ውሳኔ-ሕዝበ የሚያስፈልጋቸው ብሔራዊ ጉዳዮች – ተፈራ ድንበሩ

የመላውን አገር ሕዝብ የሚመለከቱ ጉዳዮች መወሰን ያለባቸው በራሱ በባለቤቱ በመላው ሕዝብ ነው። ዲሞክራሲ ባለበት አገር ሕዝብ የሚመራበት ሕገመንግሥት በሕዝብ ፈቃድ ይወሰናል። የመሬት ይዞታ፤ መሪ ሥር ዓተ-ትምህርት፣ ብሔራዊ ቋንቋ፣ የአገር አከላለል፣… ወዘተ በቀጥታ በሕዝብ ፍላጎት መወሰን ያለባቸው ዋናዋና የአገር ጉዳዮች ናቸው።

ይህ ጽሑፍ የወቅቱና ምን ጊዜም መነጋገሪያ የሆኑትን የአሰብ የባህር በር፣ ተጨማሪ ብሔራዊ የኢትዮጵያ ቋንቋንና የአዲስ አበባ ክፍለሀገርን አከላለል ይመለከታል።

የአሰብ በር የአገራችን ጉዳይ ነው፤ ይህ ብሔራዊ በራችን ነው፤ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ   ክልል እውን ዲሞክራሲያዊ ሆኖ ክልሎች ራሳቸውን በራሳቸው ሲያስተዳድሩ ለአገር ውስጥ ምርትና ለውጭ ንግድ መውጫ በር ያስፈልጋቸዋል። “ድንቢጥ ብታልም ጥሬዋን” እንደተባለው አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ አመራር አሰብን አሳልፎ መስጠቱ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ያልቆመ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሲሆን፣  የሥልጣን ሕልም የሚያልሙ ፖሊቲከኞችም ነገ የአገር ሥልጣን ላይ ቢወጡ የሕዝባቸውን ፍላጎት ለማሟላት ማጣፊያው ጠፍቶባቸው ሕዝቡ የባሰ ችግር ውስጥ እንዳይገባ በመገንዘብ ይህን ጉዳይ አጀንዳቸው አድርገው መሥራት ኢትዮጵያዊ ያደርጋቸዋል። ራስን ስለመቻል አስቀድሞ አለማስተዋል እንደ ኤርትራውያን የባሰውን መናጢ ሆኖ የኃያላንን መንግሥታት እጅ በማየት የአገርን መሠረታዊ ጥቅሞች አሳልፎ እስከ መስጠት ይዳርጋል። የኢትዮጵያ በሮች የነበሩት ጅቡቲና ዘይላ ታሪክ ሆነው ቀርተዋል፤ አገር በመለገስ መቀጠል አያዋጣንም፤ መተማም ሆነ አልፋሸጋ የጎንደር ብቻ እንዳልሆኑ ሁሉ የአሰብ ጉዳይም የዚህ ወይም የዚያ ክልል ጉዳይ ሳይሆን የክልሎች ሁሉ ጉዳይ ስለሆነ ይዋል ይደር እንጂ እንደእሳተገሞራ ታምቆ ቢቆይም ወደፊት መፈንዳቱ አይቀርም።

አሰብ ለኤርትራ የተሰጠው ሕዝቡ በነፃ ባልመረጠው ሕገወጥ መንግሥትና በሕገወጥ መንገድ ነው፤ የኤርትራ ጉዳይ በፌዴሬሽን ከመወሰኑ በፊት የተበበሩት መንግሥታት ኢትዮጵያ ታሪካዊው የባህር በር የሚያስፈልጋት መሆኑን አውቋል። እ ኤ አ በ1950 ዓም በተደረግ 316ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጉባኤ በውሳኔ ቁጥር 390 ገና ኤርትራ በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቀላቀል ውሳኔ ሲሰጥ የባህር በሯን በተመለከተ እንደሚከተለው አስቀምጧል፦

The rights and claims of Ethiopia based on geographical, historical, ethnic or             economic reasons, including in particular Ethiopia’s legitimate need for         adequate access to the sea

ከ1966 ዓም አብዮታዊ የመንግሥት ለውጥ በፊት አሰብ ከኤርትራ ተለይቶ እንደአንድ ጠቅላይ ግዛት ልዩ አስተዳደር ነበር። ከዚህ በተጨማሪ አንድ አገር የወንዝ ተፋሰስን በመለወጥ የጎረቤት አገር ሕዝብ ሕልውና እንዳይጎዳ በማለት የቪየናም ሆነ የሄልሰንኪ ኮንቨንሽንሽኖች ኢትዮጵያ በወንዞቿ የመጠቀም መብቷን የማይገቱ ቢሆንም አባይን ለማልት በምታደርገው ጥረት ላይ በየጊዜው ተጽዕኖ እንደተደረገባት ይታወቃል። በአንፃሩ የገዛ ባህር በሯን ተቀምታ በችግር ላይ እንድትወድቅ የሚያደርግ ምንም ሕግ የለም፤  የዓለም ኅብረተሰብ አመለካከትም አይደለም። ኤርትራም ሌላ የባህር በር ያላት ከመሆኑም በላይ አሰብን ልትጠቀምበት ስለማትችል ለእጅ አዙር ቅኝ ገዥዎች አሳልፋ መስጠቷም ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ስለሆነ ኢጋድም ይህን ጉዳይ እንደችግር አለማየቱ ይገርማል፤ ለነገሩ ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም ይባላል። የክልሉ አካል በሆነው በር ዝንታለም የኖረው የአፋር ሕዝብ መብት ተረግጦና ያለፍላጎቱ እንደፍልስጥ ኤም አገር እንደሌለው ተቆጥሮ በኤርትራና በኢትዮጵያ ለሁለት ተከፋፍሎ ጥንታዊ ማንነቱን እንዲያጣ ተደርጓል። አንድ የኢጣሊያ የንግድ ድርጅት አሰብ ላይ መሬት መግዛቱን ሰበብ በማድረግ ቀጥሎ ኢጣልያ ባንዲራዋን እንዳውለበለች ሁሉ ትግራይን ነፃ ለመውጣት በሚንቀሳቀስ ድርጅት ትግርኛ ተናጋሪ ወገን ሥራ ፍለጋ ሄዶ በእንግድነት የኖረበትን መሬት ለትግራይ በማካለል በሌላ በኩል በራሱ ምድር ላይ የነበረውን አፋር ከፋፍሎ የሁለት አገር አናሳ ማድረግ ፍትሐዊ አይደለም። ለውጭ ጠላቶች የእግር እሳት ሆኖ ዳርድንበሯን በመጠበቅ ኢትዮጵያን ካቆዩት ወገኖቻችን መካከል የአፋር  ሕዝብ ይገኝበታል። የስለሆነም በአሰብ ወደኤርትራ መካለል ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሕዝበ-ውሳኔ የፈቀዱት ስላይደለ አያቶቻችን ደማቸውንና አጥንታቸውን ከስክሰው ያቆዩት ታሪካዊ የባህር በራችን ስለሆነ ለአገራችን ሊመለስ ይገባል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሁሉ ሠው ያንብበው  እንዲነበብ ያድርግሐ

ሁለተኛ ኦሮሞ ተጨማሪ ብሔራዊ የኢትዮጵያ ቋንቋ እንዲሆን የሚደረግ ጥረት አለ። ለዚህ ድጋፍ በመኖሩ አንፃር ተቃውሞም ሊኖር እንደሚችል ማወቅ የሕዝብን ፍላጎት ማክበር ነው። የኦሮሞ ቋንቋ ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር ሲታይ ቁጥሩ ከፍ ያለ ይሁን እንጂ የአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ መግባቢያ ቋንቋ አይደለም። አንድ ቋንቋም ባሔራዊ ሆኖ እንዲያገለግል መንግሥት በቀጥታ የሚወስን ቢሆን የሕዝብን ፍላጎትና ሥልጣን መጋፋት ነው የሚሆነው። በመሠረቱ ጉዳዩ ከ80 ያላነሰ ቋንቋ የሚናገሩ ማህበረሰቦችን ሁሉ ይመለከታል። ስለሆነም ይህ መታየት ያለበት በአገር ደረጃ ነው ማለት ነው።  ስለቋንቋና ብሔራዊ መብት ሲነሣ አማርኛ ተናጋረውና ኦሮምኛ ተናጋሪው ብቻ ናቸው የአደባባይ መነጋገሪያ የሚሆኑት፤ ይህም ማለት ሌሎች ማህበረሰቦች መኖራቸውና  ፍላጎታቸው ሁሉ እንዳልነበረ የሚታይ ያስመስላል። ስሙን ለ”አፍሪቃ” ሰጥቷል የሚባለው ከክርስቶስ ልደት በፊት በቀይ ባህር አካባቢ የሠለጠነና መርከቦችን በመሥራት በአካባቢው መንግሥታት የንግድ ግንኙነት ታዋቂ የነበረው የአፋር ሕዝብ፣ እንዲሁም ዳሞት፤ ዛጉዌ፣ ሐዲያ፣ ከፋ፣ ሲዳማ፣ ወላይታ፣ … ወዘተ ግዙፍ ታሪክ ካላቸው ማህበረሰቦች መካከል ጥቂቶቹ ሲሆኑ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ ክስተቶች በአስከተሏቸው ፍልሰቶች እንዲሁም በጋብቻና በሌሎች ማህበራዊ ትሥሥሮች ወይም ማኅበራዊ መስተጋብሮች ዝግመታዊ ለውጦች ኢትዮጵያውያንን አሁን ባሉበት ደረጃ እንዲገኙ አድርጓቸዋል። ሁሉም ወግ፣ ባህልና ከነዚህ ጋር የሚሄዱ እሴቶችና ጥቅሞቻቸው እንዲከበርላቸው መፈለጋቸው የማያጠያይቅ ሲሆን እንዲህ ያለ ለውጥ እነሱንም ይመለከታል። ማህበረሰቦቹ እያንዳንዳቸው የየራሳቸው ቋንቋ ቢያድግላቸው ወይም መግባቢያ ቢሆንላቸው አይፈልጉም ማለት አይደለም፤ ሆኖም መክረው፣ ዘክረው በሕዝበ-ውሳኔ የፈጸሙት ነገር ቢያንስ ሕጋዊ ነው። ነገር ግን ይህን ሕጋዊነት ባለመከተል የሚፈጸም ውሳኔ የማያባራ ንትርክና ውዝግብ በማስከተል አንድነታችንን የሚጎዳ ቀዳዳ ሊከፍት ይችላል።

አንድ ተጨማሪ ቋንቋ ብሔራዊ  ሲሆን በሥር ዓተ-ትምህርት ላይ፣ በመንግሥት ሥራዎች ላይና በመንግሥት ይፋዊ ሥራ  (official business) ላይ እንዲሁም ከዚህ ጋር በተያያዙ የምጣኔ ሀብት ላይ ጫናዎች በማስከተል የአገሪቱን አቅም የባሰ ሊያዳክም ይችላል፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣን ዕዳ ከፋዩ ሕዝብ ሁሉ ውሳኔው ስለሚመለከተው የሚያስከትለውን ሁሉ በወቅቱ አውቆ ሲወስን ዕዳውን ለመክፈል ፈቃደኛነቱን በሕጋዊ መንገድ ስለሚያረጋግጥ የመንግሥት ባለሥልጣናት ምክርቤቱን ጨምሮ  የሚያስከትልባቸው ተጠያቂነት ይቃለልላቸዋል ማለት ነው።

እንዲህ ያለ ለውጥ ከመደረጉ በፊት የኅብረተሰቡ አመለካከት ከፖሊቲካዊ አንፃር ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ፈርጆች በነፃ በታመነበትና ማኅበራዊ መግባባትን የተከተለ መሆን ይኖርበታል። እዚህ ላይ መጥቀስ የሚያስፈልግ ነገር አለ፤ ይኸውም በኦሮሚያ ክልል ውስጥ  አማርኛን ተጠቅመው ጉዳያቸውን መግለጽ የሚችሉ ዜጎች (አማሮች፣ ጉራጌዎች፣ ሐዲያዎች፣ ወላይታዎች… ወዘተ)  አማርኛ የፌዴራል ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ጉዳያችሁን በኦሮምኛ (በቁቤ አጽፋችሁ) ካላቀረባችሁ አንቀበልም በማለት ብዙ ዜጎች ተጉላልተዋል፤ የገንዝብ ኪሣራም ደርሶባቸዋል፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ የኦሮሚያ ክልል አገራቸው እንዳልሆነ ተቆጥሮ በደረሰባቸው ተጽዕኖ የተነሣ ቤት ንብረታቸውን ያጡና የተፈናቀሉም እንዳሉ የአደባባይ ምሥጢር  ነው። እንዲህ ያለ ተጽዕኖ የሚወገደው በአንድ አቅጣጫ ብቻ አጥብቦ በማየትና የተለያዩ ማህበረሰቦች መብት ባለመጠበቁ ስለሆነ በደፈናው ሕግ ሆኖ የሚወጣ ነገር ሁሉንም ነገሮች አይቶና እንዲህ ያሉ ቀዳዳዎችንም ደፍኖ ለመውጣት የሚችለው ተጠቃሚው ሕዝብ ሁሉ አስተያየቱን ሰጥቶ፣ ዳብሮና በሁለንተናዊ መልኩ በሕዝብ የታቀፈ ሲሆን ብቻ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ማነህ ባለ ሳምንት? እኔ ነኝ የምትል የአብይ አህመድ የነገው የፖለቲካ ጭዳ

ከፖሊቲካ አመለካከት ተነሥተው አማርኛንስ ማን መረጠው ብለው የሚከራከሩ ሊኖሩ ይችላሉ። ለዚህ መልሱ በጣም አጭር ነው። አማርኛን የትኛውም መንግሥት አልመረጠውም፤ አማሮችም አልመረጡትም፤ እነሱ ራሳቸው የተፈጠሩት በአማርኛ ነውና። አማርኛ ቋንቋ የተናገረው ኢትዮጵያዊ አማራ ተባለ እንጂ አማራ የሚባል ነገድ አልነበረም፤ ቋንቋውን በመናገራቸው አማራ የሚባሉ ኢትዮጵያዊ ማህበረስቦች ጎንደሬ፣ መንዜ፣ ቡልጌ፣ ወሎየ፣ ጎጃሜ… ወዘተ ተብለው ይታወቃሉ እንጂ በአንድ ላይ ተጠቃልለው በብሔር-ብሔረሰብነት አይታወቁም ነበር፤ ይህ መለያ እየተቀረጸ የወጣው ከኢሐዴግ አመራር ወዲህ ነው። ለምሳሌ የዘመኑ ፖሊቲካ ከመከሰቱ በፊት በህትመት ሥራቸው የሚታወቁት ተስፋ ገብረሥላሴ ዘብሔረ-ቡልጋ እንጂ ዘብሔረ አማራ ብለው አያውቁም፤ ብሔረ-ዘጌ፣ ብሔረ-አገው የሚባሉም ታይተዋል። ኢሕአዴግ ካመጣው መለያ በፊት አማራ ከክርስትና ሃይማኖትና ከኢትዮጵይዊነት ጋር ራሱን አጣምሮ የሚያይ ሕዝብ እንደሆነ እንጂ እራሱን በብሔረሰብነት ለይቶ አያውቅም፤ እስከቅርብ ጊዜ ድረስም አማራን ከክርስትናና ከኢትዮጵያዊነት ጋር አጣምረው የሚያዩ ብዙ ማህበረሰቦች አሉ። በነበረው  የድሮ ቋንቋ ለመግለጽ እንጂ ዛሬማ አማርኛ ተናጋሪው ሁሉንም ሃይማኖት ተላብሷል፤ ሁሉንም ሆኗል፤ አማራ የብዙ ኢትዮጵያውያን ደም ያለበት ኅብረተሰብ ስለሆነ ከምንም በላይ ኢትዮጵያዊ መለያውነቱ ይበልጥ እየተጠናከረ የመጣ  ሕዝብ ነው። ከፊሉ አፍሪቃ ኢትዮጵያ ተብሎ በሚታወቅበት የዓለም ክፍል እስከሜሶፖታሚያ ድረስ መግባቢያ የነበረው ግዕዝ ተፈጥሯዊ በሆኑ ማህበራዊ ክስተቶች የተነሣ በዝግምታ ለውጥ ብሔራዊነቱ ሳስቶ በቤተክርስትያንና የቆዩ ሥነጽሑፎች መዘክር ውስጥ ተወስኗል። ሆኖም አማርኛ ከግዕዝ ተወለደ ሊባልም አይቻልም፤ አማርኛን በአማራነት የሚታወቁ ማህበረሰቦች እንዳልመረጡት ሁሉ በመንግሥት ውሳኔም ሳይሆን በተፈጥሮ እድገት ብሔራዊ የሆነ ቋንቋ ነው። በዝግመታዊ ለውጥ የዛሬዩቱ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ይዘት እየተቀረጸ ሲመጣ አማርኛንም ከብዙ ማህበረሰቦች አውጣጥታ አገራችን ኢትዮጵያ በብሔራዊነት የወለደችው  ቋንቋ ነው። ከ500 ዓመታት ወዲህ አሜሪካንስ የተባሉት ሕዝቦች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች በየጊዜው እየፈለሱ የመጡበትን ትተውና የእንግሊዘኛ ቋንቋን ቋንቋቸው አድርገው አሜሪካውያን ነን ሲሉ፣ ቢያንስ ከ1000 ዓመታት በፊት ጀምሮ ከየራሳቸው አውጣጥተው አማርኛን በመፍጠር ኢትዮጵያዊ የሆኑ ማህበረሰቦች  አማራ መባል ተፈጥሯዊ የኅብረተሰብ እድገት ነው። በመሆኑም የዓለምን ታሪክ አካሄድ በመረዳት ይልቁንስ ወደፊት በጋራ የሚጠብቁንን ችግሮች በማስተዋል የጋራ ራዕይ ማየት ይገባል።

ሦስተኛውና ሌላው መታየት ያለበት የወቅቱ ጉዳይ የአዲስ አበባ ክልላዊ መንግሥት መብት ነው። አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ ነው፤ በርዕሰ ከተማነቱ ደግሞ ከዳር እስከዳር ያለው  የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ አዲስ አበባን የረገጠ ሠራተኛ ወይም ነጋዴ ሁሉ የተለያዩ ግብሮችን በመክፈልና ልማቱን በማሳደግ ከዳር እስከዳር ለብዙ ዘመናት ሀብቱን ያፈሰሰበት ከመሆኑም በላይ በመንግሥትም ሆነ በግል ሥራ ወይንም በንግድ የኖረበትና የሚኖርበት፣ ሌላውም ተወልዶ የኖረበት፣ ወልዶ ያሳደገበት አገሩ ስለሆነ የዚህ ወይም የዚያ ብሔረሰብ ንብረት ወይም እርስት አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ክፍለሀገር እንደመሆኑ መጠን በአዲስ አበባ ላይ ውሳኔ መስጠት የሚችለው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ መንግሥትም ሆነ የመንግሥት ምክርቤት ሥልጣን ሊኖረው አይችልም።

Encyclopedia Britanica እንደ አዲአ አበባ ያለውን ክልላዊ መንግሥት ሲገልጽ፣ “City-state, a political system consisting of an independent city having sovereignty over contiguous territory and serving as a centre and leader of political, economic, and cultural life.” ይለዋል።  ርዕሰ ከተማ የሁሉም ክፍለሀገሮች ማዕከል ነው።    ርዕሰ ከተማ የሁሉም ክልሎች ተወካዮች ተሰብሰበው ውሳኔ የሚሰጡበት መቀመጫ ስለሆነ ሁሉም ወገኖች ባለቤት የሆኑበት ራሱን የቻለ ክልል ነው እንጂ አንዱ ወገን ለብቻው ባለቤት ሊባልበት አይችልም።

 

“Finance and Governance of Capital Cities in Federal Systems ” በሚል ኢትዮጵያም ያለችበት የከተሞችን ፋይናንሽያል አወቃቀር ዓለም-አቀፍ ጥናት ተከታታይ ጥናቶች አድርጎ አቡጃን፣ አዲስ አበባን፣ ካንቤራን፣ ዴልሂን፣ ሜክሲኮንና ዋሽንግተን ዲሲን በተመሣሣይነት ፌዴራል ዲስትሪክት ብሎ በመለየት ሚናቸውም እንደሚከተለው ተጠቅሷል፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  የውጪና የውስጥ ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች ሤራ ፤ በተባበረ ክንዳችን ይከሽፋል ! - መኮንን ሻውል

– National seat of government not under jurisdiction of any one state/province

– Extent of federal control ranges from Abuja (tightly controlled by federal    government) to Canberra (largely an autonomous city-state)

– Issues of local democratic and accountability deficit

– Limited fiscal autonomy

– Direct access to federal funds

 

በበለፀጉ አገሮች ሕግ ሲወጣ የተለያዩ ሕዝቦች ፍላጎቶችንና ጥቅሞችን ለማካተት በአገር ላይ ያሉ የሕዝብ ክፍሎችን ሁሉ ከማዘሉም በላይ የሚያስከተለውን ማህበራዊ፤ ፖሊቲካዊና የምጣኔ ሀብት መዘዞች ሁሉ በርቀት እና በዝርዝር ታይቶ ሊያስከትሉ የሚችሉ ችግሮችን መፍትሔ በመስጠትና ሊነሱ የሚችሉ የመብት ጥያቄዎችን መፍትሔ ሰጥቶ ሊደነገግ ስለሚችል ሕዝብ ተቀብሎት በቀጣይነት ዳብሮ ያለማቋረጥ ያገለግላል። የሕዝብ ምክርቤቶችም የዚያን የሕዝብ ፍላጎት የሚያንፀባርቁ አካሎች ናቸው እንጂ በሕዝብ ተመርጠናል ብለው ሌሎች በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ እንኳ ሕዝብን ሳያስመክሩ ሕግ አያወጡም።

እንዲህ ያሉት ውሳኔዎች በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ ወይም በውሳኔ-ሕዝብ እንኳ ተወስነው ፍጹም ሊሆኑ አይችሉም፤ ቢያንስ ውሳኔው ዲሞክራሲያዊ ነው እንኳ ማለት  አይቻልም። ዲሞክራሲያዊ አሠራር  (1) የሕዝብ ውክልናን (representation) እና (2) የብዙሐን ድምፅን (majority) አሠራሮች ይመለከታል:: ለምሳሌ በአሜሪካ በተደረገው የፕሬዘደንት ምርጫ በብዙሐን ድምፅ ያሸነፉት ወይዘሮ ሔላሪ ክሊንተን ሲሆኑ ዶናልድ ጆ ትራምፕ የተመረጡት በውክልናው ዓይነት የምርጫ  ክፍለሀገሮች ተቆጥረው ብልጫ ስላገኙ ነው።  በመጀመሪያው ዓይነት ሲታይ የትኛውም ማህበረሰብ ከየትኛውም መኅበረሰብ አያንስም፣ አይበልጥም፤ ስለሆነም የሕዝብ ቁጥሩ ግምት ትልቅ ዋጋ ሳይሰጠው በክልልነቱ ከሌሎች ክልሎች ጋር እኩል ድምፅ ኖሮት አንድን ክልል በሚመለከት ውሳኔ ላይ ተሳታፊ ካልሆነና ሌላ መንግሥታዊ አካል የሜወስን ቢሆን ተጽዕኖ ተደረገበት ማለት ነው፤ ይህም ፀሪ-ዲሞክራሲያዊ ነው። በተለይም እንደኛ ባሉ በጠመንጃ አፈሙዝ ውሳኔን በሕዝብ ስም የመፈጸም ልምድ ባለበት አገር  በፖሊቲከኞች ወይም የመንግሥት ሥልጣን ላይ ባሉ ሰዎች የሚወጡ ሕጎች በአንድ አቅጣጫ በሚተላለፍ የብዙሐን መገናኛ መግለጫዎች ሞገድ የግድ ለማሳመን ከሚደረግ ዘመቻ በስተቀር  በሰከነ መልክ ሕዝብ እንዲመክርበት ስለማይደረግ በፖሊቲካ ጫና በሚደረግ ግርግር በግብታዊ መልክ እኛ ለሕዝቡ እናውቅለታለን በሚሉና በሥልጣን ላይ ባሉ ፖሊቲከኞች ውርጅብኝ ስለሚወሰኑ ሕጉም ዘርፈ-ብዙ ሆኖና በስሎ ስለማይወጣ ዝርዝር የሕዝብ ጉዳዮችንና ፈቃዳቸውን ካለማካተቱም በላይ አሠራሩም ሕዝባዊ ወይም ዲሞክራሲያዊ ስለማይሆን ማህበረሰቦችን የማያበራ ግጭት ውስጥ ሊጥል ይችላል። በአገር ደረጃ የሚወሰኑ ነገሮች ሁሉ  በአገር ላይ ያሉ ብዙሐን ማህበረሰቦችን ሁሉ ይመለከታል፤ ስለሆነም ጉዳዩ ሁሉንም የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለሚመለከት መንግሥት ለሕዝብ ፍላጎቶች ተገዥ በመሆን ሕዝብን ያገለግላል እንጂ  በብሔራዊ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ወስኖ በአዋጅ ሕዝብ ላይ ጫና የማድረግ ሥልጣን ስለሌለው እንዲህ ያለው ጉዳይ የሚፈታው በውሳኔ-ሕዝብ ብቻ መሆኑ መታወቅ አለበት። “አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ” እንደሚባለው የሕዝብን አንገብጋቢ ጉዳዮች በችልተኝነት እንደረመጥ አዳፍኖ ማቆየት ወይም ለጎታች የአገር ችግሮች እርሾ ማቆየት ስለሚሆን ወደፊት በእድገት ፋንታ ሌላ አዘቅት ውስጥ እንዳንገባ በወቅቱ ሊታሰብበት ይገባል። በቅድሚያ ያልተመከረበት ነገር የሚያስከትለው መዘዝ ብዙ ነውና። ስለዚህ ስለወደፊቷ ኢትዮጵያ ራዕይ አለን የሚሉ ሁሉ እነዚህን ጉዳዮች ዋና አጀንዳዎች ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ተፈራ ድንበሩ

 

 

 

16 Comments

  1. The great Oromo nation doesn’t need your blessings in order to decide on Oromia and afaan Oromo. It is up to them for those hardliners like you whether you or not the natural rights of the Oromo nation on it’s own soils. You are a loser and simple minded popogandist. Your writings are just garbage in and garbage out! It Will bring nothing watch out!

    Some hardliners like you speak about a fake equality and unity while they have been promoting the principles of discrimination and racism, let alone about human dignity. His friend in crimes Girma Seyifu told us last time in one of his statements that he doesn’t want to see the development of the Oromo culture and language in Finfinne. He cannot tolerate it. For persons like him the Oromo are an alien in Finfinne. Besides that he claim that those from coutryside are not capable enough to take a position of leadership in the big cities even if they are highly qualified for the jobs. Ketemenet is for him and for those like him a big deal and a great asset. Ketemenet is as his point of view the main required qualification to take a position of leadership in the cities. Such persons are irrational and primitive. 

    Oromoo nationalism or Oromuuma is the core  values and ingredients of the Oromo struggles for social, economic, cultural and  democratic rights, freedom and prosperity. The Oromo nationalism is against the inhuman systems  of Minilik, Haile Selassie, Mengistu Hailemariam and that of Meles Zenawi and those who have been trying to defend those dark eras. But it is not against no nations and no peoples of Ethiopia. Oromo nationalism promotes mutual understanding among nations and nationalities of Ethiopia, especially between the Oromo and Amhara nations. Abiy Ahmed is a product of the Oromo struggles. The main source of his  political power is the Oromo people in general and the Qeerroo  in particular, but not his personal merits. Dr. Abiy knows all these more than any body might do it.

    The current spearhead of the Oromo struggles is the Qubee generations or QEERROO, but not Abiy Ahmed and Lemma Megerssa. These two heroes of the nation are tasked  to implement the roadmaps of the freedom which are worked out by the Qubee generations. The main sources of the political powers of Abiy Ahmed and Lemma Megerssa are the struggles of the Oromo nation in general and that of the QERROOS in particular. Dr. Abiy Ahmed is the Primeminster of all Ethiopians. But don’t forget he is the son of the Oromo nation.

    No one has disowned the ethnic background of Mengesitu, Haile Selassie, Gobana Datche, the Hitler of Africa and other Anti-Oromo and Oromummaa elements. If you can claim that Meles Zenawi himself is an Oromo, it is okay. In general, we have no problem with the ethnic background of an individual or a group of individuals. What matters most is their psychological makeup and stands on the basic human rights and the systems which they have served. That means, it doesn’t matter from which ethnic background they were or are.

    The struggle of the Oromo nation is not against the Amahara and the Tigre peoples. It is only against subjugation and exploitation, discrimination and forcibly imposed assimilation.

    We believe the Oromo nation is the pillar of peace, stability, security and prosperity of the Horn of Africa. You should have to accept these facts and work with us so that we can promote together mutual understanding and respect. It is up to you if you think rationally and adjust yourself with the realities  of this time instead of dreaming the golden time of the eradicated old past eras. By negotiating we can build a multinational federal states of Ethiopia at the best interests of all nations in Ethiopia.

    Narrow nationalists are those who are against the democratic rights of the differet nations in Ethiopia. They have been using always derogatory terminologies in order to undermine the demands of the Oromo nation. Those individuals are desperate and hopeless. No more business as a usual.

    Only the Oromo nation had full rights to decide about Oromia and afaan Oromoo! The time of deciding by aliens on the fate of the Oromo nation has gone forever!

    Down with anti-Oromo, anti-afaan Oromo and anti-Oromuuma!

    Go forward with our Qeerroo and beloved leaders BEKELE GERBA, MARARA GUDINA, LEMA MAGERSSA, ABIY AHMED and many others!

    No more business as a usual in Oromia including Finfinne!

    Lemane Megerssa has massage for those like you. Read it:

    m.facebook.com/story.php?story_fbid=2160439874187243&id=100006637535160

    • የግዕዝ/የሱባ/የሳባ/ ፊደል የኦሮሞ እንደነበረ አንድ ጥናት አረጋገጠ።
      ===========================
      ሳባ = ሳ ሰው, ህዝብ, /የእግዛቤሔር ሰው
      ባ ነብስ, መንፈስ
      ሳባ ስንል መንፈሳዊ የእግዛቤሔር ህዝብ ለማግለጽ ነው። ለግለሳብ የሚሰጥ ሳይሆን የወል ስም ነው። ሳባ ኦሮሞ ሳባ አማራ ወዘተ/የኦሮሞ ህዝብ የአማራ ህዝብ እንደማለት ነው/።
      ወል የምለው ቃል ከተነሳ ወደ ሎረት ፀጋዬ ገ/መድህን አባ ገዳ ግጥም ይመልሰናል። ሎረቱ ግጥሙን ከማንበባቸው በፊት ግጥሙ የተጻፈው በወል ቤት ግጥም ዘይቤ መሆኑንና “ወል” የምለው ቃል የጥንታዊ ጥቁር ግብጽ አይሮግላፍክስ ቃላት እንደሆነና ትርጉሙም, አንድነት, ሀብረት, የጋሪዮሽ ነው ብሏል። በመቀጠል ባስቀመጡትም ምሳሌ ወሎ- አንድነት, ወለጋ – ታላቅ አንድነት, ወላይታ -የእውነት አንድነት እንድሁም ወልዲያ, ወልወሎ, ወልቂጤ, ወልመራ, የመሠሠሉትን ጠቅሷል።
      ከዚህና ከሌሎች ቀጥታ ኦሮሞ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ከአሮግላፍክ ቃላት እንደመጡ እንገነዘባለን። በማሆኑም የጥናት ተቋም ተቋቁሞ በአውሮፓና በተለያዩ የአለም ክፍል ሙዜየም ውስጥ ተዘርፎ የምገኙት ተጠንቶ በተቀነጃ መልክ እስክ ቀርብ ትንሽ ፍንጭ ለመስጠት ያህል ከነጌ ጀምሮ የሚከተሉት አርዕስት ላይ ትንሽ /highlight/ መስጠት እሞክራለሁ።
      1ኛ. አይሮግላፍክ ቃላት ምንድነው?
      2ኛ. የሱባ/ሳባ/ ፊደል ከየት መጣ?
      3ኛ. ኦሮሞ እንዴት ከከተማና ከስልጣኔ ተለየ?
      4ኛ. የ2,500 ዓመት ጦርነት/በኦሮሞ ህዝብ ላይ/ እና ሌሎችም ጨምሮ ይጠብቁኝ።

  2. The great Oromo nation doesn’t need your blessings in order to decide on Oromia and afaan Oromo. It is up to you for those hardliners like you whether you accept or not the natural rights of the Oromo nation on it’s own soils will be decided only by the Oromo nation. You are a loser and simple minded popogandist. Your writings are just garbage in and garbage out! It Will bring nothing watch out!

    Some hardliners like you speak about a fake equality and unity while they have been promoting the principles of discrimination and racism, let alone about human dignity. His friend in crimes Girma Seyifu told us last time in one of his statements that he doesn’t want to see the development of the Oromo culture and language in Finfinne. He cannot tolerate it. For persons like him the Oromo are an alien in Finfinne. Besides that he claim that those from coutryside are not capable enough to take a position of leadership in the big cities even if they are highly qualified for the jobs. Ketemenet is for him and for those like him a big deal and a great asset. Ketemenet is as his point of view the main required qualification to take a position of leadership in the cities. Such persons are irrational and primitive. 

    Oromoo nationalism or Oromuuma is the core  values and ingredients of the Oromo struggles for social, economic, cultural and  democratic rights, freedom and prosperity. The Oromo nationalism is against the inhuman systems  of Minilik, Haile Selassie, Mengistu Hailemariam and that of Meles Zenawi and those who have been trying to defend those dark eras. But it is not against no nations and no peoples of Ethiopia. Oromo nationalism promotes mutual understanding among nations and nationalities of Ethiopia, especially between the Oromo and Amhara nations. Abiy Ahmed is a product of the Oromo struggles. The main source of his  political power is the Oromo people in general and the Qeerroo  in particular, but not his personal merits. Dr. Abiy knows all these more than any body might do it.

    The current spearhead of the Oromo struggles is the Qubee generations or QEERROO, but not Abiy Ahmed and Lemma Megerssa. These two heroes of the nation are tasked  to implement the roadmaps of the freedom which are worked out by the Qubee generations. The main sources of the political powers of Abiy Ahmed and Lemma Megerssa are the struggles of the Oromo nation in general and that of the QERROOS in particular. Dr. Abiy Ahmed is the Primeminster of all Ethiopians. But don’t forget he is the son of the Oromo nation.

    No one has disowned the ethnic background of Mengesitu, Haile Selassie, Gobana Datche, the Hitler of Africa and other Anti-Oromo and Oromummaa elements. If you can claim that Meles Zenawi himself is an Oromo, it is okay. In general, we have no problem with the ethnic background of an individual or a group of individuals. What matters most is their psychological makeup and stands on the basic human rights and the systems which they have served. That means, it doesn’t matter from which ethnic background they were or are.

    The struggle of the Oromo nation is not against the Amahara and the Tigre peoples. It is only against subjugation and exploitation, discrimination and forcibly imposed assimilation.

    We believe the Oromo nation is the pillar of peace, stability, security and prosperity of the Horn of Africa. You should have to accept these facts and work with us so that we can promote together mutual understanding and respect. It is up to you if you think rationally and adjust yourself with the realities  of this time instead of dreaming the golden time of the eradicated old past eras. By negotiating we can build a multinational federal states of Ethiopia at the best interests of all nations in Ethiopia.

    Narrow nationalists are those who are against the democratic rights of the differet nations in Ethiopia. They have been using always derogatory terminologies in order to undermine the demands of the Oromo nation. Those individuals are desperate and hopeless. No more business as a usual.

    Only the Oromo nation had full rights to decide about Oromia and afaan Oromoo! The time of deciding by aliens on the fate of the Oromo nation has gone forever!

    Down with anti-Oromo, anti-afaan Oromo and anti-Oromuuma!

    Go forward with our Qeerroo and beloved leaders BEKELE GERBA, MARARA GUDINA, LEMA MAGERSSA, ABIY AHMED and many others!

    No more business as a usual in Oromia including Finfinne

  3. We also need referendum on our national flag. The current official flag with a blue star embedded in it is invented by Woyane without asking the Ethiopian people. We Ethiopians know only our historical tricolor flag GREEN, YELLOW and RED. That is it. Even in Tigrai, in the past, the national flag with tricolor (and with no blue star) was very respected, and observed in funerals and weddings. We need to have referendum on our flag. 100 million Ethiopian people should vote and decide on it once and for all.

    • OROMIA IS NO MORE A WISH, IT IS A REALITY. IT IS IN THE MIDDLE OF THE ETHIOPIAN POLITICS. BESIDES IT IS THE MAIN AGENDA IN WORLD POLITICS WHICH DEALS WITH ETHIOPIA. MORE THAN EVERYTHING YOU CANNOT ERASE OROMIA FROM THE MIND AND HEART OF THE OROMO NATION IN GENERAL AND THE QUBEE GENERATION IN PARTICULAR.

      The flag of those inhuman systems of your forefathers will be prohibited in the future Oromia and in the southern part of that country like the banners of Nazis and apartheid whether you believe it or not. Already it is underway. The Qubee generation don’t like even to touch it.

      The true multinational democratic Ethiopia will have its own flag and banner which will be decided democratically so that it will reflect the reality of that country.

      Whether you like it or not we will build a new multinational democratic Ethiopia which will embrace all it’s citizens equally. We will assure that the Gada democratic principles will work in OROMIA and beyond that.

      THE TRUTH SHALL PREVAIL!

    • And Oromos will never give up our heritage – black, red & white, The symbol of black civilization.

  4. ስለ አሰብ ወደብ ያሉትን ደግፋለሁ፤
    ስለ ተጨማሪ ብሄራዊ ቋንቋ ያሉትም ልክ ይመስለኛል። ግን ከዚህ ጋር በተያያዘ ከማውቀው/ካነበብኩት የሚቃረኑ ስለ ሁለት ነገሮቸን ላነሳብዎት እወዳለሁ። 1/ አማራ የሚለው መለያ እየተቀረጽ የመጣው ከኢህሃዲግ አመራር ወዲህ አይደለም። እኔ ተወልጄ ያደኩት ደቡብ ክልል ውስጥ አብዮቱ ሲመጣ 6 አመቴ ነበር።በስፍራውም ከተለያዮ የኢትዮጵያ ክፍሎች የመጡ ሰዎች ነበሩ። ኦሮሞ የሆነው አባቴ ኦርቶዶክስ ቢሆንም አማራ ተብሎ አይታወቅም። በናቴ ወገን ጎንደሬ የሆኑት አያቴ ግን አማራ እንደሆኑ ቃሉን እየጠቀሱ ይናገሩ ነበር ሌሎችም በጎንደሬነትም በአማራነትም ያውቋቸዋል። ብዙ ጎጃሜዎችም አብረውም አሉ። በንጎሱም ሆነ በደርግ ጊዜ እንሱን በተለይ ከኦሮሞና ከሌሎች ዘሮች ለይቶ ማውራት ባስፈለገ ጊዜ አማራ እያልንና እያሉ እንደሚጠቀሱ በጣም በግልጽ አውቃለሁ። እርግጥ ነው በአማሮቹ መካከል ወንዘኝን ሰላለ ጎጃሜ ጎንደሬ መንሼ የሚለው ጎልቶ ይታወቃል። ትግሬዎችን ግን ትግሬ እንጂ ኦርቶዶክስ በመሆናቸው አማራ ብለን አንጠራም። ዛሬም በህይወት ያለችው እናቴም አማራ ኦሮሞ የሚለውን ክላሲፊኬሽን በግልጽ ታውቃለች። በኋል አድጊ ዪኒቨርሲቲ ስገባ ከሃረር የመጡ ልጆች አማራን ለክርስቲያን መለያ አድርገው እንደሚጠቁሙ ተረድቻለሁ።
    2/አማርኛ ቋንቋ ከሌሎች ቋንቋዎች የተውጣጣ ቋንቋ እንጂ ከግዕዝ የተወለደ እንዳይደለ የተናገሩት እስከዛሬ ከማውቀውና በዶ/ር ግርማ ደመቀ እና በሌሎችም ምሁሮች ከተመሰከረው እውነት ጋር መቶ በመቶ ይጋጫል።

  5. This is Habesha hypocrisy at its best! “Oromiffa would have a negative impact on other nations/ nationalities but Amharic won’t have any”! “The right of few non-Oromos living in Oromia is abridged because these have to use Oromiffa in official communications. Therefore, the Oromo that make up 99% of the population must learn Amharic instead.” Are these types the only intellectuals Habeshas have?? Tragic!!

  6. ገመዳ አሁንም አልተስተካከልክም የህዝብን እንድነት እልገባህም????

  7. አፋን ኦሮሞ ከአማርኛ ጋር ጎን ለጎን ኦፍሽያል የኢትዮጵያ የስራና የጋራ የመግባቢያ ቋንቋ እንዲሆን ሁሉም የኢትዮጵያዊ ስለሚፈልግና ስለሚሆን ሰለዚህና በዚህም አፋን ኦሮሞ የኦርሞ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ አገራዊና የሁሉም የኢትዮጵያውያን ቋንቋ መሆኑ ሰለሆነ ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የኢትዮጵያዊ ይመለከተዋል በመሆኑምኦሮምኛ ኢትዬጵያዊ ቋንቋ ነው።ሙሉ መብቱና ክብሩ የመጠበቅ ጉዳይ የጋራ ጥያቄና በጋራ መልስ የምንሰጠው ጉዳይ ነው።

  8. የግዕዝ/የሱባ/የሳባ/ ፊደል የኦሮሞ እንደነበረ አንድ ጥናት አረጋገጠ።
    ===========================
    ሳባ = ሳ ሰው, ህዝብ, /የእግዛቤሔር ሰው
    ባ ነብስ, መንፈስ
    ሳባ ስንል መንፈሳዊ የእግዛቤሔር ህዝብ ለማግለጽ ነው። ለግለሳብ የሚሰጥ ሳይሆን የወል ስም ነው። ሳባ ኦሮሞ ሳባ አማራ ወዘተ/የኦሮሞ ህዝብ የአማራ ህዝብ እንደማለት ነው/።
    ወል የምለው ቃል ከተነሳ ወደ ሎረት ፀጋዬ ገ/መድህን አባ ገዳ ግጥም ይመልሰናል። ሎረቱ ግጥሙን ከማንበባቸው በፊት ግጥሙ የተጻፈው በወል ቤት ግጥም ዘይቤ መሆኑንና “ወል” የምለው ቃል የጥንታዊ ጥቁር ግብጽ አይሮግላፍክስ ቃላት እንደሆነና ትርጉሙም, አንድነት, ሀብረት, የጋሪዮሽ ነው ብሏል። በመቀጠል ባስቀመጡትም ምሳሌ ወሎ- አንድነት, ወለጋ – ታላቅ አንድነት, ወላይታ -የእውነት አንድነት እንድሁም ወልዲያ, ወልወሎ, ወልቂጤ, ወልመራ, የመሠሠሉትን ጠቅሷል።
    ከዚህና ከሌሎች ቀጥታ ኦሮሞ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ከአሮግላፍክ ቃላት እንደመጡ እንገነዘባለን። በማሆኑም የጥናት ተቋም ተቋቁሞ በአውሮፓና በተለያዩ የአለም ክፍል ሙዜየም ውስጥ ተዘርፎ የምገኙት ተጠንቶ በተቀነጃ መልክ እስክ ቀርብ ትንሽ ፍንጭ ለመስጠት ያህል ከነጌ ጀምሮ የሚከተሉት አርዕስት ላይ ትንሽ /highlight/ መስጠት እሞክራለሁ።
    1ኛ. አይሮግላፍክ ቃላት ምንድነው?
    2ኛ. የሱባ/ሳባ/ ፊደል ከየት መጣ?
    3ኛ. ኦሮሞ እንዴት ከከተማና ከስልጣኔ ተለየ?
    4ኛ. የ2,500 ዓመት ጦርነት/በኦሮሞ ህዝብ ላይ/ እና ሌሎችም ጨምሮ ይጠብቁኝ።

  9. ዘመድ የለህም ወይ አሰብን ለማስመለስ በጦርነቱ ግዜ በ ኤርትራ መሬት ማዳበርያ የሆነ ።
    እሺ በቃ ተወው አንተ ራሱህ ጸሃፊው ብቅ በል በቀጠሮ የማዳበርያ እጥረት አለን

  10. የግእዝ ፊደላት ) እናት ፊደላት 26 ናቸው )……………………. 1/ አማርኛ ሲስፋፋ በራሱ ድምጽ የማይገኙትን ግንበኩሽ ቋንቋ የሚግኙ ድምጾችስምንት ፊደላት ሸ ቸ ጀ ጨ ኘ ኸ ዠ ቨ ተጨምረው አሁን 34 ደርሰ
    ዋል።በተጨማሪም ዲቃላ
    እና ህፁፃን ፊደላት አሉ ።
    2/ ትግርኛም እንደዚሁ በግእዝ 26 ፊደላት ላይ እንደ ” ቐ ” የመሳሰሉትን በማከል የፊደል ገበታ/ሰሌዳ/ይዟል። ለምሳሌ”መቐሌ”
    3/ ኦሮሚኛም እንድዚሁ በግዕዙ 26 ፊደል ላይ የኦሮሞው ተወላጅ የቋንቋ ሊቀ ሊቃውንት አናሲሞስ ናሲብ(አባ ገመቺስ) እና አስቴር ጋኖ የተባሉት ከዛሬ 230 አመታት በፊት ከዚህ በታች ያሉትን ፊደላት ፈጥረው
    ዸ ዹ ዺ ዻ ዼ ዽ ዾ ዿ
    ተጨማሪ አክለው የፊደል ገበታ አሟልተዋል።
    ኣንድኣንድ የኦሮሞ ምሁራን ግዕዝ የኦሮሚፋ ቃላትን ኣይጽፍም በማለቱ በኣለማወቅ በስሕተቱ ገፍተውበታል። ጎዸቱ፣ ቶኮፋዸ፣ ዹፌ፣ ዹጉማ፣ ጀዺ፣ ዻባ፣ ዻራርቱ፣ ባዻዻ፣ ዻዻ፣ ጄዼ፣ ዼራ፣ ዽባፍ፣ ዽባ፣ ነንዾከዼስ ምሳሌዎች ናቸው።
    ተጨማሪ አክለው የፊደል ገበታ አሟልተዋል።
    ሌሎቹም የኢትዮጽያውያን ቋንቋዎች ሁሉ እንደዚሁ አሟልተዋል።በመሆኑም በዚህና ስለዚህም የግእዝ ፊደል በመባል በጋራ በወልና በጥቅል ስም ይጠራል።

Comments are closed.

Share