ኦሮሚኛ ተናጋሪ የኦነግ ጠባብ ብሔረተኞችና በአክቲቪስት ስም የተደራጁ አክራሪዎች!  (በመርዕድ ከተማ) 

ለስልጣን የቋመጡ ሃገር በቀል ኦሮሚኛ ተናጋሪ የኦነግ አክራሪ ጠባብ ብሔረተኞች በኪስ በሌለው የሬሣ ሣጥናቸው ያጨቋቸውን መናጆና መንጋ ጀሌዎችን በፈጠራ ታሪክ በመተብተብ ያለ ልጓም ይጋልቧቸዋል:: ምኞትና ፍላጎት እየተጋጩ እረፍት ይነሷቸዋል:: እውነታን፣ምክንያታዊነትን፣ማስረጃንና መረጃን ሣይሆን ስሜትንና ህልምን እያስጨበጡ ይነዱዋቸዋል:: ያለ ንፋስ የሚበተን አቧራ ያለ ሙቀት በበረዶ የሚቀልጥ ደመና መኖሩን እየሰበኩና በቀን ቅዥት ተሸፍነው እኛ ለናንተ <<ህልም>> አለን ይሏቸዋል:: የያዙትን ኢትዮጵያዊ ማንነት አስጥለው የማያውቁትን ዓለም እንዲቋምጡ በማድረግና በማስጨበጥ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ቅኝት የ19ኛውን ክፍለ ዘመን የፈጠራ ትርክታቸውን ይግቷቸዋል:: ዛሬ ላይ በወያኔ የተጫነባቸውን ጭቆናና የአፓርታይድ ሥራዓት ሣይሆን ጥንት በግል ደረሠብን የሚሉትን <<ጉዳትና ቁስል>> እያወሡ ከዛሬ ጋር ሣይሆን ከትላንት፣ከእውነታ ጋር ሣይሆን እነርሱ እራሣቸው ከማይፈቱት ህልምና ቅዠት ጋር ግብ ግብ እንዲይዙ በዘገምተኛ ህሊናቸው ይሠብኩዋቸዋል:: በ21ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ሆነው ከ19ኛውን ክፍለ ዘመን ጋር ያዋጓቸዋል::እነርሱ በሠማንያ የተጋቡትን የህልም እንጀራና የህልም ዕይታን (wishful thinking & wishful seeing) ምስኪን ደቀመዝሙሮቻቸውን ይጋብዟቸዋል:: የቀቢፀ – ተስፋ ናና ከረሜላ እያስላሡ መርዛማ አረንቻታ ይግቷቸዋል:: በ21ኛው ክፍለ ዘመን ቅኝት የ19ኛውን ዘመን በምናባቸው ያስዳስሷቸዋል:: ከነባራዊው ዓለም እውነታ ጋር ያፋቷቸዋል:: አንድ ዓይነት ቋንቋ የሚናገር፣ አንድ ዓይነት ሃይማኖት ወይም ስነልቦና ያለው

የኦሮሞ ማህበረ-ሕዝብ ብቻውን ከኖረ ከጭቆና ተላቆ ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ይሆናል እያሉ በቅዥት ባህር ይቀዝፏቸዋል:: ዛሬ ላይ ሆነው ነገን እንዳያልሙና ለነገ እንዳያቅዱ ችካልና ግርዶሽ ይሆኑባቸዋል:: እነኚሁ ጭፍን ጠባብና አክራሪ ብሔረተኞች ጥሬ ያልሠጧትን ዶሮ እንቁላል ማስፈልፈል፤ ሣር ያልቀለቧትን በቅሎ ማስገር እንደሚችሉ በመለፈፍ ጀሌዎቻቸውን ኮርቻ ጭነው በቅጥፈት ይገሯቸዋል:: ገና ከፅንሳቸው ኢ-ዲሞክራሲያዊ የሆኑ ለግል ዝናና ጥቅም የሚራወጡ በገደብ ዐልባ ስሜታዊነትና የግል ዝና የመቃተት ህመም (Histrionic Personality Disorder – HPD) የሚሠቃዩ ቋንጣ እንዳየችው ያቺ ድመት ቀቢፀ ተስፋን ብቻ አንግበውና የአብሮነቱን ጣራ ደርምሠው ዜጎችን ከጋራ ጎጆ ለመበተን የሚቃትቱ ገመምተኞች የህዝብን መፃዒ ዕድል በራሳቸው ወስነው የዋህ እርግቦችን ከሠፈሩበት ዛፍ አውርደው የሠለለ ቅርንጫፍ ላይ ለማሣረፍ እንደሚደክሙና እንደሚታገሉ ያመላክቷቸዋል:: የተጠናወታቸውን የግል የበታችነት ስሜት ከህዝቦች ፍላጎት ጋር እያጋቡና እያጋጩ የነርሱን ከንቱ ህልም ታቅፈውና ተደግፈው ኢትዮጵያዊነትን እንዲንዱ ኢትዮጵያ ሃገራቸውን እንዲያፈርሱ ይገፏቸዋል:: ሽረባና መርዝ ቀምመው ቂም፣በቀልና ደም ያቃቧቸዋል (በዊሊያም ሼክስፒር ድርሠት ውስጥ ኦቴሎ ሚስቱን ዴዝዲሞናን የገደለውና በኋላም ተፀፅቶ እራሱን የገደለው በላጎ የቅጥፈት ወሬ ተታሎ እንደነበር እናስታውስ!።) ይህን መሣዩን ከንቱ ቅዥት ቃዥተውና ምስኪን አሸብሻቢዎቻቸውን አሸክመውና ነድተው በተመሣሣይ ቀመር ከዚህ ቀደም ለስልጣን የበቁ እንደ ወያኔና ሻዕቢያ ያሉ <<የነፃ አውጪ ግንባር>> ተብዬዎች የሠበኩትን ፍትህና ዲሞክራሲ ነፍገው ለስልጣን ጥማቸው መወጣጫ የተጠቀሙትን የምልዐተ-ህዝቡን ትከሻ ተመልሠው በባሠና በከፋ መልኩ ሲወቅሩና ሲረግጡ አሁን ማየት ብዙ አላስቸገረም ወይም ነቢይ መሆንን አልጠየቀም:: ይህ ጭፍን ጠባብና አክራሪ የኦሮሞ ብሔረተኞች ቅዥት እውንና ገቢር መሆን ቢችል ኖሮ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎው ለአንድ ዓይነት ቋንቋ፣ሃይማኖትና ስነልቦና ለመፍጠር የሚደረግ ትግል በሆነ ወይንም አንድ ዓይነት ቋንቋ የሚናገር ፣አንድ ዓይነት ሃይማኖት ወይም ስነልቦና ያለው ማህበረ -ሕዝብ ከውልደቱ ቀን አንስቶ ዲሞክራሲያዊ በሆነ ነበር:: ለዚህም ነው <ቄሣር ክሊዮፓትራን ባይወድ የዓለም መልክ አንድ ይሆን ነበር> በሚል ዓይነት ምልከታና እራስን ብቻ በሚያገለግል ብዥታ(self-serving bias) የሚደፍቋቸው!

ተጨማሪ ያንብቡ:  “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሐዊና ሕጋዊ ነው”

በጅምላ ፍረጃ (Hasty Generalization)የተካኑት እነዚህ በህልም የሠከሩ ጠባቦች ትላንት ከሚገድሉት ጋር ሲገድሉ፣ከሚቀድሱትና ከሚዘይሩትጋር አብረው ሲጨፈጭፍ፣ሲይስጨፈጭፉና ሲያሸበሽቡ የነበሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ አክራሪ አክቲቪስት ተብዬዎች ዛሬም ተከታዮቻቸውን እየማገዱና በነሱና በነፃነታቸው ስም እየቸረቸሩ ያሉ ፖለቲካዊ በታኝ ሃይሎች (Political centrifugal forces)ናቸው:: ውጤቱ ወይም ጦሱና መዘዙ (unintended consequences) ባይገባቸውም በተግባርም ሊያሣኩ የሚፍጨረጨሩት ሂሣቡ የተወራረደውን፣በተደጋጋሚ በሽንፈት የተገባደደውን ኢትዯጵያን የማፍረስ የቅኝ ገዢዎችን ምኞት ገቢር እንዲሆን ነው:: ጠባብ ብሔረተኞቹ የወያኔ ገዢዎች ድሮም ሆነ አሁን <<በነፃነት ግንባር>> ስም ያንቀሣቀሱዋቸውንና የሚያንቀሣቅሱዋቸውን ባንዳዎችና ሹምባሾች የተጓዙበትን መንገድ እንዳለ በመቅዳትና በማቀንቀን (copycat) ሊተገብሩም የሚቃጣቸው ጥንታዊውንና ዘመናዊውን ቅዠት ነው:: ሊንዱትና ሊዋጉትም የሚዳዳቸው ረቂቅና ሚስጥራዊ ሐሳብ ወይም የእምነት ቃል የሆነውን ኢትዮጵያዊነትና የመሠረተ-ሃሣቡ ማህተም የሆነችውን የቁርጥ ቀን ልጆቿ በደም በአጥንታቸው እነርሱ ሞተው የታደጓትንና ያኖሯትን ኢትዮጵያን ነው:: ለዚህም እኩይ ተግባራቸው ያሠለፉት በአክቲቪስት ስም በበጎች የተደራጀና በጎች የሚመሩት የጥፋት ብርጌድ ነው::ታዲያ ምን ያደርጋል ታላቁ አሌክሣንደር አንድ ወቅት <በጎች ከሚመሩት የአንበሣ ሠራዊት ይልቅ አንበሣ የሚመራው የበጎች ሠራዊት ይሻላል> ብሏቸው ነበር::

ሌላው እኔን የሚገርመኝና የሚያስታውሰኝም <የእንሠሦች ዓመፅ (Animal Farm)> በተሠኘው ልበ ወለድ መፅሐፉ ጆርጅ ኦርዌል የዜጎችን ፍፁም እኩልነት እናሠፍናለን ብለው ስልጣን፣ልዩ መብትና ጥቅም ለጥቂት ምርጦች ጀባ የሚሉ ግብዝ መንግስታትን የተቸበት ምፀት ውስጥ በእንሠሦቹ የመጀመሪያ የአመፅ እንቅስቃሴ ምዕራፍ እንሠሦቹ ሁሉ ተግባብተውበት የነበረው “ሠባቱ ትዕዛዛት (Seven Commandment)” በተሠኝውና በአሣሞቹ የተነደፈው መተዳደሪያ ሠነድ ላይ የተደነገገው(ልክ እነደ ወያኔ «ሕገ-መንግስት) <ሁሉም እንሠሦች እኩል ናቸው (All animals are equal)> የሚለው መመሪያ ያለ እንሠሦቹ እውቅና ወይም ይሁንታ(awareness & approval) ጮሌዎቹ አሣሞቹ(ልክ እንደ ወያኔ) ሥልጣን መንበር ላይ ከቆናጠጡ በሗላ የበላይነታቸውን በሚያሠፍንና በሚያረጋግጥ መልኩ ተሻሽሎና ተለውጦ <ሁሉም እንሠሦች እኩል ናቸው::አንዳንዶቹ ግን ከሌሎቹ የበለጠ እኩልነት አላቸው (All animals are equal,But some animals are more equal than others)> በሚል አዲስ መመሪያ/motto/ ተተክቶ የአሣማዎቹ መንግስትና አሣማዎቹ ቁንጮ ሆነው በመውጣት በትረ-ሥልጣኑን በመቆጣጠር ያገዱዋቸውንና የነዱዋቸውን እንሠሦች ነው::በዚሁ መፅሃፍ <ናፖሊዮን> የተሠኝው አሣማ <አንዱ እንሠሣ ሌላውን ፈፅሞ መግደል አይችልም> ሲልና ሲደነፋ ቆይቶ ‹ለዓመፅ ተነሳስታችሁ ነበር› በሚል ሠበብ በውሾቹ ያስገነጣጠላቸውን የዋህ እንሠሦችን ነው:: <የሠው ልጅ ሁሉ ጠላታችን ነው> በሚል ሸውራራ ዕይታ ከአላማጆቻቸው ጋር የነበራቸውን መስተጋብር አፍርሰው የበተኗቸውን እንሠሦች ነው::የዚህ መፅሓፍ ይዘትና ምፀት ወያኔ በቋንቋ ፌደራሊዝምና በጎሣ ስም አደራጅቶ የነዳቸውን እንደ ኦነግ ያሉትን ሃይሎች ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  " ጠዋት ወጥቶ ፣ማታ መጥለቅ " (በመኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ)

አሁን የማየው ትይንትም ከዚህ ያልሸሸና ያው ጠባብ ብሔረተኞቹም ሆኑ ገዢዎቹ የወያኔ አሣሞች፤ተናካሾቹም የኦሮሞ አክራሪ ጠባቦች ያው የናፖሊዮን ውሾች መሆናቸውን ብቻ ነው::የኦሮሞ አክራሪዎችም ሆኑ ወያኔዎች ጠባብ ብሔረተኞች ናችው።ሁለቱም ግንኙነታቸው የአዞና የወፍ ነው።ሁለቱም የኢትዮጵያ ጠላቶች ናቸው።ሁለቱም የሚዋጉት ኢትዮጵያዊነትን ነው።መፍትሄውም ለጋራ ጠላቶቻችን የጋራ ግንባር መፍጠር ብቻ ነው።መፍትሄውም ሁለቱንም በጋራ መታገል ነው።

ብደምረው፣ብቀንሰው፣ባባዛውና ባካፍለው ዜሮ እየሆነ ያስቸገረኝ ስሌትም ይህ ብቻ ነው!!
=====
” ማንኛውም የተሽከርካሪ ጎማ ወይም መሪ ምንም ያህል ወደ አንድ ወይም ሌላ አቅጣጫ ቢገፋ:ቢዞርና ቢንጋለል ሚዛኑን ጠብቆ በመሽከርከር በፊት ወደነበረበት እንደሚመለሠው ሁሉ: ከቶውን ሊቀለበስ የማይችል መስሎ የሚታይ ግዙፍ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከተከናወነ በሁዋላ ሁሉም ነገር እንደገና ወደ ድሮ ቦታው ዞሮ ማፈግፈጉ ወይም ወደ መጀመሪያ ቅርፁ ተመልሶ በነበረበት መዳከሩ ላፍታም አያጠራጥርም”
1984
(ጆርጅ ኦርዌል)

“… Even after enormous upheavals & seemingly irrevocable changes,the same pattern has always reasserted itself,just as gyroscope will always return to equilibrium,however far it is pushed one way or the other ”
1984
(George Orwell)
~~~~XXX~~~~

16 Comments

  1. የግል ኣስተያየት መስጠት የዲሞክራሲ መብት ቢሆንም እንደ ዓሣ የጠነባ አስተያየት መስጠት ግን እራሽን ያዋሪዳል። ባንተ ቤት የኦሮሞን ህዝብ ትግል ማቅለልህ ነው። ደደብነት ይሉሃል እንድያ ነው።

  2. አቤት የስድብ መዐት፥ አቤት የውሸት መዐት። በስድብና በውሸት የሚቀየር ነገር የለም። እርስዎም ለአመኑበት ነገር አክቲቭስት ሁነው ተከታይ ያፍሩ እንጂ ስድብና ሃተታ ከውሸት ጋር መርጨቱ ኢትዮጵያን አያድነም።

  3. I am sorry to say it, I did not learn anything positive from this article. The entire message was just curse. People have the right to have different opinions (right or wrong). I believe, the aforementioned activists and their followers/supporters are not stupid as the article tried to portray them. I don’t think this will help Ethiopia, or the unity this writer is preaching. I am an oromo Ethiopian, and I believe that the oromo people have unanswered legitimate questions. How to demand answers? We all can have different approaches. Please, if we are really concerned about genuine unity, let us not dismiss people’s concerns (even if it is raised by a single person, or a group). Let us focus on the real issues and try to find good solutions.

  4. Nararoo, How on earth he could be a democratic one’s who believes in racial political agenda? don’t be offended when some one express his opinion.
    instead, you have to discourage the individual who are preaching hate,racism,
    against Unity like the TPLF’s do.

  5. This article was written by one Neftegna Psychiatrist who lives in Belgium or The Netherlands. his name is Dr. Assefa Negash. He needs a Psychiatrist for himself.

    Yebesebese ye Harrar Neftegna newu.

  6. You are a son of the rotten nefregna and a very simple minded person. You are homeless and a settler in Oromia. You want to rely always on the Oromo nation like a parasite. We have a loving heart you can ask us and we can help you. But stop worshiping the Hitler of Africa, your Emiye Menelik. The dark time of the Menelik’s era will not come back again. The rotten and inhuman systems of the invaders of old neftengas will never reincarnate. The ghost of Minilik also will not defend the failed ambitions of his offspring.
    The main problem is your mentality and the culture in which you grew up. The mentality and the culture of the dark era of Minilik, Haile Selassie and Derg which are still influencing and confusing you. You need redemption. The Oromo Qubee generation can probably help you in the near future by teaching and heralding a true democracy in that country. But in the meantime it is better if you reconcile yourself with the reality of this time. You cannot turn back the wheel of history.

    Give up! You have already lost the war of discrimination and assimilation. Even most of the Amaharas have been suffering under the policies of the outdated Neftenga systems. They need help to becom free from the bad and outdated mentalities. Therefore, first of all: you better liberate yourself from the bad culture and mentalities of your forefathers. Don’t forget you are living in the 21st century, but not in that 19th century. Also don’t forget you have a lot of problems within yourself and in your home country. Sooner or later you will be challenged by the peoples of Agewo, Qimant, Wa’ito and so on. WATCH OUT! You will be shrunken while you are dreaming to control Oromia and it’s people.

  7. ጸጋዬ አራርሳ አዲስ ስታንዳርድ ላይ ባቀረበው ጽሁፉ ውስጥ ኦሮሞ የአዲስ አበባ ታሪካዊ ባለቤትና ምድሩ ላይ የበቀለ [indigenous] መሆኑን ለማሳየት ካቀረበው ጸሐፊ ከሻለቃ ዊሊያም ሀሪስ መጽሐፍ የተወሰዱ ናቸው። ሆኖም ግን የሀሪስ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኝው ታሪክ ጸጋዬ በኩሸት የነገረን የኦሮሞ የአዲስ አበባ ታሪካዊ ባለቤትነትን የሚያሳይ ሳይሆን ተቃራኒውን ማለትም ኦሮሞ የአዲስ አበባ ታሪካዊ ባለቤት እንዳልሆነና እንዴውም የአዲስ አበባ መጤ እንደሆነ የሚያሳይ ነው። የኔ ጽሁፍ አላማ ማንም ፊደል የቆጠረ ሁሉ የሀሪስን መጽሐፍ አንብቦ ሊያረጋግጠው የሚችለውን እውነታ [በመጽሐፉ የሰፈረውን ማለቴ ነው] ለዘረኝነት ጥማቱ ማርኪያ ሲል ጸጋዬ አራርሳ ጠምዝዞ ያቀረበውን ድፍረት የተሞላበት ውሸት ማጋለጥ ነው። ከዚህ ውጭ ጽሁፌ የጸጋዬ አይነት አላማ እንደሌለው አንባቢዎቼ እንዲያውቁልኝ እሻለሁ።
    ጸጋዬ አራርሳ ባሳተመው የአዲስ ስታንዳርድ ጽሁፉ የአዲስ አበባን ኗሪዎች ታሪክ ሲያስቀምጥ “A cursory glance at writings by William Harris, Alexander Bulatovich, and even Evelyn Waugh, indicates that the State operated in Addis Abeba as an occupying force of settler colonialists bent on pushing out and displacing the indigenous Oromo peoples” ብሏል። ይህ የጸጋዬ ትርክት እውነትነው አለውን? እስቲ የሚቀጥሉትን አንቀጾች እንመልከት። በመጀመሪያ የጸጋዬን ምንጭ ማንነት እንግለጥ።
    ጸጋዬ የጠቀሰው ሻለቃ ዊሊያም ሀሪስ በንጉስ ሳህለ ሥላሴ ዘመን ኢትዮጵያን የጎበኘና ንጉስ ሳህለ ሥላሴ ወደ ጉራጌ ምድር ሲሄዱ አብሯቸው የተጓዘ የእንግሊዝ መንግሥት ልኡካን ቡድን መሪ ነው። ዊሊያም ሀሪስ ከጉብኝቱ በኋላ አገሩ ተመልሶ ባዘጋጀው “የኢትዮጵያ ደጋ አገር” ወይንም በእንግሊዝኛው “The Highlands Of Ethiopia” መጽሐፉ ስለ ከንጉሱ ጋር ስለነበረው ጉዟቸው በስፋት ያወራል።
    ሻለቃ ሀሪስ በጉዞ ማስታወሻው እንደነገረን ሳህለ ሥላሴ ወደ ጉራጌ ሲጓዙ በፍልውሀ በኩል ተሻግረው እንደሄዱ፤ ሲመለሱ ደግሞ በእንጦጦ ዞረው ወደ አንኮበር እንደገቡ፤ በየመንገዳቸው ኦሮሞዎችን እንዳገኙና ግብር ያስገቡላቸው እንደነበር ያትታል።
    ጸጋዬ አራርሳ አዲስ አበባን ዋና ከተማ አድርጎ እንደገና የተመሰረተውን የኢትዮጵያ መንግስት “an occupying force of settler colonialists bent on pushing out and displacing the indigenous Oromo peoples” ሲል ሀሪስ ያልጻፈውን ቢጠቅስም፤ የጸጋዬ ዋና ምንጭ ዊሊያም ሀሪስ ግን “The Highlands Of Ethiopia” በሚል በጻፈው መጽሐፍ ገጽ 234 ላይ “Thus affairs continued until the sixteenth century, when the invasion of Mohammad Graan led to the total dismemberment of the Ethiopic empire ; and Shoa, among other of the richest provinces, was overrun and colonized by the Galla hordes. Libne Dengel, the emperor of Gondar, fell by the hand of the Moslem conqueror.” ሲል ጽፏል። ጸጋዬ አራርሳ ግን በአዲስ ስታንዳርድ የጻፈው ዊሊያም ሀሪስ ኦሮሞ ወራሪና ቅኝ ገዢ ነው ያለውን አበሻ ለሚላቸው ገልብጦ በመስጠት ነው። ከፍ ሲል ከቀረበው የሀሪስ ሀተታ የሚያስረዳው የሸዋና የተቀሩት ሀብታም የኢትዮጵያ ክፈለ ሀገሮች ወራሪና ቅኝ ገዢ ኦሮሞ እንደሆነ እንጂ ጸጋየ እንዳለው ከኦሮሞ ውጭ የሆነው አበሻ በተለይም አማራ አይደለም።
    ምን ይሄ ብቻ! ደፋሩ ጸጋዬ ከኦሮሞ በስተቀር ያለውን የአዲስ አበባ ኗሪ “መጤ፣ ወራሪ፣ ሰፋሪና ቅኝ ገዢ” አድርጎ ለማሳየት የተጠቀመበት የዊሊያም ሀሪስ መጽሐፉ በገጽ 244 ላይ ስለ ኦሮሞ “But the glory had departed from the house of Ethiopia, her power had been prostrated before the mighty conqueror and his wild band; and the Galla hordes, pouring flagrante hello into the richest provinces, from southern Central Africa, reerected heathen shrines during the reign of anarchy, and rose and flourished on her ruins.” የተባለውን እሱ በአዲስ ስታንዳድር ላይ ባወጣው ጽሁፍ ለኦሮሞ የተባለውን ገልብጦ የሌለ ተረክ ይነግረናል።
    ባጭሩ ጸጋዬ አራርሳ ከኦሮሞ ውጭ ያለው የአዲስ አበባ ነዋሪ “an occupying force of settler colonialists bent on pushing out and displacing the indigenous Oromo peoples” ሲል ሀሪስን አጣቅሶ ያቀረበው ክስ መሰረት የሌለው የጸጋዬ የራሱ ፈጠራ ነው። እንዴውም በተቃራዊው ጸጋዬ ከኦሮሞ ውጭ የሆነውን የአዲስ አበባን ነዋሪ “an occupying force of settler colonialists bent on pushing out and displacing the indigenous Oromo peoples” ለማለት በማስረጃነት የተጠቀመበት የዊሊያም ሀሪስ መጽሐፉ ሸዋን ጨምሮ ለም የሆኑ የኢትዮጵያ ክፍለ አገሮችን ወራሪና ቅኝ ገዢ የሚለው ኦሮሞን ነው።
    ከዊሊያም ሀሪስ በተጨማሪ በዘመኑ ሸዋን የጎበኙ ሌሎች የውጭ አገር ተጓዦችም ማስታወሻቸውን ትተው አልፈዋል። ለምሳሌ የኦሮሞ ብሔርተኛ ነን የሚሉ ግለሰቦች በብዛት የሚጠቅሱት ዮዋን ክራምፍ አንዱ ነው። JOURNALS OF THE REV. MESSRS. ISENBEEG AND KRAPF, MISSIONARIES OF THE CHURCH MISSIONARY SOCIETY, DETAILING THEIR PROCEEDINGS IN THE KINGDOM OF SHOA, AND JOURNEYS IN OTHER PARTS OF ABYSSINIA, IN THE YEARS 18-39, 1840, 1841, AND 1842. በሚል በቀረበ መጽሐፍ ላይ የሰፈረው የዮዋን ክራምፍ ማስታወሻ እንደሚያስረዳው ጸጋዬ አማራ እንደወረረው ሊነግረን ወደሚፈልገው ወደ አዲስ አበባ ወይንም ወደ ሸዋ ምድር ብቻ ሳይሆን የአቢሲኒያ ምድር ወደ ሆነው ወደ ባሌም ኦሮሞዎች የገቡት ግራኝ አሕመድ አቢሲኒያን ወርሮ ሕዝቦቿን ከገደለና ኗሪዎችን ካፈናቀለ በኋላ እ.ኤ.አ በ1559 ዓ.ም. እንደሆነ ይነግረናል።
    ይህንን ከፍ ብሎ የቀረበውን ታሪክ ዮዋን ክራምፕ እንዲህ ሲል ያስቀምጠዋል፤ “Adjoining to and south-eastward of Efat is the district of Gan, and adjoining and eastward of it again is Bali, a small kingdom, through which the Gallas first rushed into Abyssinia in 1559, Bali is west south-west of Zeilah, and south-west of Mocawa. Fattigar, once a considerable province, lies to the southward and south-westward of Gan and Bali of the ancient Mahomedans.” ከዚህ የምንረዳው ጸጋዬ “an occupying force of settler colonialists bent on pushing out and displacing the indigenous people” ሲል ያቀረበው ተረክ [narrative] የሚገልጸውና ወራሪው ኦሮሞ እንጂ ጸጋዬ እንዳለው ከኦሮሞ ውጭ የሆነው የአዲስ አበባ ኗሪ አይደለም።
    ከዚህ በተጨማሪ ዮዋን ክራፕፍ ንጉሱ በሌላ ጊዜ ወደ ጉራጌና አካባቢው ሲጓዝ አብሯቸው ተጉዞ ኖሮ በጉዟቸው የሚያገኟቸው ኦሮሞዎች ንጉሱ ፊት እየቀረቡ ግብር ያስገቡ እንደነበር፣ ንጉሱም በኦሮምኛ እንደሚያነጋግሯቸው፤ ሹመትና ሽልማት እየሰጡ በአካባቢው በሰፈሩ ኦሮሞዎች መሀል አልፈው ጉራጌ እንደደረሱ ያወሳል። ከጉራጌ ጉዞ በኋላ በእንጦጦ ዞረው ወደ አንኮበር እንደተመሰሉ፤ እንጦጦ ላይ በግራኝ ወረራ የፈረሰ የቤተ ክርስቲያን ቅሪት እንዳለና በዚሁ የግራኝ ወረራ ወቅት የፈረሰችና የበርካታ አቢሲኒያ ነገስታት መናገሻ ሆና ታገለግል የነበረች ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ እንደነበረችና ከመፍረሷ በፊት ዓፄ ልብነ ድንግል ለመጨረሻ ጊዜ በዋና ከተማነት ይገለገልባት እንደነበር ይተርካል።
    የጸጋዬን ተረክ [narrative] መሰረት አልባነት ለማስረገጥ እሱ ራሱ በጽሁፉ ካቀረባቸው የውጭ አገር ጎብኝዎች በተጨማሪ የግራኝ አሕመድ ወረራን የከበተውን የአረብ ፋቂህን መጽሐፍ Futuh Al-Habasha: The Conquest of Abyssinia [16 century]፣ የበርሙዴዝን “The Portuguese expedition to Abyssinia in 1541-1543”፣ ወዘተ ማቅረብም ይቻላል።
    እንግዲህ! ይህ ሁሉ ማስረጃ ከፊታችን ተቀምጦ ነው የሕግ ባለሙያው ጸጋዬ አራርሳ የልብነ ድንግልን ልጆች ያያታቸው ዋና ከተማ ለነበረችው ለእንጦጦና አዲስ አበባ ዙሪያ መጤና የዋና ከተማችን እንግዳ አድርጎ ሊያቀርባቸው የፈልገው። ጸጋዬ በአዲስ ስታንዳርድ መጽሔት ያቀረበው ድፍረት የተሞላበት ጽሁፍ ዊሊያም ሀሪስ በሳህለ ሥላሴ ዘመን በፍል ውሀ በኩል አድርገው ወደ ጉራጌ ሲሄዱ ኦሮሞዎችን አገኘን ያለውን ትርክት አዛብቶ በማቅረብ ከሸዋ አልፈው ወደ አያቶቻቸው ርስት ወደ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ የትውልድ ምድር ወደ ፈጠጋር [ሐረርጌ አዋሳኝ] ሳህለ ሥላሴ ያደረጉትን ጉዞ ጠምዝዞ ኦሮሞዎችን ብቸኛ የአዲስ አበባ ባለቤቶች፤ በግራኝ ወረራ ምክንያት የሞቱና ከርስታቸው የተፈናቀሉትን ደግሞ ለአዲስ አበባ እንግዳና መጤ አድርጎ አቃርኖ ማቅረቡ የምሁር ዋነኛ ባህሪ ማለትም integrityን የሌለው መሆኑን ከማሳየቱ ባለፈ ታሪካዊ እውነታውን አይለውጠውም።
    ከግራኝ ወረራ በኋላ በየዘመኑ የነገሱት የኢትዮጵያ ነገስታት ሁሉ በየዘመናቸው ፈርሳ የነበረችውን የአያቶቻቸውን አገር አንድ ለማድረግ ሲጥሩ የነበሩት በግራኝ አህመድ ወረራ የተበታተኑትን የኢትዮጵያ ክፍለ አገሮች እንደበፊቱ አንድ ለማድረግ እንጂ ጸጋዬ ሊነግረን እንደሚፈልገው ቅኝ ግዛት ፍለጋና ለወረራ አልነበረ። የእንግሊዙ ዊሊያም ሀሪስና የፈረንሳዩ ቴዎፍሎስ ሌፌቭር የሚነግሩን ይህንን ሀቅ ነው። ኢትዮጵያ [በካርታም ላይ ቢሆን] እስካለች ድረስ አዲስ አበባ የመላው አትዮጵያዊያን፣ የአፍሪካዊያንና የዓለም ከተማ ነች፤ ከኦሮሞ ጀምሮ የመላው አትዮጵያዊ ከተማ ሆና ትኖራለች። ይግባኝ በአቻምየለህ ታምሩ!

  8. አቤት አቤት ገና አሁን እሳት የላሰ ጸሀፊ ተገኘ ይባላል ብለህ አስበክ ከሆነ መልሳችን በጊዜ የማይነቃ ፋራ ነው በቃ እያልን ይህን ጽሁፍ ለተክሌ ይሻው ብታነብለት ለየት ያለ አድናቆት የምታገኝ ይመስለኛል። ዘረጦ ነገር

  9. Mind sick neftgna your day is over tplf days is over. No single new generation accept your dirty idea to undermine oromo child. while you are jealously dying for oromo land you land is being divided by tplf to tigrai and Sudan. you have no right to talk about oromo children business oromo can defend themselves they do not ask for your help. you want tplf stay in power for jealously of oromo children. whether you wanted or not tplf is falling soon. you jealously does not take you any where. the brave oromo children and peaces love other Ethiopians will work together and live together. naftegh you have no place in oromia.

    you did not have home land you cry for Africa to take finine. you day dream. made you loss Gonder to tigre and Sudan. how on earth you can protect Ethiopia when infect you couldn’t protect Gonder. Do worry about
    Ethiopian. Ethiopian will be protected by Oromo children and others peace loving people
    your outdated idea make that country what we are facing currently. Because of you neftgna tplf is destroying the paradise country. you will regret if you do not stop from this your outdated idea. for ever.
    neftegna and wayane tplf hate oromo children because they are destroying plf while neftgna is sleeping. The Ethiopian people never ever listen for neftegna and tplf. they are listing to oromo children Qeeroo and Jowhar Mahamed. they will live together peaceful on that land not like neftgna and tplf want. they will live together in democracy where every body live by the rule of the law.

  10. Why is the concerns of Oromo activists be the headache of Tigrean thugs and Menilikian old dogs? Go fuck your fictitious ‘Ethiopia’ and leave Oromo alone!You have nothing to offer us!

  11. The writer and his kinds used to say and believe the same thing about Eritrea, and they witnessed in horror when Eritrea is gone for ever. Had the Eritreans not been mistreated and been handled and understood with ultimate care, the result would have beenjoyed much different. These guys are delusional self-righteous megalomaniac and are in a continous state of denial of history and the current reality on the ground; and they believe that God is one of their tribesmen and help them with all their misdeeds and wrong doings. My advice for them is that you are not special to God and God does not approve or help any injustice perpetrated by whomever. If you want to save Ethiopia: 1) Recognize that you have no monopoly over Ethiopia. You or your group are not the decision makers. 2) Accept the historical injustices perpetrated by your past and current leaders and repent for your blind support and approval of their crimes, 3) Prepare yourselves to sit down as equals with all the nations/people of the country. Remember: do not to expect special Absynian/northern priveldge, 4) And finally psychologically prepare yourselves to accept when and if a leader is elected from the south. Otherwise your bravado and double-talk will not save your archaic Ethiopia. Thanks.

  12. The writer and his kinds used to say and believe the same thing about Eritrea, and they witnessed in horror when Eritrea is gone for ever. Had the Eritreans not been mistreated and been handled and understood with ultimate care, the result would have been much different. These guys are delusional self-righteous megalomaniac and are in a continous state of denial of history and the current reality on the ground; and they believe that God is one of their tribesmen and help them with all their misdeeds and wrong doings. My advice for them is that you are not special to God and God does not approve or help any injustice perpetrated by whomever. If you want to save Ethiopia: 1) Recognize that you have no monopoly over Ethiopia. You or your group are not the decision makers. 2) Accept the historical injustices perpetrated by your past and current leaders and repent for your blind support and approval of their crimes, 3) Prepare yourselves to sit down as equals with all the nations/people of the country. Remember: do not to expect special Absynian/northern priveldge, 4) And finally psychologically prepare yourselves to accept when and if a leader is elected from the south. Otherwise your bravado and double-talk will not save your archaic Ethiopia. Thanks.

    OM 
    September 9, 2017 at 5:31 pm
    Reply

  13. the more you hate oromo children the more people love them. the more you belittle yourself. naftegna you dirty deed will belittle you more. oromo children are determined for their right and freedom. This guys will govern you soon.They are the one who protect Ethiopia. while you are barking at them they are doing extraordinary job to free all Ethiopians from fascist tplf. you will go to hell with tplf babda.

  14. This message is for sisay Agena. Please do not start speaking like naftegna. you were professional journalist. who value his professional, but now neftegnas are putting you on the discussion that has meaningless. we are watching you the word you use. the Oromo straggle is continue no one can stop it. the freedom is in our door step. it better for every body not to spoil it. We had great respect for you. Oromo people never hate any one. Ethiopian people are read to send tplf to hell. But ESAT is working opposite.

Comments are closed.

Share