November 28, 2018
4 mins read

የአቶ ሌንጮ ለታ ፓርቲ ከኦዴፓ ጋር ተዋሃደ

በአቶ ሌንጮ ለታ የሚመራው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) እና የቀድሞው ኦህዴድ የአሁኑ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ(ኦዴፓ) ጋር ተዋሃዱ።

የሁለቱ ፓርቲዎች አመራሮች ዛሬ ከቀትር በኋላ በኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ቢሮ የውህደት ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡ ተዋህደው በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙት ከኦዴፓ አቶ ለማ መገርሳ ናቸው፡፡

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት እና የኦዴፓ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ፤ ”በአንድ አዕምሮ እና ልብ ለመስራት ከስምምነት ላይ ደርሰናል። ኦዴፓ በወጣቶች የተሞላ ፓርቲ ነው። ከኦዴግ ጋር ስንዋሃድ ጠንካራ ተቋም ይወጣናል” ብለዋል። የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር አመራሮች ወደ ሃገር ከመምጣታቸው በፊት ”ሲረዱን” ነበር ያሉት ፕሬዚዳንት ለማ፤ አብረን ለመስራት እድሉን ስላገኘን ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።

”ለአንድ ኦሮሞ ህዝብ ከ10 በላይ ሆነን ከምንታገል፤ ከእኛ ጋር አንድ አይነት ዓላማ እና ሰልት የሚከተሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን መጥተው ቢቀላቀሉን አሁንም ለመቀበል ዝግጁ ነን። ይህም ለኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን ለሃገርም ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው።” ብለዋል።

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ሌንጮ ለታ በበኩላቸው ”የመበታተን ባህል ወደ ችግር እና ድህነት ነው የሚወስደን” ብለዋል። አቶ ሌንጮ ጨምረው ”ዛሬ ላይ የፓርቲዎች ውህደት ብቻ ሳይሆን የህዝብ አንድነት ጭምር ያስፈልገናል፤ የኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ሳይሆን እንደዛሬ ነው ማሰብ ያለብን” ሲሉ ተናግረዋል።

የኦዴፓ የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ስምምነቱን አስመልከቶ እንደተናገሩት ሁለቱ ፓርቲዎች የኦሮሞ ህዝብ አንድ እንዲሆኑ ባቀረበላቸው ጥሪ መሰረት ሊዋሃዱ ችለዋል፡፡ ‹‹የኦሮሞ ህዝብ ለፓርቲዎቹ አመራሮች አንድ ሆናችው ወደ እኛ መምጣት አለባችሁ የሚል መልዕክት አስተላልፏል›› ያሉት አቶ አዲሱ ኦዴፓ ከኦዴግ ጋር የህገ ደንብ፣ የስትራቴጂ እና የፕሮግራም ልዩነት የሌለው በመሆኑ በጋራ ለመስራት እንደማያስቸግረው ጠቁመዋል፡፡ በዛሬ የስምምነት ሰነዱ ቢፈረምም ወደፊት ከሁለቱ ፓርቲዎች ቴክኒካል ኮሚቴ ተቋቁሞ በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት የኦቦ ሌንጮ ለታ ኦዴግ ቀደም ሲልም ከኦዴፓ ጋር መስራት ጀምሯል:: ወደ ሃገር ቤት ከገቡት አመራሮቹ መካከልም ሹመት አግኝተው እየሰሩ አሉ::
ሌንጮ ባለፈው ሳምንት በፓርቲ አመራርነት እንደማይቀጥሉ ሆኖም ግን ከፖለቲካው ዓለም ሕይወታቸው እስከሚያልፍ እንደሚቀጥሉ መግለጻቸው ይታወሳል::

ዶ/ር አብይ አህመድ ትናንት ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ሰማንያ አንዱ ፓርቲዎች ወደ ሦስት እና አራት ተዋህደው ዝቅ እንዲሉ ጥሪ ማቅረባቸውን ዘግበናል::
https://www.youtube.com/watch?v=DKNGEfUvzgA

92797
Previous Story

ሰባት ህንዳዊያን ኢትዮጵያ ውስጥ ታግተናል አሉ

92808
Next Story

በታጣቂዎች ለተገደሉ የኦሮሚያ ፖሊስ አባላት ሽኝት ተደረገላቸው | ኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ በኦሮሚያ ጸጥታ ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጠ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop