ማንን እንመን? – ገብርኤል ብዙነኀ

 ይህ ጥያቄ እኔ ባደባባይ ላውጣው እንጅ በያሉበት ሆነው ባንድ ጉዳይ ላይ የተለያዩ  ነገሮችን የሚዘበራርቁትን ጳጳሳት  መምህራን የሚሉትን በቤተ ክርስቲያናችንውስጥ ያለውን ብቻ ሳይሆን በሩቅና በቅርብ ያለውን ተመልካች እየታዘባቸው አማኙን እያሳዘነ ነው።  በየ ቤተ ክርስቲያን በህዝብ ፊት እየቆሙ የሚያሰራጩትመዘበራረቅ የማያመውና የማይሰማው እኔ ምና ገባኝ ብሎ ዝም የሚል ክርስቲያን እንደምን ያለ ክርስትና ነው? የሚል ጥያቄ ከተለያየው ህዝብም በየቦታው እያስነሳነው።

ቀሲስ አስተርዕየ

የውጩ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ የቀድሞው ቆሞስ አባ ወልደ ትንሳዔ ያሁን ሊቀ ጳጳስ አቡነ በርናባስ “ክርስቶስ በሥጋው ፍጡር ጠበቃ አማላጅ ነው” ይላሉ።

 የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን  እወክላለሁ የሚሉት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል ፤ “የውጩ ሲኖዶዶስ ክርስቶ በሥጋው ፍጡር ነው ስለሚል ከእንግዲህ እርቅ የለም” ይላሉ።

የውጩ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ስያትል የሚኖሩ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሉቃስ የሚባሉት በበኩላቸው የራሳቸው ሲኖዶስ አባል የሆኑትን “አቡነ በርናባስን እስልምና እንኳ ፈራጅ ብሎ አያምንም ክደው አማላጅ ነው በማለታቸው መናፍቅ ናቸው” ብለው አውገዘዋል።

ቆሞስ አባ መአዛ በየነ የሚባሉትም ቤተ ክርስቲያናችን ከምትለው ውጭ የሚወቀሱባቸውና የሮማ ካቶሊክን እስታቹ በቤተ መቅደስ መተከልንና ብዙ የዘበራረቁት እንዳለ ሆኖ፤ አሁን በተነሳው ነገርም፤ እነ ዶክተር አክሊሉን እየጠቀሱ ተከሰተባቸው እያሉ አቡነ በርናባስን በመደገፍ ይናገራሉ። 

 በገለልተኝነትን ሽፋን በማድረግ ለሳቸው የተመቻቸውንና ደስ ያላቸውን ብቻ እየመረጡ ነው ማለት ነው የሚናገሩት? አሁን የሚናገሩትን ትክክል ይሁኑ አይሁን ሊመሰክሩላቸው የሚችሉት ባንዲት ቅንጣት ብቻ የሚስማሟቸው ሰዎች ካልሆኑ ማነው የሚመሰክርላቸው።  በግላቸው ስለሚያደርጉት ያፈነገጠ ነገር ትክክል ስለመሆናቸው ማነው የሚያረጋግጥላቸው?  ከማን መምህር ከየት ጉባዔ ተማሩት?

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላን መተግበር ሌላ ኦሮምኛ ተናጋሪ ገበሬዎችን በግፍ ከመሬታቸው መንቀል ሌላ, ኦሮምኛ ተናጋሪ ገበሬዎችም ከኢትዮጵያ ሌላ ሀገር የላቸውም

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ የሚባሉም፦  የኛ ሊቃውንት አባቶች የማይጠቅሷቸውን የጣሊያኖችን ሰዎችና እነሱ የሚሉትን እየደረደሩ አኀት አብያተ ክርስቲያናትናት ከነሱና ከእሱ  እንዲማሩ በድፍረት እየተናገሩ ነው። ይህም ባብነቱ ትምህርት ነበርን በሚሉ ሁሉ ትልቅ ውርደት ያስከተለባቸው ወቅት ነው። የተዘበራረቀ የሚናገሩት ሁሉ የሊቃውንት ጉባዔ የሚባለው ጭራሽ እነደሌለ ነው።የተመለከተውን ሁሉ እያስገረመው ነው። ተሃድሶዎች ጋር በውጊያ ስንጠመድ ሳናውቀው ቀኝ እግራችን ካቶሊኮች ግቢ ዘው ብሎ መግባቱን ይሆን?

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ንጽህና የAugustine “Immaculate Conception” በኋላም 1854 የሮማ ካቶሊክ Pope Puis ዶክትረን አድርጎ የወሰነውን የኦርቶዶክሶች እምነት ነው አትናትዮስም ከሺህ አመት በፊት የተናገረው ነው ን ነው ካቶሊካዊ አገላጽ እና ፍጽም ከኦርቶዶክስያልሆነና አትናትዮስም “On the Incarnation by St. Athanasius” በሚለው መጽሃፉ ውስጥ የማይገኝ ነው። ይህንን የAugustine የስህተት ትምህርትመላው ኦርቶዶክሳውያን በተለይም ከእኛ ጋር የእምነት አንድነት ያላቸው Oriental Churches (አሃት አብያተ ክርስቲያናትን) በፍጹም እንደማይቀበሉት የካቶሊክብቻ እምነት እንደሆነ ሳይገልጹ ጭራሽ የአትናትዮስም እምነት ነበር አሉን ካቶሊቶሊኳዊውን እምነት የእኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክቤተክርስቲያን  ለማድረግ  ነውን !

በዚህች አጭር ጽሁፍ የተገለጹት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚታየውን ወዲህ ወዲያ ወዲህ  የተዘበራረቀ ነገር እየተናገሩ እርስ በርሳቸው በመደባደብ ህዝቡን  የርስ በርሳቸው መደባደቢያ ብትር የሚታገሉበት ሜዳ አደረጉት። ከማዳመጥ በቀር የምትናገሩትን ሁሉ ከየት አመጣችሁት? ብሎ ህዝቡ እንደማይጠይቃቸው ተረድተው፡ በዚች ኢትዮጵያቤተ ክርስቲያን ፤ በመነኩሴ በጳጳስ  በሰባኪ ስም ራሱን ሸፍኖ በመደባደብ እየዞሩ ህዝቡን በመከፋፈል ችግሩን እያጋጋሉ  እያሰለቹን ቤተ ክርስቲያንን እያናወጣት ያለው የተዘበራረቀ ንግግራቸው ግራ ለተጋባነው ማነው እውነቱን ሊገልጽልን የሚችለው? የጥንት ሊቃውንት ያብነቱ መምህራን ይህን የተዘበራረቀ ነገር እንዴት  ያስተካክሉትና ያስታርቁት ነበር?ማነው የዋሸው?

ተጨማሪ ያንብቡ:  “ውሸት ቁጥር የለውም” እና “አያ ጅቦ - ኦሮሙማ መጣብህ” !!

የሚነገረንና የምንሰማው ምንድነው? ወዴትስ እየተመራን ነው? እርስ በርሳቸው በሚደርጉት ሽኩቻ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነገረ መለኮት ራሳቸው እየሳቱና ህዝቡንም እያሳቱ ናቸው።ለቅድስና መወዳደርና መነጻጸር እጅግ አስፈላጊ ሆንም፤

ቅዱስ ጳውሎስ እራሳቸውን ከገዛ ራሳቸው ጋራ እያነጻጸሩ እኛ ብቻ በማለት እራሳቸውን እያገነኑ ከተግዳሮት እንደወደቁ ሰዎች አንሁን። ራሳቸውን ከራሳቸው ጋራ የሚያነጻጽሩ ሰዎች የሚናገሩትን አያውቁም” ብሎ ያስጠነቀቀውን ባለመርሳት፤

“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሄርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ተጠንቀቁ ። ከሄድኩህ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ ደቀ መዛሙርትን ወደ ኋላ ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገረን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሱ እኔ አውቃለሁ” ( የሐዋ ፳፡፳፰᎗፴) እያልን ወደፊት የሚከሰተውን ሳይቀር እየተናገርን እንደ እነ ቅዱስ ጳውሎስ፤ ያለፈውን ካለው ጋራ እያነጻጸርን፤ ዘመናችንን እየዋጀን፤ የሚመጣውንም እየገመትን፤ የተኩላ ባህርይ ካላቸው ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን በትጋትና በቅድስና ለመጠበቅ በታሪክ የሰማናቸውን እንደነ አቡነ ጴጥሮስ የነበሩትን ሰማእታት ሳንረሳ፤ ክርስቶስ የዮሐንስን ደቀ መዛሙርት አነጋግሮ ከሸኘ በኋላ ሰዎች ከእምነቱና ከወቅታዊውችግር ጋራ የማይገናኝ ነገር ሲነጋገሩ ሰማና “ነፋስ የሚወዘውዘውን ሸምበቆ ወይስ ቀጭን ዋብስ የለበሰው ሰው ለማየት ነው  የመጣችሁ?” እያለ አቋም የለሽነታቸውንና አላማ ቢስነታቸውን በምሬት  ነገራቸዋልና።

ቀሲስ አስተርአየለመሆኑ እሰዎ  እንዴትስ ያስታርቁታል?  በእምነታችን ላይ የዘራውን የጥርጣሬ መንፈስእንዴት ይመለከቱታል? መታለፍ በሌለባቸው  ነገሮች ላይ የግብጽ ይህን ይላል አኀት አብያተ ክርስቲያናት ይህን ይላሉ፤ የሮማ ካቶሊኮች ይህን ይላሉ፤ ከማለተዎ  በፊት ከዚህ ቀደም እንደሚያደርጉት አስተማሩኝ ከሚሏቸው ሊቃውንት አባቶች የተማሩት ካለ ይንገሩን። የተነሳውን ዝብርቅርቅ አብራርተውና አፍታተው ለመግለጽ ካቅመዎ በላይ ከሆነ፤ የማያውቁትና ያልተማሩት ከሆኑ አንዳንድ ጊዜ ዝምታ ወቅ ነውና በዝምታወ ይቀጥሉ። 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ

ዝምታ ወርቅ ነው የሚባለው ባላወቁትና ባልተረዱበት ነገር እንደ ሰንበት ተማሪዎች ዘሎ መግባትን ለመቃወም እንጅ፤ የተማሩትንና  ያመኑትን፤ ውሎ አድሮ ለህዝብ መገለጡ አይቀርምና ቢገለጥ የማያሳፍረውን የመናገር ደግሞ  የሊቃውንት የምሁራን የክርስቲያኖች ነውና።ምን ብሎ እንዲጠይቅ የሚያደርግ ነው። ይልቁንም የቤተክርስቲያኒቱ አካል ነኝ ለሚል በግሌ ምን ማድረግ ይገባኛል? ብሎ ራሱን እንዲጠይቅ የሚገፋፋና የሚያስገድድድ ይመስለኛል።የተዋህዶው ሃይማኖት እምነት መሠረት የሆነው ነገረ መለኮት የተዛባበት ጥያቄ ላይ የወደቀበት ወቅትነውና።

ይህ የምንገኝበት ዘመን እጅግ አስፈሪና አስደንጋጭ ጥያቄ ይቀሰቅሳል። እምነቱና ችሎታው ሳይኖራቸው ከቦታው ጋራ የተገናኘውን ክብርና ጥቅም ለመሰብሰብ ሲሉእየዘለሉ በገቡ ሰዎች ላይ የሚመጣው ፍርድ እጅግ በጣም ያስፈራል።ይህ የሜዳ ጨዋታ አይነት ጫጫታና ሁካታባቢሎናዊ ዝብርቅርቅ ምስቅልቅል ማንን እንመን?

ሰላም! ሻሎም!

 

4 Comments

  1. ወገኖቸ ኢትዮጵያውያን ተመልከቱት ይህን ሰይጣን ። ኣሁን ይህን ወሸት ኣጋኖ በማቅረብ ከወስጡም ከወጪውም ኣይደለሁም ገለልተኛ ነኝ የሚለውን ቀዳዳ ለማስፋት ነው። የክህነት ኣማላክ እግዚኣብሔር ይፈረድብህ። ኣሁን በዚህ እድሜ ሰው ኣስታራቂ ይሆናል እንጅ እሳት እየጫሩ ወንድሞችን ለማጋደል።ኣሁን ኣቡነ በርናባስ” ፍጡር ” ሲያስተምሮ ጀሮህ ሰምቷል። ኣንተ ሀሳዊ መሲህ ቀኖና ኣፍራሽ የራህን ውግዘት በግርግር ለመሸፈን። ገለልተኛ የሚለውን ከገሐነብም ከነገነትም ያልሆነ ስድና ዝርው መረን ልቅ የሆነውን ሱቀ በደሬቴ ሕጋዊ ለማሰመሰል። ወንኖቸ ኣቡነ በርናባስም እንዶህ ኣላሉም በመዋለ ሥጋዊ ኣማልድዋል የጌትነቱ የአምላክነቱ ክብር ኣልጎደለበትም ከትንሳኤ በኃላ ማማለድ የለም ነው ያሉት ኣቡነ ፋኑኤልም የምሰጢረ ስጋዊን ትምህርት ኣለመጠንቀቃቸው ካልሆነ በስተቀር ብዙ የጎላ ልዮነት ኣይደለም። ኣሁን ይህ ሰይጣን ልዩነቱን የካህዲያን የአነ ኣርይዮስና የአንስጥሮስ ኣደረገው ተመልከቱ ይህ ክፉ ኣጋንንት ነው ወገኖቸ። ኣንድብቶ ጊዜ ጠብቆ ሰዎችን ሊጠቃ ትውልዱን ሊያደባድብ የተነሳ ኣጋንት። ኣስትራዮ የባቶቻችን ኣምላክ ይፍረድብህ። እዲህ ያለህ ኣጋንት መሆንህን ኣሁን ይበልጥ ተረዳሁት። አሁን ሀገሪቱ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታ ይህን ያክል ውሸት ቀላቅሎ በትውልዱ መላከል የሃማኖት ጦነት እንዲነሳ ማድረግ ተገቢ ነው። ሰማይ ወምድር ኣይለመንህ። ኣቡነ ማትያስን እጅግ ኣከብሩካቸው ኣንተ ኣንድ ጊዜ ሳይሆን ኣስር ጊዜ መወገዝ ያለንህ ነህ። በወንድሞች መካከል ጸብን የሚዘራ እሱ ኣጋንንት ነው ባንተ ኣያሁት። ኣሁንም ደግሜ እላለሁ ሰማይ መሬት ኣይለመንህ። ኣቡነ ፋኑኤል ከመቸ ጀምሮ ዘምድ ኣደረካቸው “ኣባ መላኩ ኣዲስ ተክል “ናቸው አያልክ ስማቸውን ስታጠፋ ኣልነበረም። ገና ቀለሙ ሳይደርቅ ብፁዕ ኣቡነ ኣካላቸው ነበርን ለማጋጨት ኣጋንንት።እኔ በዚህ ጉዳይ ላይ መልስ ሰጥበታለሁ ይህ ሰው መንፈስ ቅዱስ ባወቀ የኣጋንታዊ ባህሪው ይፈ ያሆነበት ነገር ነው ። ማንን እንመን ኣሁን ካህን ነኝ የሚል ሰው ይህን ይላል ፤ፈጣሪህን እመን አንጅ ማንን ልታምን ነው ሰዎች ላገልግሎት ተመረጡ አንጅ ንደፈጣሪ ልታማናቸው ኣይገባም ከሃዲ።

  2. I do not think anyone can win the “debate or arguemeant” on religious beleifs including the very interpretaion of the Great Book. Becuse if we drwaw ourselves into this theological or religious ideology or system of beleif and rigidly continue to fight who is the winner and who is the loser or who is sinful and who is blessed , we will end up destryoing the very feedom of human being given by nobody else but his or her crteator, God and God only .
    I do not know why we do not just teach or preach about what we beleive in and how we believe in rather than trying to condemn each other because we differ in the beleife syastem we have been accustomed or thought to ? Let’s be critical of each other’s way of teaching respectifully if necessary and leave the final choce and decison to each human being.
    It is the right thing to ask for explanation or further interpreation on what a given religious teacher or sect or domain has to say about his/her or its teachings or system of beleifs. But name calling and condemning someone as heretic/reformist or conservative, sinful or blessed, fake or genuine is against the very human freedom to have his or her own choice as long as he or she respects the freedom of othrs .

    Folks, fighting over who is a ture beleiver (I am not sure if there is one including those at the top ) whereas the country and her children are expereincing terrible hell right here in thier own homeland is totally nonsensical. I am sorry to say this ; but that is the way it is!!
    As I always want to beleive , the very sacrifice Jesus Christ paid is not merely to tell us that we will be blessed and go to heaven for the simple reason we confess that he has died and reserected . To my understanding, what is the most glorious messge He has showed us has been and is how love and compassion reqires action , not millions and millions of words of rhetoric or a highly gargenized doctrine and rule . Yes, it is what we do and how we do in this world that would take us to heaven , not what we simply preach and pray or fight over who is true beleiver and who is heretic .
    As the follower of the Ethiopian Orthodox Church which has its own multi -faceted and truly great values, I strongly belive that the very sufferings of the innocent people of Ethiopia is not a punishment from God at all although we cannot escape His fatherly correctional measures . I want to argue that it is mainly becuse of our terrible failre to use the very power house of knowledge and action (brain) God has given us properly and genuinely that we are witnesing the painfully dehumanizating political sitution and devastaing socio-economic reality in our country. And as far as the very mission of our religious leadres and preachres is concerned, they have totally failed the people of Ethiopia and it is totally wrong if not terribly disingenous to use God as an execuse for our own stupidity of inaction . I would argue to the exent that it is becuse of our religius leadres and other members of a clergy (with ver few exception) that the untold sufferings of the people looks endless, not becuse of God as there is no shch merciless God at all.
    I do not know why we make big noises or get over sensitive whenever we deal with very disappointing behaviours and actions of religious leadrses and preachers. Can’t we challenge them whenver they try to draw us into the debate or arguement about who inherits heaven or hell after death whereas all what we practically do on this planet ( hard work, honsty, trustworthiness, love, comopassion, togethrness, generousity, peace, selflessnes, ….) is the only way to a much better life after death ? I strongly beleive we can and shoud!! God cannot and should not be used as an execuse for our own clumsy and disingenous way of discharging our responsibilites.

    let’s fight for the very freedom of the innocent people of Ethiopia with our couragous and genuine way of communication with God so that He helps all our efforts to bring about a system in which we live in peace, love, compassion, fredom, justice, unity and shared prosperity.
    With all due respect!!

  3. “አመድ በዱቄት ይስቃል”
    መልስ ብለህ ቀሲስ አስተርአየን እየዘለፍክ የጻፍክ (የጻፍሽ) Mengesha
    October 11, 2017 at 9:21 am
    የቀሲስን ፎቶ ስታይ ለሰዎች የተቆረቆርክ መስለህ የራስህን ስም ማሳሳቻከራስህ ደብቀህ፤ ብዙ ማሳሳቻ የተረዳሁትስድብህ ፀሊምና እኩዪነትነው የእኩይነት መንፈስ ድምጸ ቀብሮ እንዲሰለጥንብን ደንብ የለም።የአስቆረቱ ይሁዳ የስድብ ትረካ፤ ከትዕቢተኛነቱ እስከ ጌታዉን ክህደት የደረስዉን ያልተባረከ ርጉም የሚገርም የስድብ ምሩቅ ነህ የቆሸሸ አንደበት በመሆንህ በዚህ በኛ ዘመን ባንተ የዕዉቀት ዕድሜ መቸ ነው የሚታሰበው?ለመሆኑስ እንዲህ የመሰለዉን የተዋህዶው ሃይማኖት እምነት መሠረት የሆነው ነገረ መለኮት አስትምህሮ መፉለስ አንተን የመሰሉ ሰወች ለሁሉ ተስፋ በሆነችዉ ቤተክርስቲያን ላይ የምትፈጽሙት መናፍቅአዊ ደባ በዚህ እኩይነት አትራፊው ማን ይሆን?በቆሸሸ አንደበት በእኩይነት መንፈስ የሰይጣንን አየር በመርጨትህ፤ ካቅምህ በላይ ራስህን አውጥተህ ወድቀሀል። ጽሁፉን ጨርስህ እንዳታነብ ዓይንህን ጋርዶብህ፤ ድንቁርናህንና በውስጥህ ያለውን ጥላቻ በማዝረክረክ የራስህን ማንነት በራስህ እንድትመሰክር በቀሲስ ላይ ያዘልከውን ጥላቻ በራስህ ላይ የሚገርም የስድብ ምሩቅ ነህ ።
    “ኣቡነ ፋኑኤልም የምሰጢረ ሥጋዊን ትምህርት ኣለመጠንቀቃቸው ካልሆነ በስተቀር ብዙ የጎላ ልዮነት ኣይደለም” አትልም ነበር። እርቅ የለም ብለው እስከመወሰን የደረሱበት ጠንቅቀው በማያውቁት ምሥጢረ ሥጋዌ ከሆነ። “ኣባ መላኩ ኣዲስ ተክል መሆናቸውን በራስህ እየተናገርክ መሆንህን የማትረዳ ነህ። “አዲስ ተክል ናቸው አያልክ ስማቸውን ስታጠፋ ኣልነበረም” እያልክ ቀሲስን ልትነቅፍ ትሞክራለህ። ስም ማጥፋት የሚባለው የቀረበውን ሳትረዳ በግል ስሜትና ጥላቻ አንተ አሁን በቀሲስ አስተርአየ ላይ ያለ ማስረጃ የምትናገረው እንደሆነ አይገባህም? እንዴት ይህን መረዳት ተሳነህ? “ኣቡነ ፋኑኤልን ከመቸ ጀምሮ ዘምድ ኣደረካቸው” እንዴት ልትል ቻልክ? የት ቦታ ነው ቀሲስ አቡነ ፋኑኤልን ዘመዴ ነህ ያሏቸው? በሁለቱ መካከል መኖር ያለበት የዝምድና ትርጉሙ ምንድነው? ተብለህ ብትጠየቅ መልስህ ምንድነው?
    በዚህ ጉዳይ ቀሲስን ልትወንጅላቸው የፈለከው በቀሲስ ላይ ምን የተለየና የግል ጥላቻ ቢኖርህ ነው? አዲስ ተክል ተብሎ በአባ ፋኑዔል የተወሰደው ውሳኔ ባይረሳም ባይዘነጋም ፤ እንደገና እንዳዲስ እንዲነበብ ያደረከው አንተው ነህ። “ገና ቀለሙ ሳይደርቅ ብፁዕ ኣቡነ ኣልካቸው” በማለትህ የደረቀውን ቀለም አንተ ራስህ እንዳዲስ ሆኖ እንዲቀርብ እያደረከው ነው። ቀሲስ አስተርአየ ይህን በሉ፤ ይህን አትበሉ እያሉ ነግረዋቸዋል ልትለን ነው። የለያዩዋቸውና እርስ በርሳቸው እንዲወራረፉ ያደረጓቸው ቀሲስ ናቸው ብለው እነ አባ ፋኑኤል ነገሩህ?
    እነ አባ ፋኑዔል የሚወራወሩበትን ሀሳብ የግብጽ የሮም ሳይሉ ካብነቱ በሰሙት በተማሩትና በተረዱት እንዴት ያስታርቁታል? ያስረዱን ብሎ መጠየቁስ ያስነውራል?። በሰይጣናዊ ርኩስ መንፈስ በሰከረ መንፈስ ቸኩለህ ጥላቻህን ተፋህ። ችሎታው ካለህ ቀሲስ የተጠየቁትን እስኪመልሱ ታግሰህ ስህተት ካገኘህባቸው ከመሳደብ ተቆጥበህ ልክ አይደሉም፤ ማለት ለምን አልፈለክም? ወይም በምትናገረው ቆሻሻ ንግግርህ እሳቸው እንዳይናገሩ ለማሸማቀቅ ነው። ራሳቸው በግልጽ የተወዛገቡትም፤ ካፋቸው በወጣው ከተማመኑ ቀሲስ ብቻ አይደሉም ማንም ቢናገር አዳምጠው ትክክል ነው። ትክክል አይደለም ከማለት ሌላ አይናገሩ በማለት ካንተ ጋራ የሚስማሙ አይመስለኝም። ይህ የማፈን ጠባይህ ባገር ቤት የተለመደ እኩይ ተግባር እንደሆነ ሁሉም የሚያወቀው የተለመደ ነውና አትድከም።
    ያቦን ቅጠል እንደበላች ፍየል አንተ ለፈለፍክ እንጅ፤ ቀሲስ ዝም ብለው ሊያልፉትም ይችላሉ። ምን ዓቅበጠበጠህ? ከዚህ ቀደም በተሰማቸው ነገር ሁሉ በቃላቸውም በጽሑፎቻቸውም እንደመሰከሩት
    በረሳቸው ህሊና ያደርጉታል። ለህሊናቸው ካልመሰላቸው ይተውታል። እኔ ያድርጉት ስላልኳቸው አያደርጉትም። አንተም አያድርጉት ስላልካቸው ከማድረግ ወደ ኋላ የሚሉ አይመስለኝም። ይመስክሩ ብየ እኔ ያቀረብኩት ጥያቄ ይህን ያህል ደም የሚያፈላ ነው ተብሎ የሚገመት አይመስለኝም። “እኔ በዚህ ጉዳይ ላይ መልስ እሰጥበታለሁ” የምትይው ወይም የምትለው እርስ በርሳቸው የተወራወሩት ያስነሳውን ለቀሲስ አስተርአየ ያቀረብኩትን ጥያቄ ከሆነ፤ የፈለግነውን ትምህራታዊ መልስ ካንተው በማግኘታችን ደስታውን አንችለውም። የምንፈልገውም እሱ ነውና ንገረን።
    አባ ፋኑዔል አዲስ ተክል ላለመሆናቸው ልታስረዳን ከሆነም ንገረን እንስማህ። ንግግርህን በጥሞና ለተመለከተው፤ አባ መላኩ እንዲባሉልህ የምትፈልግ ሰው ትመስላለህ፤ ሀሳብህ ከዚህ የተለየ ከሆነ በግል ጥላቻህ ቀሲስ አስተርአየ ተሸማቀው ዝም ይላሉ ብለህ ገምተህ ያደረከው ትመስላለህ። “አሁን ሀገሪቱ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታ ይህን ያክል ውሸት ቀላቅሎ በትውልዱ መላከል የሃማኖት ጦርነት እንዲነሳ ማድረግ ተገቢ ነው? ማለትህ፤ ያንባቢን መንፈስ ለመቀልመም ያመነጨኸው እኩይ መንፈስ ነው ከማለት ።በጥላቻ ቁስል በሚመግል በዚህ ጭንቅላትህ ስለሀገር ታስባለህ ብሎ ማነው የሚገምትህ? አገሪቱን አጣብቂኝ ውስጥ የከተታት ማነው? ቀሲስ አስተርአየ ናቸው ልትለን ነው?
    “ኣቡነ ማትያስን እጅግ ኣከብሩካቸው” የምትለው ዛሬ ነው ያከበርካቸው? አቡነ ማትያስ እስከ ዛሬ ላንተ ማን ነበሩ? ያከበርክበትስ ምክንያትህ ምንድነው? “ኣንድ ጊዜ ሳይሆን ኣስር ጊዜ መወገዝ ያለብህ ነህ” የምትለው ማንን ነው? ስለ ውግዘት ብታውቅ ይህን ቃል አትጠቀምም ነበር። ሰው አስር ጊዜ አይወገዝም። ቀሲስ አስተርአየ አስር ጊዜ አይደለም። አንድ ጊዜስ ማነው ያወገዛቸው? አውጋዡ ማነው? የት ቦታ መቼና በምን ምክንያት ነው አቡነ ማትያስ አወገዝኩ ያሉት? ያወገዙበትን ምክንያትና ውግዘት ያሳለፉበትን መረጃ እስኪ አምጣው። ይህንን ቃል ከየት አመጣሀው?
    “ማንን እንመን” ብየ ያቀረብኩት ጥያቄ ከገባህ፤ ሰዎቹ እርስ በርስ ስለሚወዛገቡባቸው የተላየዩ ነገሮች ማለቴ ነው እንጂ ስለፈጣሪ አይደለም። አባ ፋኑዔል የተናገሩትን እንመን፤ ወይም አባ በርናባስ የተናገሩትን እንመን ማለት ወይም ሁሉም አይታመኑም ማለት ሲገባህ፤ የተነሳውን መሰረታዊ ሀሳብ ጠምዝዘህ፤ ፈጣሪህን እመን ማለትህም በጥላቻና ባሉባልታ መስከርህን ያስረዳል። ከላይ የተጻፈውን ሳታይ የቀሲስን ፎቶ አስቀድመህ በማየትህ በሳቸው ላይ ያለህ የግል ጥላችህ ተቀስቅሶብህ ከሆነ ጽሁፉን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ አንብበህ ሀሳቡን ተረድተህ ፎቶውን ብቻ አይቼ ነው ብለህ የመሳሳትህን ሀለፊነት ስትወስድ ብቻ ነው። ለሰዎች የተቆረቆርክ መስለህ የሰይጣንን አየር በመርጨትህና ለተነሳው ሁሉ ውዝግብ መልስ አለኝ ብለህ ራስህን በማስገባትህ፤ ካቅምህ በላይ ራስህን ከአንጠለጠልክበት ከገደል ጫፋ ተመዘግዝገህ ወድቀሀል። አገራችንና ቤተ ክርስቲያናችንን እያመሰ ያለው ይህ አይነት አስተሳሰብ ባላቸው ሰዎች ነው። እኔ አሁን የተነሳውን ውዝግብ እንዴት ይመለከቱታል? የግብጽ የሮም ቤተ ክርስቲያን ሳይሉ ኢትዮጵያውያን መምህራን ያስተማሯቸውን እንዲገልጹልን ብየ ለቀሲስ አስተርአየ ያቀረብኩት፤ ከዚህ ቀደም ከ8 ዓመት በፊት ነሀሴ 15 ቀን 2009 ዓ/ም የከንሳስ መድሀኔዓለም ከቀሲስ ጋራ በመቆም ለመላው እምነት ተከታይ ያቀረቡትን ይህንን ጥሪ በመመልከት ነው። ከገባህ ተመልከተው። ስድብህ ንስሃ የሚያስፈልገው የከፋ ሃጢአት ሁኖ ይሰማኛልና እግዚአብሔር በቸርነቱ ይቅር ይበልህ። “አመድ በዱቄት ይስቃል”
    ገብርኤል ብዙነኀ

  4. men Manen enmen yelalu,!!! erswo yetemarut men yelal?
    Demos ENDE SENBETTEMARI!!? MEN MALET NEW
    BETAEKUT SENBET TEMARI LENANTE KURAT NEW!!!!

Comments are closed.

Share