October 16, 2017
3 mins read

የተቃዋሚ ጎራዉ የወያኔ መዉደቂያ ደረሰ የሚለዉ ወቅታዊ አጀንዳ መሰረቱ ምን ይሆን?

ሸንቁጥ አየለ
——————–

ይሄን ያህል ጀነራል: ይሄን ያህል ልብስ አልባሽ: ይሄን ያህል ሹም ከዳ እናም ወያኔ ሊወድቅ ነዉ እያለ ወቅታዊ አጀንዳዉን ያራግበዋል::ጥያቄዉ ከማን ወገን ነዉ የከዳዉ::ሀያ ስድስት አመታት ሙሉ ከወያኔ/ህዉሃት/ፓርቲ ወይም ጀነራሎች ዉስጥ አንድም ሀይል ከድቶ አያዉቅም::የወያኔ የስልጣን ነብስ: ልብ: አዕምሮ እና ስሜቱ ደግሞ ህዉሃት እና ህዉሃት ብቻ ነዉ:: ለበርካታ አመታት እንቶኔ ከዳ : እንቶኔ ለቀቀ ሲባል የህዉሃት ጀነራሎች ዉስኪያቸዉን እያንጫለጡ ይስቃሉ::የህዉሃት ፖለቲከኞችም የተቃዋሚዉ ሚዲያ የሚያርገበግባቸዉ ሚስጥር የሚመስሉ ነገሮችን አዉቀ ይለቃሉ::

ህዝብም ይሄንን የተቃዋሚ ሚዲያ ትንታኔ ተከትሎ እንዲህ ይላል::”ደረግም : ሀይለስላሴም ሊወድቁ ሲሉ እንዲህ በርካታ ባለስልጣኖቻቸዉ ይከዷቸዉ ነበር::እናም የወያኔ መዉደቂያዉ ደርሷል” እያለ ይተነብያል::ሆኖም በስሜት የሚግለበለበዉ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ለህዝቡ የማይነግሩት እና እራሳቸዉ ተቃዋሚዎችም የማያስተዉሉት ጥብቅ እዉነታ የወያኔ እና የቀደሙት የመንግስታት ስርዓት መሰረታዊ ልዩነት እጅግ ጥልቅ እና ዋናዉ የነገሮች ማጠንጠኛዉ መሆኑን ነዉ::

ከሀይለ ስላሌ ሚኒስቴሮች ዉስጥ አንድ ሚኒስቴር ቢከዳ ወይም ከደርግ ጀነራሎች ዉስጥ አንድ ጀነራል ቢከዳ አጠቃላይ የመንግስታቱን ስርዓት የመናጥ ጉልበቱ ከፍተኛ የሆነበት ዋናዉ ምክያት አንድ ወጥ የመንግስት ስርዓት በሀገሪቱ ስላለ ነበር:: የስርዓቱ ሚስጥራት: ሰነዶች : እንዲሁም ስትራቴጅዎች በአንድ ቋት ዉስጥ ስለነበሩ አንድ ቦታ የስርዓቱ ጆንያ ተቀደደ ማለት አጠቃላይ ስርዓቱ ማፍሰስ እና መቦርቦር ይጀምራል ማለት ነዉ::

የወያኔ ስርዓት ግን ከዚህ ፈጽሞ በጅጉ የተለዬ ነዉ::ለምሳሌ ወያኔ ኦፒዲኦም ሆነ ሙታኑ ብአዴን በአንድ ቀን ቢፈርሱ ምንም አይሆንም::ስልጣን በወያኔ ሰራዊት እና ደህንነት እጅ ናትና ሌላዉ ቀርቶ አለምን ለማታለያነት እና በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለማላገጫነት ያዋቀረዉ ፓርላማ ቢፈርስም ወያኔ ቀጥ ብሎ በሽፍታ ስርዓስት ሀገሩን ይመራዋል:: ወያኔ የተለዬ ስርዓት ነዉና በተለመደዉ የመንግስት አወቃቀር ስልት ወያኔን ሊተነትኑት የሚሞክሩ ተቃዋሚዎችን እና ተንታኞችን ሁሌም እንዳታለላቸዉ እና እንደሸወዳቸዉ ነዉ::

negaso gidada2
Previous Story

“የሰንደቅ ዓላማና አርማ ጉዳይ ለህዝብ ውይይት አልቀረበም” – ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ (አዲስ አድማስ)

freedome
Next Story

ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ… – ነፃነት ዘለቀ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop