አቡነ ሳሙኤል ከእጩ ፓትርያርክነት ስማቸው እንዲነሳ የተደረገበት ምክንያት ተጋለጠ

(ዘ-ሐበሻ) በብዙዎች ዘንድ 6ኛው ፓትርያርክ እንደሚሆኑ ሲገለጽላቸው የነበሩት፣ በድምጽም አሸንፈው የነበሩትና ራሳቸውም “መንግስት እኔን ፓትርያርክ አድርጎ መሾም ይፈልጋል” በሚል ሲናገሩ የቆዩት አቡነ ሳሙኤል ባለቀ ሰዓት ከእጩ ፓትርያርኮች ውጭ ሊሆኑበት የቻለው ምክንያት ከአቡነ ጳውሎስ ደጋፊ ከሆኑትና አሁን አቡነ ማቲያስን ማሾም የሚፈልጉት እነ ንቡረ እድ ኤልያስ እና ወ/ሮ እጅጋየሁ ግሩፕ በአሸናፊነት በመውጣቱና ለመንግስት “አክራሪ ናቸው” የሚል ጥቆማ በማቅረባቸው እንደሆነ ተዘገበ።
እንደ ሃራ ተዋህዶ ዘገባ አካሄዱን ተቃውመዋል የተባሉትን የአስመራጭ ኮሚቴውን አባላት በተናጠል በማስፈራራትና ተስማምተው እንዲፈርሙ በማድረግ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ከዕጩነት ዝርዝር እንዲወጡ የተደረገበት ዋነኛው ምክንያት ‹‹በሃይማኖት አክራሪነት ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት የበላይነት ብቻ ነው የሚሠሩት›› የሚለው የተዛባ አመለካከት፣ ቂምና ጥላቻ የወለደው ክሥ ነው፡፡ የመንግሥትን የደኅንነት መዋቅር የሚታከከው ይኸው “የጨለማው ቡድን” የሚል ስያሜ የተሰጠው አካል ይህን ክሡን ያጠናከረው ብፁዕነታቸው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት በጅማና በኢሉ አባ ቦራ በጽንፈኞች የተፈጸመውን አሠቃቂ ሽብር በሀ/ስብከቱ ጋዜጣ – ኆኅተ ጥበብ – እንዲዘገብ አድርገዋል፤ በሃይማኖት መቻቻልና በእስላማዊ አክራሪነት ዙሪያ ያሳተሟቸውን መጻሕፍት በመጥቀስ ነው ሲል ሐራ ዘግቧል።
“የጨለማውን ቡድን” እኒህን ክሦቹን በማጠናከር፣ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ከዕጩዎች ዝርዝር ተካተው በፓትርያሪክነት ለመመረጥ ከበቁ ‹‹የሃይማኖት መቻቻል እንዳይኖር ያደርጋሉ›› የሚል ለመንግሥት የሚስብ መስሎ የሚታይ፣ በሐቀኛ ገጹ ግን አንድም÷ የአድርብዬ ጠባይ የተጠናወተው፣ አንድም በቡድኑ ለፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኞች ድጋፍ የሚሰጡ ሕገ ወጥ ግለሰቦችና ቡድኖች መሠሪ ተንኰል በተገፋ አቋሙ ለጊዜውም ቢኾን ያሰበው የተሰካለት መስሎ ታይቷል፡፡ ያለው ድረ ገጹ “ታድያ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ይህ ቡድን ነፍስ ዘርቶ ሊጠናከርበት ያደባበት የምርጫ ሂደትና የምርጫ ውጤት አካል አንኾንም፤ አናደምቅም ቢሉ ቅር ያሰኛልን? የብዙዎች ጥያቄ ነው” ሲል ዘገባውን አጠናቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  እውን አብዮት ማለት የነበረውን እንዳልነበር ማድረግ ማለት ነው? - ጠገናው ጎሹ

በነገራችን ላይ ሐበሻ ድረ ገጽ ኦክቶበር 11 ቀን 2012 ዓ/ም መንግስት በፓትርያርክነት ለማስቀመጥ ከሚፈልጋቸው መካከል አቡነ ማቲያስ አንዱ መሆናቸውን ዘግባ ነበር። (ይህን ዘገባ ለግንዛቤ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)

11 Comments

  1. This reportage seems to focus more on wild speculation which is obviously rampant in Amest Kilo these days, than the reality on the ground. The truth is no one knows for sure the names of Archbishops who passed the first round of the election process until the Holy Synod approves the nominations of the Election Committee. What is true, however, is the fact that the Abba Samuel camp is being hit by one allegations after another making it extremely difficult for the Electoral Committee to reach a consensual agreement on recommending him to the Holy Synod. As the Election Committee has stated clearly what matters most in this selection is not the number of people who have nominated a particular Archbishop, but rather whether or not the nominated Archbishop does have what it takes to retain and maintain the traditions of EOTC in a fast changing Ethiopia. Don’t let us, therefore, lose sight of the fact that a Church which is brought into being by the Blood and Flesh of Jesus Christ is governed by Theocracy and not Democracy.
    Finally, if Z-Habesha wants to be taken seriously by its readers, then it must avoid “yemender weary” like a plague. Please give a chance to God to install His Shepered on the Holy See.

  2. When are you guys going to stop lying, lies over lies over lies….you are worst than ETV…..ye taxi Tera woreyachihun eyametachihu tizefezifalachihu denkoro taxi neji hulu

  3. Zehabesha, please get your reports based on facts and clean your personality from hearsays. I like your websites, but you need to clean it a little bit. You posted a while ago condemning Samuel as a woyane Tigreans who is going to be elected by woyane. Now you did a 360 degree turn and you are telling us he is purged because woyane thinks he is akrari Orthodox? Something is fish and not right. How is this Pope now become Akrari orthodox from akrari woyane? No, no, get it right. This type of wild reporting will not help our people and country. This is not politics.

  4. I have already told you. It is one and the same, whether the patriarch is abune samuel or abune matheyas nothing will change both are TPLF. the patriarch is Sibhat Nega and the synod is TPLF. Guys don`t fool your self everything is under TPLF.

  5. Hello, you are opposing everyone. Whom do you want then? Everyone is woyane TPLF? even if the person is Oromo or amhara he is woyane or TPLF? You cannot oppose everyone arbitrarily. You need to oppose a reasons not because someone is Tigreans or Oromo or Woiyta or any. This is sickenning honestly. I think you wanted a muslim Imam? kkkk, seriously whom do you want? Merkoriious? Merkorious is yekesere Patriarch. He run away by betraying 60 million people to live American life. He was wrong given the high post, his grace, but he is a disgrace for our church. Merkorious is hodam and materialist like everyone of us; he is not better than me and you. He came to America to live An American life. He is also stupid because he has no respect for the Ethiopian people even. He is claiming the Ethiopians in Ethiopia are nothing worthy and he is telling us he has taken the office to become refugee in USA? He is an idiot and I do not even know who put in that position in the first place. I have listened to this renegede rebellious patriarch. He lies very much and watch him the way he talks. If he brave enough let him tell us how was removed from his high post. But he is coward and infidel, apostate and he has no gut to stand either for the 60 million followers or for himself. He Charlatan. All he is doing is unceremonious evil and immature. He has no any wisdom. The story will over after the election and he continue playing religious politics. A loser, yekesere patriarch.

    • @Gzaee hailemichael…you see how stupid you are like your father Sibhat Nega..i am hating tigre because of stupid person like you and your idiot father Sibhat nega.

  6. ዘሃበሻ ስለዲቨሎፒንግ ስቶሪዎቹ እናመሰግናለን… በአቡነ ሳሙኤል ጉዳይ ስታቀርቡት የነበረው ተከታታይ ዘገባዎች ከየት ተነስቶ የት እንደደረሰ አስቃንቶናል.. አንዳንዱ ዝም ብሎ ማንበብ ሳይችል ር ዕስ እየተመለከተ እንደተሳሳታችሁ አድርጎ ሊያስቀመጥ ይችላል… ምንም ውሸት ስላላየሁበት ደስ ብሎኛል… በተለይም የአቡነ ጳውሎስ ደጋፊዎች አሸነፉ የሚለው ዘገባችሁና ከዛም በትግራይ ጳጳሳት መካከል ልዩነት እንዳለ የዘገባችሁት ዘገባ በሁለቱ መካከልም የአቡነ ሳሙኤል ደጋፊና የአቡነ ጳውሎስ ደጋፊ የሚል መውጣቱን በመጨረሻ መንግስት ከሁለቱ ወያኔ ጳፓሳት አቡነ ማቲያስና አቡነ ሳሙኤል አንዱን እንዲመርጥ ተገዷል…. አቡነ ሳሙኤል አክራሪ ናቸው በሚል በአቡነ ፓውሎስ ደጋፊዎች ተወንጅለው መንግስት ለጊዜው ባያስመርጣቸውም አቡነ ማቲያስም ያው ናቸው… እናንተው ከ3 ወር በፊት ‘መንግስት በፓትርያርክነት ሊሾማቸው ከሚፈልጋቸው ፓትርያርኮች መካከል አቡነ ማቲያስን በአንደኝነት አስምቀጣችሁ አንብቤአለሁና’/// በቀለም ተሾመ ገብረህይወት ወያኔ ካልወደቀ ይህች ቤ/ክ ሰላም የላትም

Comments are closed.

Share