እኛ በኛ እንኩራ

እንደ ትላንትናው ፣ እንዳባቶቻችን

ከመሃል ከተማ ፣ እስከ ጠረፋችን

ካመፀኞች ጋራ ፣ ይጀመር ፍልሚያችን

ምንሽር ጓንዴውን ፣ ያጩኸው ህዝባችን ።

አገሬ ኢትዮጵያ ፣ ቴዎድሮስ ያደገባት

ጋራው ሸንተረሩ ፣  ታሪክ የሰራባት

ሜዳ መስሎት ዛሬ ፣ ባንዳው ፈነጨባት ።

ሞቅ ሞቅ አድርገው ፣ ወያኔ ይሸበር

ትንፋሽ አሳጥረው ፣ በማሰው ይቀበር ።

ለእናት ኢትዮጵያ ፣ ባንድነት ዝመቱ

ትርጉም አልባ ፣ እንዳይሆን አገሬ ማለቱ

ግዴታን መወጣት ፣ ይሁን እንደጥንቱ

ሬሳን ይመስል ፣ ይብቃ መጨመቱ ።

ሁሉም ጦሩን ያንሳ ፣ ጠላት ላይሆን ወዳጅ

ሉአላዊነቱን ፣ ያስከብር በግዳጅ ።

ጀግና የጀግና ልጅ ፣ የሃገር አለኝታ

ግንባሩን የሚሰጥ ፣ ሳይፈራ ላንዳፍታ

ና ግጠመኝ የሚል ፣ ሞልቶ በየቦታ

ውድ የሚሞትላት ፣ አገሬ መች አጥታ ።

ህጻን ሽማግሌ ፣ ወጣት ወንድ ሴቱ

ዝናን ያተረፈ ፣ ዛሬም እንደጥንቱ

ባገሩ የሚኮራ ፣ ቆፍጣናና ብርቱ

ችግር የማይፈታው ፣ የጥንት የጠኋቱ

ንቅንቅ የማይለው ፣ ቆርጧል አንዴ ሃሞቱ ።

ያሳለፍነው ይብቃ ፣ ጠንክረን እንስራ

ሸክማችንም ይቅለል ፣ እኛ በኛ እንኩራ

ንፋስ ሳይገባብን ፣ ባንድነት በጋራ

ፋኖው ተነስና ፣ ጓዶችህን ጥራ

ልክህን አሳየው ፣ ለባንዳው ኩታራ ።

 

 

ታዛቢው

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአፍሪካ አምባገነን መሪዎችና የብዕር ጀግኖቿ ጦርነት
Share