ እስከ ማገድ የሚሄድና ሌሎች አደጋዎችም ሊመጡ ይችላሉ፡፡ ይህ አደጋ ብቻ ግን አይሆንም፤ የትግል ዕድሎችም ይፈጠራሉ፡፡ በህዝባችንና በድርጅታችን ጉልህ መጠናከር በኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የተሻለ ተነፃፃሪ መነሳሳት፣ እንዲሁም በሕገ-መንግስትና ፌደራሊስት፣…ወዘተ ሰልፍ ለይቶ ትግልና መተናነቅ የሚፈጠርበት ሂደትም ይሆናል፡፡
….ያም ሆነ ይህ ግን ፈተናዎችንና አደጋዎችን ለመከላከል ዕድሎችን መጠቀምና ማስፋት አሁንም በጥንካሬያችን፣ በመርህ ላይ በተመሰረተ አንድነታችንና ፅናታችን ላይ ብቻ የሚንጠለጠል ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ዕድገቶች ግምት ውስጥ በማስገባት አጠቃላይ የፖለቲካዊ፣ የፀጥታና ኢኮኖሚያዊ ዝግጅቶቻችንን በተለይ ደግሞ በንቃት የሚቆም ወጣት ከመፍጠር ጎን ለጎን የፀጥታ ዝግጅታችንን መልሶ በጥልቀትና በዝርዝር መፈተሽ ያስፈልጋል፡፡”የኢህአዴግን ውህደት በበላይነት ከሚመሩት አንድ ክፍተኛ ባለስልጣን በሰጡኝ መረጃ መሰረት አምስቱ አጋር ድርጅቶች እና ሦስቱ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በመዋሃድ “የኢትዮጵያ ብልፅግና ፓርቲ” ለመመስረት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ናቸው። የኢትዮጵያ ብልፅግና ፓርቲ (ኢብፓ) ምስረታ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባርን (ኢህአዴግ) ሙሉ በሙሉ ያፈርሰዋል። ከዚህ በተጨማሪ አዲሱ ፓርቲ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚለውን አቅጣጫ ያለፈበት የህወሓቶች የጭቆና መሳሪያ እንደሆነ ከላይ የተጠቀሱት ባለስልጣን ነግረውኛል። በሌላ በኩል ህወሓቶች የውህደቱ አካል እንደማይሆኑ በፅሁፍ ጭምር መግለፃቸው ተሰምቷል።

በዚህ መሰረት አዴፓ፣ ኦዴፓ. ደህዴን እና አምስቱ አጋር ድርጅቶች ተዋህደው አዲሱን ፓርቲ ሲመሰርቱ የኢህአዴግ መስራችና ባለቤት የነበረው ህወሓት ለብቻው ተነጥሎ መቅረቱ እርግጥ ሆኗል። ምክንያቱም፣ አንደኛ፡- ኢህአዴግን መታገያ መድረክ በመጠቀም ያደረገው ሙከራ ውጤት አላመጣም። ሁለተኛ፡- ከህገ መንግስት ወይም ፌደራሊስት ኃይሎች ጋር ግንባር መፍጠር አልቻሉም። ስለዚህ ህወሓት የቀረው ብቸኛ አማራጭ የመጨረሻውን ፍቺ ለመፈፀም ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ነው። ይህ ደግሞ ከላይ በተጠቀሰው መሰረት የትግራይ ክልልን መገንጠልና ይህን ተከትሎ ለሚመጣው አደጋ ራሱን ማዘጋጀት ነው።

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መቀሌ ላይ ስብሰባ የተቀመጠው ድርጅቱ ካስቀመጣቸው ሦስት አማራጮች ውስጥ አንዱን ብቻ ይዞ ነው። ከላይ በተጠቀሰው መሰረት ህወሓት የቀረው ብቸኛ አማራጭ ራሱንና የክልሉን ህዝብ አጠናክሮ እና በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚገኙ የብሔር ቡድኖች በማነሳሳት “ትግልና መተናነቅ” ነው። በዚህ ምክንያት “የሀገር መበተን ካስከተለ” በሚል ከባድ ጫና፣ ፖለቲካዊ፣ ሕጋዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ከዚያም አልፎ “ከሁሉም አቅጣጫ የፀጥታ አደጋዎች” ሊከሰቱ እንደሚችሉ በመለየት ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል። በአጠቃላይ ህወሓት ከኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያም ጭምር የመጨረሻውን ፍቺ ለማድረግ ተዘጋጅቷል።

ህወሓት በሁሉም አቅጣጫ ሊያጋጥሙኝ ይችላሉ በሚል ከሚያደርጋቸው ቅድመ ዝግጅቶች አንዱ የቴሌኮሚኒኬሽን ግንኙነት መስመር ነው። በዚህ ረገድ ህወሓት ከኢትዮቴሌኮም ሰርቨር ጋር የሚያገናኘውን መስመር በመቀየር በሁመራ በኩል የፋይበር ኦፕቲክ ኬብል በመዘርጋት በሱዳን በኩል ከዓለም አቀፉ የኢንተርኔት ግንኙነት መስመር ጋር ለማገናኘት ጫፍ ላይ ደርሶ ነበር። ሆኖም ግን በመጨረሻ ሰዓት የፌደራሉ ደህንነት መስሪያ ቤት ጉዳዩን ደርሶበት የግንኙነት መስመሩን እንደቆረጠው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የመንግስት ኃላፊ በቅርቡ አጫውቶኛል። በተመሳሳይ የመጨረሻው ፍቺ ከተፈፀመ በኋላ የሚገጥመውን የውጪ ምንዛሬ ከግምት በማስገባት ዶላርና ዮሮ በከፍተኛ የምንዛሬ ዋጋ እየገዛ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል በአማራና የቅማንት ማህብረሰብ፣ በአማራ ክልል የኦሮሞ ማህብረሰብ በሚኖርባቸው አከባቢዎች፣ እንዲሁም በኦሮሚያና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አከባቢዎች የሚታዩ ህገወጥ ተግባራት በሙሉ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የህወሓት ቅድመ ዝግጅት አካል ናቸው።

በአጠቃላይ ህወሓት ከኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያም ጋር የመጨረሻውን ፍቺ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅቱን ከሞላ ጎደል አጠናቅቋል። የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መቀሌ ላይ በሚያደርገው ስብሰባ ድርጅቱ ለመጨረሻው ፍቺ የተደረገውን ቅድመ ዝግጅት ገምግሞ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። ህወሓት የመጨረሻውን ፍቺ ለመፈፀምና ከሁሉም አቅጣጫዎች የሚገጥሙትን አደጋዎች ለመከላከል ቅድመ ዝግጅት አድርጓል ሲባል በአጭሩ “ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስና ለማተራመስ ዝግጅቱን ጨርሷል” እንደማለት ነው። የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ መሰረት ስብሰባው አራት ቀናት እንደሚፈጅ ተገልጿል። ስለዚህ ከሁለት ቀናት በኋላ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ይወስናል!

9 Comments

  1. what are you talking about? The very evil mission of destroying the country is already being done by ODP together with its dangerously extreme Oromo political elements and anarchist youth movement (Qeerro).
    Don’t you get bored or tired of singing the song about blaming only TPLF? Can’t you see what is going on in the country particularly these very days? Why don’t you decry the very dangerously stupid way of doing politics by the very government and ruling party of the Prime Minister who claimed winning of the Nobel Prize? Don’t you feel this is a very disgraceful situation not to those no-shame politicians of ODP/OLF/EPRDF but also to the very people of Ethiopia ? Don’t you have a sense of observation about the dehumanization of the people when on the one hand being told to be proud of the Prize , and being victimizes the government and the ruling party led by the Prize winner on the other hand ? I could go on and on .But as the notoriously ugly and dangerous ways of doing politics by not simply the ordinary cadres and anarchists but sadly enough by the government and ruling circle of the Prime Minister himself are countless , the points I mentioned are quite enough to a person whose mind and heart are open for good.

  2. This is not news, Teshome. We new this a long time ago. The news is what the galas are doing. Do not you think blocking roads at Gohatsion and Debrebrehan is a sign for the creation of tomorrow’s gala land. You should have written on this subject, in particular about what the savage gala youth did during the last 72 h.

  3. This is old woyane and white people think about Ethiopia!Now the ODP started the process! No one can do it! woyane based and related party’s will be destroyed soon! Ethiopia is Ethiopia! Ethiopia can stay and will countinuing without leaders! is ther any true ledear for the last 35 years in the country? no one!100%!!! But Ethiopia is still Ethiopia!!! Evil thinkers are always disturbe the people! We may kill each other! But Ethiopia is Ethiopia! Woyane still tried alot and can try everything to do evil activities by using cheated mony from poor Ethiopians! But at the end, Woyane will receive what is appropriate!

  4. Go to hell.What are you saying.Oromo is an Ethiopian,working day and night to bring this country forward. You, Amara and Tigre, know what you had been doning in Ethiopia for the last 150 years. You never come to power again in Ethiopia. Oromia and Tigray will never be under the rule of NEFTEGNA.

  5. Now TPLF wants to be same as what EPLF SHABIYA was between 06-1991 upto 06/1998, those unbearable seven years of Woyane and SHABIYA mismatched marriage with uneven unfair unrealistic governance that has destroyed Ethiopia because Woyane and shabiya followed an ideology of “what is Ethiopia’s belongs to Eritrea and Ethiopia, while what is Eritrea’s belongs to only Eritrea” ideology.

    Now TPLF wants to say “what is Ethiopia’s belongs to Tigray and the rest of Ethiopia , but what is Tigray’s belongs only Tigray”.

    Ethiopian government in early 1998 was best friends with the Eritrean government. Within a matter of few months Eritrean government became worst enemies with the Ethiopian government.
    Unless the core reason of the Ethio-Eritrean war is adressed not one but hundreds of peace prizes do not bring lasting peace between the two countries. Both sides need to figure out what it was that turned the best of friends relationship they had into the worst of enemies that quick , then both countries leaders must instill in themselves and in their whole countries people to do a conscious effort for the reason that brought the Ethio Eritean war doesn’t happen again.

    Sugar-coating the real reason of why the Ethio-Eritrean war started, by saying the reason was the two cousins family feud (Meles Zenawi’s and Isayas Afeworki’s) personal feud war or border war over Badme, is not the way peace is achieved.

    The real truth of why the Ethio-Eritrean war started need to be addressed.

  6. It is very important to be aware of the truth that the TPLF has two plans, Plan A and plan B.
    Plan A is to cling to power in Ethiopia at any cost by implementing its divide and rule politics.
    Plan B is if plan A fails, the TPLF will fall back to its plan B which is declaring the indpendence of the republic of TIgray. In fact, the TPLF has been pursuing these plans in parallel. Instigating turmoil and chaos in the rest of Ethiopia is part of the plan because the TPLF leaders wrongly believe that it is of crucial importance for safety and security of Tigray. The TPLF is working to mobilize some short sighted Oromo nationalists for its puropse of destablization. It has both the financial resources and astuteness to lure these Oromo nationalists.

  7. ኢትዮጵያን የሚጠብቃት አምላክ አይተኛም አያንቀላፋም፡፡ 24 ሰዓት በሙሉ በሥራ ላይ ነው፡፡ ስለዚህ የጠላት ዲያብሎስን ዕቅድ አይሳካም፡፡

  8. I don’t think TPLF will divorce. If it does, TPLF can’t be sure what it did to Eritrean Ethiopians which shocked Addis Ababans could not happen again. Besides, the money TPLF is wasting in the past year alone on bandits who burn churches and kill people is already being felt since robbing banks was stopped. And there is the cases of land taken from Gondar and Wollo which will guarantee war once the unilateral divorce takes place. Also they are in the minority right now, there are thousands of Tigrayans who never liked TPLF to begin with and tens of thousands more who learned to hate it.

    Shunned but not shy, those people will destroy TPLF in less than a year because they don’t share the ideology, the abuse of power and the crimes commited and the guilt. Some of the outspoken will garner support overnight and as always TPLF will split and join the outspoken like it always does. And we’ll all pretend TPLF never happened. For another 50 years that is.

  9. TPLF ህብረተሰብንና መንግስትን (State) እንደማዋቀርና ሀገሪቱን እንደማበልፀግ ይልቅ፣ ቀና-በጎ አስተሳሰብ ያላቸውን የገዛ ሃገሪቱ ልጆችዋን በማባረርና፣ ከውጭ አገሪቱን የመዝረፍ ፍላጎት ካላቸው ሃይሎች ጋራ ብቻ በመተቃቀፍ ሃገራችች የመዝረፍ ተግባራት ላይ ሲንደፋደፍ፣ በሌሎች ሃይሎች ስልጣኑ ተወስዶበት ሲያበቃ፣ ይሄው ችግር ውስጥ ገብቶ ይገኛል:: ችግር ውስጥ የከተተው ራሱን ብቻ ሆኖ ቢኖር ኖሮ፣ ችግሩ ቀለል ያለ ይሆን ነበር:: ችግር ውስጥ የገቡት ግን “ዘላለሙን” Geisel ውስጥ የሚገኘው የትግራይ ህዝብ እና እንዲሁም መላ ኢትዮጵያ ሆነው ይገኛሉ! በዚህን ጊዜ TPLF የትግራይ ህዝብ ላይ ከሌሎች የመጣ አደጋ እንዳለ ብቻ ነው መናገር የሚፈልገው:: በርግጥ ከላይ እንዳልኩት የትግራይ ህዝብም አደጋ ላይ ወድቆ ይገኛል:: TPLF ግን ለተከሰቱት አደጋዎች እንደ ዋናው መነሾ እርሱው መሆኑን መስማት አይፈልግም:: እርሱው አስፈላጊነት እንዳለውና፣ ይሄ አስፈላጊነቱ ተቀባይነት ካላገኘ የመገንጠል ምርጫዎችንም እንደሚያመጣ ያስተጋባል:: ይሄ አስተሳሰብ ግን የበለጠ ችግሮችን ከማስከተሉ በስተቀር የሚያመጣው ፋይዳ የለውም:: እኔ ኣኽሱም ከላሊበላ እንዲሁም ዓድዎ ከጎንደር ተለይቶ የሚመጣ መፍትሄ ምን ጊዜም አይመጣም ባይ ነኝ:: ከዚያም በላይ ደግሞ በግሎባላይዘሽን ክፍለ ዘመናት ጊዜ አለሙ በሙሉ በመቀራረብና በመተቃቀፍ ተግባራት ላይ በሚገኝበት ጊዝያቶች፣ እኛ አካባቢ ግን እንደ “ሻሸመኔን ከአዋሳ ወይንም ደግሞ ዓድዋን ከኣኽሱም ለማስገንጥልና ነፃነትን ለመጎናፀፍ” አይነት ተግባራት ላይ መገኘት simply DESTRUCTIVE ከመሆን ሌላ የበጀ ፋይዳ የለውም::
    ስለሆነም የ’DESTRUCTIVE ስሜት እና ፍላጎት ለሌላቸው መላ ኢትዮጵያውያን የሚቀርበው ጥያቄ፣ ይሄ ራሱው ካመጣው መወጠር የተነሳ በ’DESTRUCTIVE ተግባራት ላይ ብቻ ለመቀጠል የተነሳውን TPLF’ን በምን አይነት Therapy እንተባበረው፣ ባጠቃላይስ ህብረተሰባችንን እንዴት አድርገን በሰላም ይኖር ዘንዳ እንንከባከበው፣ አይደለምን እንዴ የመንደርደርያ ሃሳብ መሆን የሚገባው!?

Comments are closed.

Previous Story

ግልፅ ደብዳቤ ለክቡር ዶ/ር ዓብይ ኣሕመድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር – መርስዔ ኪዳን

Next Story

“እያረሙ እንጅ እያበዱ” ላለመሄድ ከራስ መጀመርን ይጠይቃል – ጠገናው ጎሹ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop