ድርድር ከወያኔ ጋር? የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና መጪው ጊዜ! (ለውይይት መነሻ) – ባይሳ ዋቅ-ወያ

ይህንን የግል አስተያየቴን በጽሁፍ ካማስፈሬ በፊት ዛሬ አገራችን የምትገኝበትን ሁኔታና የወደፊት ዕጣዋ ምን ሊሆን ይችላል በሚለው ሃሳብ ላይ ለረጅም ጊዜ በአዕምሮዬ ሳወጣና ሳወርድ ቆይቻለሁ። እንደኔው ጉዳዩ የሚያሳስባቸው ብዙ እንዳሉም ስለማውቅ ጭንቀቴን በውስጤ ዓምቄ ከምኖር ባጋራቸው ምናልባትም በውይይት ሂደት ወደ አንድ የጋራ መፍትሄ ልንደርስ እንችላለን ብዬም ስላሰብኩ ይህንን ለውይይት መነሻ እንዲሆነን ያህል ለመጻፍ ወሰንኩ። ዓላማዬም በተበታተነ መልኩ በየቦታው የምንወያይባቸውን ያገራችንን የፖለቲካ ቀውስ ከተቻለ ባንድ መድረክ ላይ በማምጣት ቅርጽ ያለው ውይይት እንዲካሄድበት ነው። በመሆኑም ይህ ጽሁፌ ውይይቱ በምን ዙርያ መካሄድ እንዳለበት ለመጠቆም እንጂ ሳይንሳዊ ጥናት ስላልሆነ ራሱ የውይይት ነጥብ እንዳይሆን ከወዲሁ ለማሳሰብ እወዳለሁ። የማቀርባቸው ሃሳቦች ሙሉ በሙሉ ትክክለኛ ናቸው ወይም ሊከሰቱ ይችላሉ የሚል መቶ በመቶ የሆነና የተረጋገጠ ሂሳባዊ ስሌት የለኝም። ከፊት ለፊታችን የተጋረጠብንን ቀውስ አሸንፎ በድል አድራጊነት ለመወጣት ሂሳባዊ ስሌት ቢኖርማ ኖሮ ውይይትም ባላስፈለገም ነበርና!

የዚህ ጽሁፌ ጭብጥ፣ አገራችን አደገኛ ወደ ሆነ የርስ በርስ ግጭት እያመራች እንደሆነ የሚጠቁሙ ቅድመ ሁኔታዎች እየታዩኝ ስለሆነና ያንን አደጋ ደግሞ ለማስወገድና ሰላምና መረጋጋትን አምጥቶ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን የመገንባት ኃላፊነት የሚሰጠውን የሽግግር መንግሥት የማቋቋም አስፈላጊነት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ዕውን ሆኖአል የሚለው ነው። ይህን የሽግግር መንግሥት መመሥረት ደግሞ ተግባራዊ ለማድረግ በመጀመርያ ደረጃ ተቃዋሚ ኃይሎችና ወያኔ ለድርድር ለመቅረብ ፈቃደኛ መሆነ አለባቸው እላለሁ። በዚህ ሃቅ ላይ ተመሥርቼ ነው የሚከተሉትን ሶስት ጥያቄዎች ለውይይት የማቀርበው፣

ሀ) ከወያኔ ጋር መደራደር አስፈላጊ ነው ወይ?

ለ) አስፈላጊ ነው ከተባለ፣ ከተቃዋሚ ኃይሎች ወገን ለድርድር የሚቀርቡትስ እነማን ናቸው?

ሐ) ተደራዳሪዎቹ የሚደራደሩበት የመደራደርያ ነጥቦችስ ምን ይመስላሉ?

 

የውይይት ነጥቦች ይሆናሉ ብዬ ከላይ ወደ ጠቀስኳቸው ሶስቱ ፍሬ ነገሮች ከማለፌ በፊት ግን በቅንፍ ውስጥ፣ ዛሬ አገራችን ያለችበትን ሁኔታ እንዲሁ ባጭሩ ብንመለከት የውይይቱን ወቅታዊነት በግልፅ ያሳያሉ ባይ ነኝ። የችግሮቹን ቅርጫት ክዳን ስንከፍት ከወያኔ ጋር ሥልጣን ለመጋራትም ሆነ ለመረከብ ተቃዋሚ ኃይሎች ከራሱ ከወያኔና ከርስ በርሳቸው ጋር መደራደር አለባቸው ወደሚለው መደምደሚያ ያደረሰኝን ዘርፈ-ብዙ አገራዊና ዓለም-አቀፋዊ ክስተቶችን ብንመረምር ከሞላ ጎደል የሚከተሉትን የችግር ልቃቂቶች የምናገኝ ይመስለኛል።

ሀ) ያገሪቷ ኤኮኖሚ ወያኔ በሁለት አኃዝ እያደገ ነው እንደሚለው ሳይሆን ከመቼውም ጊዜ በተለየ መልኩ ወደታች እያሽቆለቆለ ነው። እንደተለመደው አንድ-ሶስተኛው የአገሪቷ ዓመታዊ ባጀት የሚንቀሳቀሰው ከውጪ በሚገኘው ድጎማ ነው። ስለሆነም የኤኮኖሚ ዕድገት ተብሎ ሁሌም ለናሙና የሚወሰደው በአዲስ አበባና ሌሎች የክልል ዋና ከተሞች በመካሄድ ላይ ያለው የፎቅ ግንባታ ሥራ ለከተሞቹ ጊዜያዊ ውበት ከመስጠት አልፎ ለዜጎች ምንም ዓይነት ጥቅም ሊሰጥ አልቻለም፤ የእርሻ ምርቱም ካመት ወደ ዓመት እያሽቆለቆለ ነው። እፍኝ የማይሞሉ “ልማታዊ ገበሬ” ከሚባሉትና የመንግሥቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ ከሆኑት ግለሰቦች በስተቀር መላው የኢትዮጵያ ገበሬ ዛሬም ልክ ከመቶ ዓመት በፊት ይጠቀምበት የነበረውን ማረሻና ቀንበር ይዞ ተደጋግሞ በመታረስ ብዛት የነጠፈውን ማሳ፣ መንግሥት በግዴታ የሚያበድረውን ማዳበርያ እየበተነበት አርሶ የሚያገኛትን የምርት እፍታ “የማዳበርያ ብድር” እየከፈለ በቀሪው ደግሞ ቤተሰቡን በትንሹም ቢሆን እየመገበ፣ ራሱን ሳይኖር “ባለጊዜዎችን” እያኗኗረ ይገኛል።

ለ) ያገሪቷ የሃብት ክፍፍል ከመቼውም ጊዜ በላይ የተዛባ ነው፤ እጅግ በጣም ጥቂቶቹ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ እየበለጸጉ ሲሆን ሰማንያ አምስት በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሞ ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ በታች ይገኛል። በጥቂት “ዘመን አመጣሽ” ሃብታሞች በሞኖፖሊ የተያዘው ብሄራዊ ኤኮኖሚ፣ ብሄራዊ የሃብት ክፍፍልን በጣም ያዛባ ከመሆኑም በላይ “ባለጊዜዎቹ” በህገወጥነት ያካበቱትን ሃብት ለማካፈልም ሆነ ካሁኑ የተለየ የኤኮኖሚ ፖሊሲ ቢቀየስ እንደሚጎዳቸው ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ወያኔ ሥልጣን እንዲለቅ በጭራሽ አይፈልጉም።

ሐ) የመለስ መሞት በኢህአዴግ ላይ ከፍተኛ የአመራር ችግር የፈጠረ ይመስላል፤  አንድ ጠንካራና የተማከለ አመራር ሊሰጥ የሚችል “ቆራጥ” መሪ በመጥፋቱ ፓርቲው ከርቀት ሲያዩት አንድ ወጥ ይምስል እንጂ ከውስጥ ግን የተከፋፈለና የተቦረቦረ ነው። ስለሆነም እያንዳንዱ ቡድን የየራሱን ምጣኔ ህብታዊ ጥቅም ያሳድዳል እንጂ አገሪቷ ያለችበትን ቀውስና ሊከተል የሚችለውን አደጋ በቅጡ ገምግሞ መፍትሄ ሊያቀርብ የሚፈልግ ያለ አይመስልም። ክፍፍሉ እንዳለም ሆኖ ግን ሌሎች ተቃዋሚዎችን በተመለከተ፣ ወያኔ “የአባላቱን መብት ለማስጠበቅ” እንደ አንድ አካል ሆኖ ከመከላከል ወደ ኋላ እንደማይል ብዙዎች የደመደሙት ጉዳይ ነው። በዚያው አኳያ ደግሞ፣ ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ “ይጠላናል” በሚል ፍራቻ፣ከዚህ “የጋራ ጠላት” “ራስን የመከላከል” ፖሊቲካቸው አንድ ወጥ ያስመስላቸዋል።

መ) የፖለቲካው ሁኔታ በጣም አወዛጋቢ እየሆነ  ሄዷል። ባንድ በኩል ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን ሁሉ እየኮረኮመና እየጎነተለ ለማንበረከክ ብርቱ ጥረት እያደረገ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የበደሉ ብዛት ከልክ በማለፉ ሰፊው ሕዝብ ከቁጥጥር ውጪ በመሆን በአደባባይ የመንግሥቱን የጸጥታ ኃይሎች ጥይት በመጋፈጥ ብሶቱን እየገለፀ ነው። የመልካም አስተዳደር እጥረት ባገሪቷ ለተከሰቱት ሕዝባዊ ሁከቶች መንስዔ መሆናቸውን መንግሥት አምኖ የተቀበለ ቢሆንም ተጠያቂ የሆኑትን የመንግሥት ባለሥልጣናትና መንግሥታዊ አካላት ላይ እርምጃ ወስዶ የጎደለውን እንደማሟላት ፋንታ አመፁን አነሳስታችኋል በማለት በብዙ ሺህ በሚቆጠሩ ወጣቶች ላይ የወንጀል ክስ መሥርቶባቸዋል። እጅግ በጣም ብዙ የሆኑ ወጣቶች ከዩኒቬርሲቲ እየተመረቁ ሥራ በማጣታቸውና ቅሬታቸውንም ካሰሙ ደግሞ ታሥሮ መማቀቅ እንዳለ ስለሚያውቁ፣ አብዛኛዎቻቸው የተገኘውን ዕድል በመጠቀም ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ካገር እየተሰደዱ ነው፤ ወጣት ሴቶችም የተሻለ ሕይወት ፍለጋ ብለው ወደ ዓረብ አገሮች እየፈለሱ ሲሆን ብዙዎቹ ለትልቅ አደጋ ተጋልጠዋል።

ሠ) የማሰብ የመናገርና የመጻፍ መብቶች መገፈፍ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል፤ የፖለቲካ እሥረኞች ቁጥር ከግምት በላይ ሆኗል፤ በእሥረኞች ላይ የሚፈጸመው የማሰቃየት ተግባር ከኢትዮጵያውያን አልፎ የዓለሙን ማኅበረሰብ እጅግ በጣም እያሳሰበ ነው። ፍርድ ቤቱ እንዳለ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ስለሆነ ዳኞች ፍትሓዊ የሆነ ፍርድ መስጠት አይችሉም። የሰው ልጆችን መብት መከላከልን በተመለከተ ለብዙ ዓመታት በተለይም ከተመድ (UN) መቋቋም በኋላ የግንባር ቀደም ሚና ሲጫወቱ የነበሩት የምዕራብ አገራት የሞራል በላይነት ማጣትና ዓለም-አቀፋዊውን ሽብርተኝነትን ለመከላከል ብሎም ለማጥቃት በሚል ሰበብ የምዕራብ አገራት የጀመሩትን የዜጎችን መብት መጣስ እንደ ኢትዮጵያ ላሉት አምባገነን መንግሥታት የየራሳቸውን ፀረ-ሽብር ሕግ እያወጡ የዜጎችን መብት መግፈፍ በሚያስከፋ መልኩ እንዲቀጥል ገፋፍቷል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለይቶና አቅዶ የገጨንን ዘር ጨፍጫፊ ሾፌር ለቀው ተሽከርካሪውን (የነጂውን) እንዴት እንክሰሰው? - ወንድእጥር መኮነን 

ረ) ያገሪቷ መከላከያ ሠራዊት እጅግ በጣም በከፋ ሙስና ውስጥ እንደተደፈቀ ይነገራል። በቱርክና በፓኪስታን ሞዴል የተጠፈጠፈው ያገሪቷ ሠራዊት “ራሱን በራሱ ፋይናንስ ማድረግ አለበት” ተብሎ በመለስ ስለተፈረጀ፣ እጅግ በጣም ብዙ መከላከያ ነክ ፕሮጀክቶች ለመከላከያ ሠራዊቱ ያለምንም ጨረታ ስለሚሰጠው ትኩረቱ ያገሪቷን ዳር ድንበር መከላከል ላይ ሳይሆን በመከላከያ ሰራዊቱ ስም ቁንጮዎቹ ያከማቹትን ሃብት ከህዝብ ወደ መከላከል ዞሯል።

ሰ) የሕወሃት “የከፋፍለህ ግዛ” ፖሊቲካ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አኳኋን ሥራ ላይ እየዋለ ነው። ምንም እንኳ በአማራና በኦሮሞ ህዝብ መካከል በፊውዳሉ ዘመን የነበረውን ቅራኔ እንደገና ነፍስ ሊዘራበት ፈልጎ ባይሳካለትም ሌሎች አናሳ ብሄረ ሰቦችን በስውር አደራጅቶ ጸረ ኦሮሞና ጸረ አማራ ግጭት እየቀሰቀሰ ይገኛል። ያም ሆኖ ግን የወያኔ የመከፋፈል ፖሊቲካ ሳያግዳቸው በብሄሮች መካከል እየተከሰተ ያለው የመቀራረብ ሁኔታ ተስፋ የሚጣልበት ጉዳይ ነው። በአማራና ኦሮሞ ክልላት ተካሂዶ በነበረው ዓመጽ ወቅት የሁለቱም ክልል ሕዝቦች ያሳዩት የነበረው ፍጹም የመግባባት መንፈስ አስደሳች ነበር። ለወደፊትም የጽንፈኛው ዲያስፖራ ከፋፋይ ፖሊቲካ ገብቶ ካላወከው በስተቀር ይህ የአማራና የኦሮሞ  ሕዝቦች መተባበር እየተጠናከረ እንደሚሄድ ከወድሁ ተገምቶአል።

ሸ) የብሄር ጥያቄን በተመለከተ፣ በፖሊቲካ ድርጅቶች መካከል ያለው የአስተሳሰብ ልዩነት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ፖላራይዝድ ሆኖአል። “የኢትዮጵያ ህዝብ ድሮም አንድ ነበር አሁንም አንድ ነው፤ ለወደፊቱም የሚበጃት አሃዳዊ አስተዳደር ነው፣ለአንድነቷም ጋሻ ጃግሬዎቹ እኛ ብቻ ነን” በሚሉ ጥቂት ኤሊትና የዚህን ተቃራኒ ሃሳብ በሚያራምዱት “ለኢትዮጵያ  የሚበጃትና ብቸኛው መፍትሄ ፌዴራላዊ አስተዳደር” ነው በሚሉ የብሄር ድርጅቶች መካከል በጣም የሰፋ ገደል አለ። ትንሽ የሚያዝናና ነገር ቢኖር የብሄር ጥያቄ ሁሌም “ፊደል የቆጠረው” የአናሳ ቡድን እንጂ የሰፊው ህዝብ ጥያቄ ባለመሆኑ፣ ባገር ቤት ደረጃ በብሄሮቹ መካከል ጥያቄው ወቅታዊ ያለመሆኑ ነው።

 

መሆን ያለበትና የነበረበት፣

ህብረተሰብ፣ በፖሊቲካ ህይወትና አገር አስተዳደር ለዘመናት ካካበተው ልምድ በመነሳት ዛሬ በኢትዮጵያ ያለውን ማህበረሰባዊና ፖሊቲካዊ ቀውስ ያገናዘበ ሰው የሚከተለውን ሊል ይችላል። እንደ ወያኔ አናሳ የሆነና ያገሪቷን ፖሊቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ሕይወት ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠረ መንግሥት አንድ ደረጃ ላይ ህዝቡ ከዳር እስከ ዳር ተባብሮ “አልፈልግህም” ብሎ ካመጸበት በጣም ቀላል የሚሆነው ቁርጠኛ ውሳኔ፣ የፖሊቲካ  ሥልጣኑን በሰላም አስረክቦ፣ ሰርቀውም ሆነ በአግባብ ያካበቱትን ሃብት ይዘው ከፖሊቲካ መድረክ መውጣት ነበር። የደቡብ አፍሪቃ አናሳ የነጭ መንግሥት ያደረገው ያንን ነው። ህዝባዊ ዓመፁ እየጠነከረና እየሰፋ በሄደበት ጊዜ አናሳው መንግሥት ከጠላቱ ከ ANC ጋር በድርድር ጠረጴዛ  ዙርያ  ለመቀመጥ ወሰነ። በድርድሩም ሂደት ሥልጣኑን በሰላም በማስረከብ አገሪቷን ከጥፋትና ዕልቂት አዳነ። ዛሬ የፖሊቲካ ሥልጣኑን እነዙማ “ይዘው” በአለም መድረክ ሲፎልሉበት ነጮቹ ግን ራሳቸውን ከፖሊቲካ አገልለው ያገሪቷን ኤኮኖሚ ግን ሙሉ በመሉ ተቆጣጥረውት ይገኛሉ። ዋናው ነገር አገሪቷ ከጥፋት ድናለች።

በሰብዓዊ ስሜት (common sense ?) የሚመራ ማንም መንግሥት የዛሬይቷን ኢትዮጵያ ሁኔታ ካጤነ በኋላ ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለድርድር ለመቅረብ አለበት ባይ ነኝ። ለወያኔ አባላትና ሥርዓት ተጠቃሚዎች ግን ይህ ሃቅ ለጊዜው የተገለጠላቸው አይመስልም። ዕብሪትና ድንቁርና ተደማምሮ በራሳቸው ላይ የተጫነባቸው ይመስል የፖሊቲካ ሥልጣኑንም ሆነ የኤኮኖሚ ዘርፍ ባለቤትነቱን ይዘው ለዘላለም የሚኖሩ እየመሰላቸው ካገር ውስጥም ሆነ ከውጪ የሚደወልላቸውን የሰላም ጥሪ ከመጤፍ የሚቆጥሩም አይመስሉም። ከዚያም በተጨማሪ ወያኔ በጥቅማ ጥቅምና በሙስና እጃቸውን አጨማልቆና በአፋላማ የያዛቸው በርካታ ግለሰቦችም የወያኔ ከሥልጣን መወገድ ማለት የነሱም የመጨረሻ በመሆኑ በተቻላቸው መጠን የወያኔን ዕድሜ ለማራዘም ሲታገሉ ይታያሉ። ይህ ግን የሚያዛልቅ ሂደት አይመስለኝም። ህዝባዊ ዓመፁ እየሰፋና  እየተጠናከረ በሄደ ቁጥር የወያኔ መሪዎች፣ ሥልጣን ካጋሩ ወይም ካስረከቡ አንዳችም አደጋ እንደማይደርስባቸው ዋስትና ካገኙ፣ “በክብር ለመሸኘት” (dignified exit) ለድርድር ለመቅረብ ፈቃደኛ ይሆናሉ ባይ ነኝ።

ወያኔ ለድርድር ዝግጁ ያለመሆኑን ያህል ተቃዋሚ ኃይሎችም ባብዛኛው ለድርድሩ አስፈላጊነት አስተዋጽዎ ሲያደርጉ አይታዩም። አንዳንዶቹ ወያኔን በተባበረ ክንድ ለማሸነፍ በስትራቴጂ ደረጃ ጊዜያዊ ወዳጅነት ሲመሰርቱ ሌሎች ደግሞ ከመሰሎቻቸው ጋር “የሽግግር መንግሥት“ ለማቋቋም ቅድመ ዝግጅት ከማድረግ አልፈን በአግባቡ ተደራጅተናል በማለት ራሳቸውን ይፋ ያደረጉ አሉ። ያገሪቷን ችግር ለመፍታት የሚቋቋመው የሽግግር መንግሥት የሚመሰረተው ግን ባሃሳብ በሚጣጣሙ ግለሰቦችና ቡድኖች መካከል በሚደረገው ስምምነት ሳይሆን የተለያየ አስተሳሰብና አቋም ያላቸውን ድርጅቶችና ቡድኖችን ሁሉ በማቀፍ ነው። በንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ፣ ያ አልበቃ ብሎ፣ ሌሎች ደግሞ ባገሪቷ ላይ በማንዣበብ ላይ ያለውን አደጋ እንዴት በጋራ ሆነን በሰላም እንፍታው እንደማለት፣ ምንም ዓይነት መፍትሄ ሊያመጣ የማይችለውንና  አወዛጋቢ የሆነውን ያለፈን የታሪክ ትንተና ወደ ኋላ ተመልሰው ከተቀበረበት ጎርጉሮ በማውጣት፣ በሱ ላይ በመወያየትና በማወያየት “የታሪክ ታጋች”  – hostage – ሆነው ዛሬን ሳይሆን ትናንትን እየኖሩ ይገኛሉ። ያም ሆኖ ግን ሁላቸውም ያለማወላወል በወያኔ ከሥልጣን መወገድ ቢያምኑበትም፣ ወያኔን እንዴት ከሥልጣን መድረክ እናወርደዋለን ወይም እንዴት አርገን ለድርድር እንዲቀርብ እናስገድዳለን፣ ወይንም ደግሞ ወያኔ በተፈጥሮ ግዴታም ሆነ በውጪ ግፊት ዛሬ ከሥልጣን ቢወርድ፣ ድህረ ወያኔዋን ኢትዮጵያ ማን ነው ተረክቦ የሚመራት በሚለው ላይ አንዳችም የጋራ ነጥብ የላቸውም።

አዎንታዊ ክስተቶች፣

በተቃዋሚ ድርጅቶች መካከል ሊከሰት ያልቻለውን የጋራ ነጥብ ጉዳይ ወደ ጎን ብንተውና ያገር ቤቱን ነባራዊ ሁኔታ ስናጤነው በጥቂቱም ቢሆን የሁኔታዎችን መለወጥ አይቀሬነት የሚያመለክቱ አዎንታዊ ክስተቶች አሉ፣

አንደኛው፣ ወያኔ እንደ ማንኛውም ከዚህ በፊት በታሪክ እንደታዩት መንግሥታት ዲያሌክቲካዊ ህግን ተከትሎ አንድ ቀን መሞቱ የማይቀር መሆኑ ነው። የማይታወቀው ነገር ቢኖር ግን የመሞቻው ቀንና የአሟሟቱ ሁኔታ ነው። በጠብመንጃ ኃይል ተደግፈው “በአሸናፊነት” ሥልጣን የያዙና ሁሉንም ያገሪቷን ችግር በጠብመንጃ ድጋፍ የሚፈቱ የሚመስላቸው አንጋፋዎቹ የወያኔ አባላት የተፈጥሮ ሕግን ተከትለው በቅርብ ጊዜ ውስጥ ማለፋቸውም እርግጠኛ ነው። በቅርቡ ኢሕአዴግን የተቀላቀለውና ለወደፊትም የሚቀላቀለው ደግሞ የትግራይ ተወላጅን ጨምሮ ከጫካ ያልመጣ፣ በጠብመንጃ ብርታት የማያምንና “በአሸናፊነት” ስሜት የተሞላ ስላልሆነ፣ እስካሁን በኢህአዴግ አባላት ድርጅቶች መካከል ይታይ የነበረው “የፊትና የኋላ ረድፍ” የደረጃ ተዋረድ የሚቀር መሆኑ ሌላ አዎንታዊ ክስተት ነው። አዲሶቹ የኢህአዴግ አባላት አብዛኞቹ እንደ አንጋፋዎቹ “ታግለው በጠብመንጃ ብርታት አሸንፈው” የመጡ ስላልሆነ በመካከላቸው ዕዳ ያለበት አባል አይኖርም። “ታጋዩና አሸናፊው” አንጋፋው ትውልድ በተፈጥሮ ሂደት ቦታ ሲለቅ አዲሱና እኩልነት የሚሰማው ወጣቱ የኢህአዴግ አባል ለለውጥ ዝግጁ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለኝ። ይህንን ሃቅ ነው እንግዲህ ተቃዋሚ ኃይሎች ከግንዛቤ ለመክተት ያልቻሉት!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኮንጎ፣ የኮሪያ ዘማቾች እና የኢትዮጵያ አብዮታዊ ሰራዊት ሁሌም በክብር ሊዘከሩ፣ ሊታወሱ  ይገባቸዋል!!

ሁለተኛው፣ በተለያዩ ብሄሮች በተለይም በኦሮሞና በአማራው ህዝብ መካከል ከአንድ ምዕት ዓመት በላይ በያኔው የገዢ ሥርዓት ሰፍኖ የነበረው ጥላቻ የደርግን የመሬት ዓዋጅ ተከትሎ የከሰመ ቢሆንም ወያኔ ግን በተቻለው መጠን በህዝቦች መካከል መቀራረብና ብሎም ወዳጅነት እንዳይመሰረት የተቻለውን ሁሉ ቢያደርግም ህዝቦቻችን ግን ያንደኛው መብት መገፈፍ የሌላኛውም መብት መገፈፍ ብሎ በመነሳት የወያኔን የከፋፍለህ ግዛ ፖሊቲካ አሽቀንጥሮ መጣሉ ተስፋ ከሚጣልባቸው አዎንታዊ ክስተቶች ዋነኛው ነው ቢባል የተጋነነ አይሆንም።

የኢትዮጵያ የፖሊቲካ ተቃዋሚ ኃይሎችና በአስቸኳይ መደረግ ስላለባቸው ነገሮች

የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ኃይሎች በሁለት ጎራ፣ ማለትም ብሄራዊና (national) አገር-ዓቀፍ (multi-national) ብሎ መመደብ ይቻላል።  ሁላቸውም ያለማወላወል የሚስማሙበት አንድ ነገር ቢኖር ወያኔን ከሥልጣን ለማስወገድ ሲሆን ከወያኔ በኋላ ሊኖር ስለሚችለው መንግሥታዊ ሥርዓት ወይም አወቃቀር ግን እንኳን ተስማምተው የጋራ አቋም ሊወስዱ ይቅርና በየግል ድርጅታቸው ውስጥ ከአባሎቻቸው ጋር እንኳ የተወያዩበት አይመስልም። ይህ ዋነኛውና ያለመዘግየት መፈታት ያለበት ቀዳማዊ ችግር ይመስለኛል።

ያም በመሆኑ ያገራችንና የህዝባችን ጉዳይ ያገባናል ለምንል ሰዎች የሚከተለውን ጥያቄ ማቅረብ እሻለሁ፥ ከላይ እንዳልኩት ኢህአዴግ እንደማንኛውም መንግሥት በዲያለክቲካዊም ሆነ በሰው ሰራሽ ምክንያቶች አንድ ቀን ወይ ህልውናውን ያጣል ወይም ደግሞ መልኩን ቀይሮ ኑሮን ይቀጥላል። ታዲይ ወያኔ በዛሬ መልኩ አንድ እሁድ ዕለት መኖሩን አቆመ እንበልና ሰኞ ጧት በአራት ኪሎ  የሚሰየመው የኢትዮጵያን ህዝብ ለማስተዳደር የሥልጣን ኃላፊነት የሚረከበው አካል ማን ነው? ምንስ ይመስላል? ብለን ብንጠይቅ፣ እንኳን አግባብ ያለው መልስ ልናገኝ ቀርቶ መለስተኛ ውይይት እንኳ ያልተደረገበት መሆኑን እንረዳለን። የዚህ ጽሁፌ ዓላማም በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ያለምንም መዘግየት ጉዳዩ ይመለከተናል በሚሉ አካላት መካከል ውይይት መጀመር እንዳለበት ለማሳሰብ ነው።

የዛሬውን የኢትዮጵያ ሁኔታ ካለኝ የሙያ ልምድ አንጻር ስዳስሰው ሁለት ነገሮች ሊከሰቱ ይችላሉ ብዬ እገምታለሁ

አንደኛው፣ የማንመኘውና ግን ደግሞ ሊከሰት የሚችል ዕውኔታ፣ የወያኔ መሪዎች ልክ እንደ ጋዳፊ ወይም ሙባራክ የህዝብን ቁጣና ዓመጽ እየናቁ እስከ መጨረሻው የሥልጣን ወንበሩን ላለመልቀቅና ብሎም ህዝቡን አንበርክኮ ለማኖር ወስኖ የሞት የሽረት ትግል ማካሄድ ነው። ለብዙ ዓመታት ህዝቡን ለመግዛት የተጠቀሙበትን የሥልጣን አለንጋና ተደላድለው የኖሩበትን የቅንጦት ህይወት በቀላሉ ትቶ መሄድ በጣም ከባድ ስለሚሆንባቸው በተቻላቸው መጠን ተከላክሎ ካልተቻለም አጥፍቶ አብሮ ለመጥፋት ይወስናሉ። ይህ ማለት አገሪቷን ወደ ትልቅ የርስ ብርስ ጦርነት ይመሯታል፣ ነፍሳት ይጠፋሉ፣ ንብረት ይወድማል ማለት ነው። ከንደዚህ ዓይነቱ የርስ በርስ ግጭት በኋላ የሚገኘው “ድል” ደግሞ ፈረንጆች እንደሚሉት pyrrhic victory (አሰቃቂ ድል) እንጂ እውነተኛና የሚያጓጓ ዓይነት ድል አይሆንም። አንድ ቀን ከዛሬዋ የሶሪያ ተፋላሚ ወገኖች መካከል አንደኛው ወገን አሸንፎ የሚቀዳጀው ድል ዓይነት ማለት ነው።

ሁለተኛው፣ የምንመኘውና ሊከሰትም የሚችል የአገሪቷንም ሆነ የወያኔን ህልውና የማይነካው የሰላም መንገድ ነው። ይህም፣ ወያኔ በራሱ ፍላጎትም ሆነ ከውስጥና ከውጪ በሚደረግበት ጫና ምክንያት ሥልጣንን ለማካፈል ወይም ሊያስረክብ ሲስማማ ነው። ይህ ነው እንግዲህ የሁሉም አገር ወዳድና ሰላም ፈላጊ ዜጋ ምኞት መሆን ያለበት። በመጀመርያ ረድፍ ያስቀመጥኩትን ዘግናኝ ትንቢት ወደ ጎን ትተን በዚህ በሁለተኛው ላይ ብናተኩርና ወያኔም እንደምንመኘው ሥልጣንን ለማጋራት ወይም ለማስረከብ ከወሰነ፣ ዛሬ ባገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሱት ኃይላት ከወያኔ ሥልጣን ለመረክብም ሆነ ለመጋራት ዝግጁ ናቸው ወይ የሚለው ጥያቄ ተገቢ መልስ ያገኘ አይመስለኝም።

ከወያኔ ጋር ስለመደራደር።

የዚህ ጽሁፌ ጭብጥ፣ አገራችን ወደ አላስፈላጊ የርስ በርስ ግጭት እያመራች መሆኑን የሚጠቁሙ ቅድመ ሁኔታዎች እየታዩኝ  ስለሆነ ያንን አደጋ ለማስወገድና፣ ሰላምና መረጋጋትን አምጥቶ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን የመገንባት ኃላፊነት ሊሰጠው የሚችል የሽግግር መንግሥትን ማቋቋም ብቸኛ መፍትሄ ነው የሚለው ነው። ይህንን የሽግግር መንግሥት ደግሞ ለማቋቋም በመጀመርያ ደረጃ  ተቃዋሚ ሃይሎችና ወያኔ በድርድር ጠረጴዛ ዙርያ ለመቀመጥ ፈቃደኛ መሆን አለባቸው ባይ ነኝ። ከዚሁ በመነሳት ነው ከላይ ያነሳኋቸውን ሶስት ዓብይ ጥያቄዎች ዘርዘር አድርጌ ከዚህ በታች የማቀርበው።

 

) ከወያኔ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነን ወይ? ድርድሩስ አስፈላጊ ነው ወይ?

ወያኔ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የፈፀመው ግፍና በደል ይህ ነው አይባልም። የግፉም አለንጋ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያልገረፈው ዜጋ የለም ብል ማጋነን አይሆንብኝም። የቤተሰቡ የጎረቤቱ ወይም የዘመዱ አባል የሆነ ዜጋ በወያኔ ገዳዮች ያልተነካበት ሰው አለመኖሩን ሁሉም ያምንበታል። ያላግባብ በታሰሩት ዜጎች ላይ የሚፈፀመውን አሰቃቂ የመብት ገፈፋ በዓለም ደረጃ የታወቀና የተኮነነ በመሆኑ እዚህ ላይ ማስታወሱ ራሱ ዘግናኝ ነው። የእነዚህን ሁሉ አሰቃቂ ግፍ ሰለባ የሆነውን የኢትዮጵያን ህዝብ፣ ሁሉም ነገር እንዳልነበር ይቆጠርና “ለተሻለው ነገ” (better future) ሲባል ከግፈኛው ወያኔ ጋር ተደራደር ማለቱ ራሱ በተበዳዩ ህብረተሰብ ቁስል ላይ ጨው የመጨመር ያህል የሚያንገበግብ ይመስለኛል። የተደፈረችን ሴት መልሰሽ የደፈረሽን ሰውዬ ራሱን አግቢው የማለት ያህል ቅንነት የጎደለው ፍርድ ይመስላል።

 

ግን ደግሞ፣ ከዚህ ከበዳዩ  መንግሥት ጋር በእኩልነት ለመደራደር ከመቅረብ የተሻለ ምርጫ ምንድነው ነው? በኔ ግምት፣ ሁለት እኩል ጎጂ ወይም መራራ የሆኑ አማራጮች አሉን ባይ ነኝ። አንደኛው፣ አንደራደርም ብሎ ልክ ወያኔ እንዳደረገው በጠብመንጃ ኃይል ሥልጣን ለመውሰድ ከወያኔ ጋር ጦርነት መጀመር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ወያኔ እስካሁን ላደረሰው በደል ይቅርታም ባይደረግለት፣ የርስ በርስ ጦርነት ሊያስከትል የሚችለውን ዕልቂት በመረዳትና ላገርና ለወገን ደህንነት ሲባል ከራሱ ከወያኔ ጋር መደራደር ነው። ፈረንጆች እንደሚሉት በዓለትና በደረቅ መሬት ላይ ከመውደቅ የቱ እንደሚሻል ማማረጥ ማለት ነው። ሁለቱም ላይ መውደቅ በጣም ጎጂ ነው፣ ግን መውደቁ የግድ እስከሆነ ድረስ ደግሞ ከሁለቱ ጎጂዎች መካከል “የተሻለውን ጎጂ” መምረጥ ማለት ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአደዋ ድል በተሃድሶና በኢንላይተንሜንት መነፅር ሲታይ ! -  ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

በግሌ ከሁለቱ ጎጂ አማራጮች መካከል፣ ከወያኔ ጋር መደራደሩ የተሻለ ጎጂ አማራጭ ነው እላለሁ። በጠብመንጃ ትግል ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ መሞከር አስከፊ የሆነ የርስ በርስ ጦርነት ከማስከተሉም በላይ በጠብመንጃ ብርታት ሥልጣን የሚወስደው መንግስትም ደግሞ ዲሞክራሲያዊና ሁሉን ዓቀፍ ለመሆኑ ማስተማመኛ የለም። በኔ ግምት ወያኔ እንደ ማንኛውም የኢትዮጵያ የፖሊቲካ ድርጅት ከፈለገ እንደ አንድ የትግራይ ብሄር ድርጅት አለያም እንደ አንድ የአገር አቀፍ ድርጅት የድርድሩ አካል የመሆን መብት አለው። ወያኔ ወደድንም ጠላንም የችግሩ መንስኤ የሆነውን ያህል ለችግሩም መፍትሄ የመሆን ግደታ አለበት። በሥራዬ ጠባይ ምክንያት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ካየኋቸውና ከተካፈልኩባቸው ባንዳንድ አህጉራት ይከሰቱ የነበሩትን የርስ በርስ ግጭቶች መነሻና መድረሻ ገምግሜ፣ የዛሬው የኢትዮጵያ ፖሊቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ሊፈታ የሚችለው በድርድር ብቻ መሆኑን ሙሉ በሙሉ አምንበታለሁ። ሌላው ምርጫ የጥፋትና የዕልቂት ነው። እንደው ያለጥፋትና ያለ እልቂት ወያኔ ያኔ እንዳደረገው በጠብመንጃ ኃይል ሥልጣን መውሰድ ይቻላል ቢባል እንኳ፣ (ያን ያህል የታጠቀና የተደራጀ ኃይል አለ ብለን እንኳ ብንወስድ) በጠብመንጃ ኃይል ሥልጣን ላይ የሚወጣ ኃይል ከላይ እንዳልኩት፣ ዲሞክራሲያዊ ሆኖ ያገሪቷን ችግር ፈትቶ ሰላም ሊያሰፍን አይችልም ባይ ነኝ።

) ከተቃዋሚውስ ወገን ለመደራደር የሚቀርበውስ ማን ነው?

 

ይሄኛው፣ ከላይኛው ያላነሰ አወዛጋቢ ይመስለኛል፣ ቁጥራቸው ከሃምሳ በላይ የሆኑት አገር ዓቀፍ ተቃዋሚ ኃይሎችና ብሄራዊ ነፃ አውጪ ድርጅቶች ለድርድር የሚቀርብላቸውን የሰላም ጥሪ ተቀበሉ እንበልና፣ እስቲ ማነው ከነሱ መሃል የኢትዮጵያን ህዝብ ወክሎ ከወያኔ ጋር ለድርድር የሚቀርበው? በኔ ግምት ተቃዋሚ ኃይሎች በአደረጃጀትም ሆነ በዓላማ የሰማይና የምድር ያህል ተራርቀዋል ባይ ስለሆንኩ፣ የነሱ ተወካይ ሆኖ በድርድር ጠረጴዛ ዙርያ የሚቀመጠው ማን ሊሆን ይችላል የሚለው የሁላችንም ራስ ምታት ይመስለኛል? እነዚህን በቅርጽም ሆነ በይዘት የማይጣጣሙትን ድርጅቶች እንዴት ተደርጎ ነው አንድ ላይ አምጥቶ የሁላቸውንም ጥቅም የሚያስጠብቅና በቅንነት የሚደራደር ቡድን መምረጥ የሚቻለው? ይህ ፈረንጆች የሚሉት የሚሊዮን ዶላር ጥያቄ ነው።

) የመደራደርያ ነጥቦቹስ ምን ይመስላሉ?

ከላይ ከተጠቀሱት ሁለት አብይ ችግሮች ትንሽ ረገብ ያለው ሶስተኛ ችግር ደግሞ፣ የመደራደርያው ነጥብ (ነጥቦች) ጉዳይ ነው። በመሰረቱ ተደራዳሪ ወገኖቹ ከተሰየሙ በኋላ ድርድሩ መጀመር ያለበት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ቢሆንም ሁለቱም ወገኖች ለድርድሩ ያላቸውን ቀናነት ለማሳየት አንዳንድ እርምጃዎችን አስቀድመው መውሰድ ያለባቸው ይመስለኛል። ለምሳሌ ያንዳንድ ፖሊቲካ ድርጅቶች መሪዎችና ደጋፊዎች እስር ቤት ስላሉ የነሱን መፈታት እንደ ቅድመ ሁኔታ ማሰቀመጥና በወያኔ በኩል ደግሞ የትጥቅ ትግል በማካሄድ ያሉት ድርጅቶች ለጊዜውም ቢሆን ማጥቃቱን እንዲያቆሙ መጠየቅ አግባብ አለው ባይ ነኝ። ዋናው የመደራደርያ ነጥብ ግን ወያኔ የሥልጣን መንበሩን ለጊዜያዊ መንግሥት ማስረከብ ሲሆን የጊዜያዊ መንግሥቱን ይዘት፣ አሰራርና የሥራ እንቅስቃሴን በተመለከተ ደግሞ ተደራዳሪዎቹ ራሳቸው በድርድሩ ጠረጴዛ ዙርያ የሚወስኑት ይሆናል።

መደምደሚያ

ከጠላት ጋር፣ በተለይም እንደ ወያኔ ዓይነት ለዓመታት ህዝባችንን ሲያስር፣ ሲገድልና ሲያሰቃይ ከነበረ መንግሥት ጋር ለድርድር መቅረብ ማለት ለሰው ልጅ ህሊና በጣም የሚከብድ ነገር ነው። እንኳን ከገደለና ካሰቃየ ባዕድ አካል ጋር ይቅርና በትንሽ ነገር እንኳ ካስቀየመ የቅርብ ወዳጅ ጋር መታረቅ በጣም ከባድ ነገር ነው። ግን ደግሞ ሰው የሚደራደረው ከጠላቱና ከተቃዋሚው ጋር እንጂ ከወዳጁ ጋር ስላልሆነ ከወያኔ ጋር መደራደር ብቸኛ አማራጭ ነው እላለሁ። ያገር ጉዳይ ደግሞ በመቀያየምና በመኮራረፍ ወይም አንዱ አንደኛውን በማጥፋት የሚፈታ አይደለም። ኢትዮጵያ ለሁላችንም እኩል እናት ናት፣ ማንም ከማንም በላይ ልጇ ሊሆን አይችልም፣ የሚያስብም ካለ ተሳስቷል። ይህ እስከሆነ ድረስ ደግሞ፣ ወያኔም እንደ አንድ የፖሊቲካ አካል ከሌሎች ተቃዋሚ አካላት ጋር በእኩልነት ቀርቦ ለመደራደርና የወደፊቷ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መሰረት ለመገንባት ተካፋይ መሆን አለበት ባይ ነኝ። ይህም የሚሆነው ደግሞ በድርድሩ ሂደት እንደሚወሰነው፣ ወያኔ አሁን ካለበት የሥልጣን መድረክ ወርዶ ከሌሎች ተቃዋሚ ኃይላት ጋር በፍፁም እኩልነትና ተዋረድ በሌለው የድርድር ጠረጴዛ  ዙርያ ተደራዳሪዎቹ በሚስማሙበት ውሳኔ መሰረት ይሆናል ባይ ነኝ።

በበኩሌ ለማለት የፈለግሁትን በግልጽ ያስቀመጥኩ ይመስለኛል። የውይይት ነጥቦችን ለማንሳት ሞከርኩ እንጂ ከድርድሩ አስፈላጊነት ሌላ፣ ተቃዋሚ ሃይሎች እንዴት አርገው ተወካዮቻቸውን እንደሚመርጡ ወይም የድርድሩ ይዘት ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ስሌት (formula) የለኝም። እያንዳንዳችን ያገሪቷ ሁኔታ ያሳስበናል የምንል ወገኖች ደግሞ፣ በየግላችን የምናምንበትን የአስተሳሰብና የአቋም ዘውድ በየኪሳችን ይዘን ከመዞር፣ በግልፅ በአደባባይ አምጥተን ብንወያይ ይበጃል ባይ ነኝ። በኔ ግምት፣ ለማንኛውም ዓይነት ችግር ዘላቂ መፍትሄ ሊገኝ የሚገኘው በድርሻ አካላት (stake holders) መካከል በሚካሄደው ቅንነት የተሞላበት ውይይት ብቻ ነው። ያንን እስካላደረግን ድረስ ደግሞ ያገሪቷ ሁኔታ አሁን ካለበት መጥፎ ደረጃ ወደ አስከፊነት ከተሸጋገረ፣ ባልጠበቅነው ሰዓትና አኳኋን “ዳግማዊ 1991” ይከሰትና፣ የሄርማን ኮሄን ልጅ የአሜሪካንን መንግሥት ጥቅም ሊያስጠብቁ ይችላሉ ብሎ የሚተማመንባቸውን ግለሰቦች ከተቃዋሚ ድርጅቶች መሃል መልምሎ፣ ለንደን ላይ ይሰበስብና “ዳግማዊ የሽግግር መንግሥት” ያቋቋምልናል። ምርጫው እንግዲህ የኛው ነው፣ ውሳኔውም በእጃችን ነው። እስቲ የእናንተን ደግሞ ልስማ!

በቸር ይግጠመን።

******

 

ባይሳ  ዋቅወያ

ጄኔቫ፣ መስከረም 11, 2017

wakwoy2016@gmail.com

[1] ጸሃፊው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሥልጣን የነበሩ የዓለም ዓቀፍ ሕግ ባለሙያ ናቸው።

 

 

11 Comments

  1. This is really well thought and expected from responsible citizen. Well done please maintain this our politicians need advise on alternatives. I know EPRDF can not be trusted but there is no option. Let us try to get win-win deal. Call for all,Can we help our country at this difficult time.

    Thank you again

  2. ኢያድግ አሁን ላይ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚያስቢል ደረጃ የቤሄርተኝነት ፈንጅ አስብጨጦናል:: አሁን ያለው ስራአት ምንም ነገር ሳያስተካክል ስልጣኑን ቢለቅ በእጃችን ያለው ፈንጅ ፈንድቶ ሁላችንም እናልቃለን:: ስለዚህ ከላይ በተፃፈው ፅሑፍ ይላ ቢታሰብበት…

  3. The Gangster tplf know very well what to do with his colonised land ethiopia. Trust me any body can try all options to deal with gangster tplf in solving the political problem of ethiopia peace fully but tplf will choice the path which is bringing the people of ethiopia killing each other.

  4. Those oromo elites like Obbo/ato Bayisa respected professionally at national and international level may express thier worry and conern. their worry and onern derived from their exprience , service and observation around the world. they are oromo in name but abyssinians in thought and action.knowingly or unknowingly at all turning points, they try to be like thorns in the mud.They pour cold water on the people resistance The problem is they think big ignoring the abyssinninans intrigue and mishievious nature.Edcuated or unedcuated abyssinians read each other,they can easily understand on common issues.They dont care about timely warning and advice from some one trained to serve in the name of Abyyssinian colonial system in the name of Ethiopia.an armed militia has voice than the fake president of the state,lookthe palace deorator Teshome Mulatu.if Ato Bayisa has Ethiopia of Amhara(Kings),Tigray(weyane) that fabricates puppets and running dogs in his mind better for him to enjoy his pension in European metro- politan.

  5. I have to appreciate the initiative of Mr. ባይሳ ዋቅ–ወያ. It is always good to express own view that would help for freedom, unity, prosperity and peace. It goes well with the saying “if you keep coins, dollars would keep themselves”.
    Whereas, apart for scenarios Bay’isaa said he has no opinion, I found the suggestion isn’t comprehensive of other might be significant scenario when change of regime is desired, for two very reasons.
    1. The scenario if one of the current anti-TPLF armed forces win TPLF led government

    In fact Bay’isaa may argue for he partly stated of such possible scenario provided armed current guerrilla would over through the present incumbent regime. But Bay’isaa’s brief touch anticipates circumstances that the would be winner allows present Ethiopian Empire to exist in shape. The question is what if winners will be those who are fighting TPLF led regime to enable referendum of the people they are fighting for? Do you think that such forces are required to sit for negotiation in the context of your article?

    2. If TPLF is convinced to use Article 39 to establish Republic of Tigray and also allows that right for others who need to exercise their right to get to such goal. In terms of this feature, my query is if you think TPLF is better off by negotiation for secession or without need blessing of the anti-TPLF forces?

  6. That is the issue man. What has been preached for 25 years is haterage, in the name of Identity difference, completely negatives and all the wrong deeds of one group on another. I don’t think that is the only face of our past. If at all that is true everything is done by few leaders, it by no means represent poor citizens. But when things go wrong like during times of instability it the poor will be victim. Imagine failure of EPRDF due you think the leaders will suffer?

    Mr. Bariisso with due respect for your thoughts I think it is wise to make peaceful separation if need be to the minimum you will have good neighbor. But let us exhaust alternative we need to discuss more and above all Listen, listen, listen to each other.

  7. @ nabil,you are dirty minded Abyssinian dog that call yourself Ethiopian even you have no basic elements of diffrentiating hyena and Bariisoo, irritated,go hell with your forum.
    @Tarik, you wrote that” freedom,unity,prosperity and peace…”, the probelm is freedom for whom? unity for what? prosperity for whom? peace for what? dictators fascists,democrats,colonisers , colonised,scessionist all are qouted, qouting these terms but in the name of these they killed people,destructed material resources,looted and exploited immense wealth of the nation,humilated the people promoting hunger and poverty. Amhara dominated social system passed Tigray- weyane dominated socialsystem came to existence.Both have displayed their ambition to dominate and humilate others under their foot in th name of unity.be cause of the military junta that cursed country lost the golden opportunity to become united and prosperous.because of TPLF mafia gangs in the palace another golden opportunity is in the process to
    be lost. good governance by black or white or yellow has the same end.good life for the people.If our people suffer miserably from time time in name of unity it is better to stop and ponder once again until when it will continue in humilation.morethan ever our people politised and know what is good governance
    and bad governce.Any classical Abyssinians ambition to solve the current situation needs critical thinking and caution.The two Abyssinian nations armed groups with sophisticated modern military capability and organizational strength,The people resistance,weak and fragmented violence or non violence focused political organizations representing partially or fully their people,the partisan ship of the world powers in the region will influence what will be the end result of the current turmoil.Weyane(Tplf) dominated EPRDf no more a real politial machinery to decieve the people,Fake EPRDF must be replaced by true representative of the people. weyane has lost its card to play to stay in power. now disbanding expired pdos (pows) or give more autonomous status for regional state governments, release all politial prisoners .expand more political environment for Oromos, Amharas and other people political activists to breath.Weyane can act as a catalyst rather than a motor in avoiding the catastrophe a head of us.As there is sweet in what we hate and hate in what we like acting proactively from all sides can seure the the peace of the people.IF weyane continue acting as beast entering sleeping room ,the people has no choice except dying and killing the beast entering the sleeping room,at the end of the day the mass is the winner.boss-dog style Abyssinian policy is expired.

  8. Mr Dawit,because of arrogance ,ignorance ,political egoism and empty pride there is lack of listening to each other.Abyssianain elites and their followers has no respects for each other and their counter parts.they are culturally accostumed to eliminating brutally whom they found threathing their authority. There is no genuine communication but only to deceive to reach ones goal.From history and my own observation ,oromo elites are always betrayed and use-throw style in that cursed country. we have wounds.no one dare to heal that wound.as unity proved to be exasperating the wound we have no guarnty separation is the healer but it is a sealed package in store for emergency now.TPLF stored its agenda of separation in Tigray Caves and terrorising others as ruler of Ethiopia.more than any other time TPLF is prepared Tigray to be indepedent state,if separation is the option still they have the upper hand.Rahter than terrorising each other and fake brother hood for years passed and to come,it is better to decide own fate.then help each other as good neighbours in the horn.who knows one day EAUS( east african united states) will be our passport.

  9. Mr. Bariisoo I understand some legitimate points you highlight. We are really unfortunate people to see that mistakes are being tried to be solved by another mistake. We have to appreciate how some of our gaps are properly exploited by the Gangsters. At any cost we are looser above all the majority are loosers.

    My honest feeling is that above the issues the way we handle them is hurting us more.That is a planned game played against us trust me the Gangsters excel to us. I agree we miss the opportunity of listening and cooperation where we both can benefit from that. But don’t forget that there is deliberate effort towards that. I wish if there is appropriate platform for better discussion.

    All the best!

  10. Mr.Dawit,thank you for your civilized dialogue in writing. The state that was establihed through cruelty maintained through cruelty and trickery and mafiose-boss style.I think what ever a planned game designed to play it is back fired. It seems the minority vs Majority lining alliance is in the process.If the majority soldifeid themselves to work toward common strategic alliance and handle their diffrences wisely,in a very short time we can see the change. To have all the options in their hands mobilising their human resources and material resources of are of paramont importance .The tendency to demonise the others and hegmonise onself widens the gap.TPLF is not acting as responsble ruling party but as bullying gangster that is why TPLF state is in coma.so they are not smart and excelled to confront the mass. they are the losers.they accumilated wealth of the nation egoistically and lose it miserably. The tendency to engage somale people and oromo people in border conflict ,Amhara and Tigray territorial disputes are the main sign of imbecile and irresponsbile action of TPLF Old guards.

Comments are closed.

Share