የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች | ከክንፉ አሰፋ

መገናኛ ብዙሃንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን  ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም።  ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው  ኦነግንም ቢሆን ‘A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሜድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም።

ጃዋር  በኢትዮጵያ  የፖለቲካ ብቅ ያለው በቅርቡ ነው። በመጀመርያም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በተማረባቸው ዱሙጋም   እና  ጭላሎ፣ አዳማም  ሆን  ሲንጋፖር ሆኖ ድምጹ  አልተሰማም። የፖለቲካ ሂሳቡን ሰርቶ ሲያበቃ የበግ ለምድ ለብሶ ብቅ አለ።  በሚኖሶታ ያለመውን  ቅዠት ይዞ  ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ሲደርስ ባነነ። እዚያው  ላይ ፈነዳ። ከዚያ በፊት ስሙም ተሰምቶ አያውቅም። እስከ ዲሲ ጉዞ ድረስ የኦሮሞ ህመም አይሰማውም ነበር። “ትንሽ ቆሉ ይዞ ወደ አሻሮው… “ እንዲሉ የኦሮሞነት ጆከሩን ይዞ ፖለቲከኞችን እና መገናኘ ብዙሃኑን  መቅረብ ነበረበት።  እነሱም ከሚገባው በላይ አስተዋወቁት። በደንብ አድርጎ ቦነሳቸው። ምሁር በሃገር የጠፋ እስኪመስል ድረስ መድረኩን  እሱ በቻ ተቆጣጠረው።  ቪ.ኦ.ኤ.፣  አልጃዚራ፣ ሲ.ኤን. ኤን፣  እና ዶች ቬለ ላይ ሳይቀር እየወጣ የኛን እጣ ፈንታ እስኪበቃን ነገረን።  “ወጣቱ ምሁር”  አንቱ የተባለ የኢትዮጵያ  ጉዳይ ተንታኝ ሆኖ ከረመ።  ድምሩን ካወራረድ በኋላ ፊቱን አዞረ። አዟዟሩ አደገኛ ነው። የፍሬቻ ምልክት ሳያሳይ እንደሚታጠፍ መኪና አይነት። “ይህ ሰው በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የጫነው ዲግሪ  ነው ወይንስ ድንጋይ?”  እስኪያስብል ድረስ በዘርና በሃይማኖት በፖለቲካ  ፈነዳ።

ባጣ ቆዩን ትግል ሲቀላቀል ለአፍ  ሟሟሻው  አጼ ምኒሊክን  አነሳ። የእምዬ ምኒሊክ አጽም እና ሃውልት ላይ ክተት አወጀ። ግዜ የሰጠው ቅል… እንዲሉ እንጂ የመላው ጥቁር ሕዝብ ማንነት መነሻ የሆኑት ምኒሊክ በሱ አፍ የሚጠሩ እንኳን አልነበሩም። ዳሩ መነሻውን የማያቅ መድረሻ የለውም። ሁለት አይን ያለው፤ ከሁለት አቅጣጫ ይመለከታል።  ሁለት ጆሮ ያለውም ሁሉንም አመዛዝኖ ይሰማል።  አንገት ያለው ደግሞ  አዙሮ ያለፈውን ይመለከታል። ያለፈው ከሌለ የወደፊቱ ከምን ሊነሳ? ጃዋር  በአምሳሉ  የፈጠራቸውን  ምስለኔዎችን   በሱ የፖለቲካ ዜማ ቃኝቶ ሲያበቃ በፓልቶክ ክፍሎች አሰማራቸው።

ከሁሉም የሚያሳዝነው  ደግሞ ገና ነብስ ያላወቁ ሕጻናትን ፎቶ በማህበራዊ ድረ-ገጾች እየበተኑ ለራሳቸው የፖለቲካ ግብ መጠቀም መሞከራቸው ነው። በሞራልም፣ በስነ-ምግባርም ሆነ  በባህል  ፍጹም ነውር የሆኑ ነገሮችን እያሰሙን አብረን ከረምን።  በቃ! የጃዋር ፖለቲካ ይኸው ነው።   ይህ ነው የሱ ጀግነነት።  ምኞቱ ጀግና መሆን ከሆነ ደግሞ ቦታው  ሚነሶታ አልነበረም።  ስለ አመጽ የሚሰብክ ወንድ ልጅ መኖርያው ልክ እንደ አንበሳ ከወደ በረሃው ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሁለቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው ኢትዮጵያ ውስጥ ከትመዋል! - ግርማ በላይ

ይህ ሰው በፌስቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረውን አንድ ጽሁፍ ካነበብኩ በኋላ፤ ለዚያ አሳፋሪ  ጽሁፍ ምላሽ በመስጠት እና ባለመስጠት ላይ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜ ነበር። በጃዋር ገጽ ላይ የሰፈረው በዚያ አስጸያፊ ጽሁፍ ያልቆሰለ ቢኖር ጉዳዩ ያልገባው ብቻ መሆን አለበት።  በእርግጥ ሌሎች እንዳደረጉት ነገሩን  ንቆ  መተው ይቻላል።  ታድይ የሰው ዝምታ እንደስምምነት የተወሰደ ይመስል የሰውዬው ሙቀት እየጨመረ ሄደ። በተቀረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ላይ የጥላቻ ዘመቻውን ገፋበት። በዓድዋ እና የአጼ ምኒሊክን ቅኝት በአዲስ ዜማ ይዞ ዳግም ብቅ አለ። እንደራሴውን በስውር እየሰበሰበ በባንድራችንና በኢትዮጵያዊነት ላይ ዘመቻ አቀደ። ይህንን በሰፊው እመለስበታለሁ።

በፌስቡክ ገጹ ላይ የሰፈረው የጃዋር መልእክት እንዲህ ይነበባል፤

…Enjoy the show, the bill is on us… ወደ አማርኛ በግርድፉ ሲመለስ “(የኦሮሞ አመጽ) ትዕይንቱን እያያችሁ ተዝናኑ። ሂሳቡን በኛ ተውት።”  እንደማለት ነው።

አሳዛኙን  የኦሮሞ  ወገኖቻችን  እልቂት ነው ተዝናኑበት እያለን ያለው።  ይህንን አሰቃቂ ድራማ ከሚነሶታ ሆኖ ሲመለከተው   አስቂኝ ነው  የሆነበት። እሱ ምን አለበት? እሳቱ  ውስጥ አልገባ።  ወላፈኑም ፈጽሞ አይነካው። ምሰቆቃውን እንደ ሆሊውድ ፊልም  ቁጭ ብሎ መመልከቱ ሳይንሰው ሌሎችንም በራሱ ወጪ  ለመጋበዝ የሚዳዳው ደፋር።  ይህ  ስላቅ ነው ወይስ  ፌዝ?  ከሞቀ ቤቱ መሽጎ  በሰው ልጅ ሰቆቃ መቀለዱ አንድ ነገር ነው። ከሁሉም  የሚያስገርመው ደግሞ በዚህ ጽሁፍ ስር ድጋፋቸውን የሚገልጹ   እንደራሴዎቹ ብዛት ነው። ሰው በዘር ፖለቲካ ሰክሮ ማሰብና ማገናዘብ ተስኖታልም ያሰኛል። ጽሁፉ በግልጽ እንደሚያስረዳው እየተካሀደ ያለው እልቂት ላይ ጃዋር ማፌዙ አልገባቸው ይሆን? በዚያው የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የሚወጡ  ዘግናኝ ፎቶዎችን  እየተመለከተ የሚዝናና ሰው  ካለ ይህ ጤነኛ አይደለም። የአእምሮ ችግር ያለበስ ሰው እንኳን በዚህ አይነቱ የሰዎች ሰቆቃ  የሚዝናና አይመስለኝም። ግን የዚህ ሰው ፍላጎት ምን ይሆን?

በዚያ ሰሞን ወዳጄ ሄኖክ የሺጥላ የለቀቀው ጽሁፍ ጃዋርን በደንብ አድርጎ ይገልጸዋል።

“እንጀራውን” በተገፉ እና በተከፉ ሰዎች ታሪክ ላይ ያደረገ ሰው ፣ ህይወቱን በሰዎች መከራ ላይ የገነባ ፣ ኑሮውን ባጋጣሚ ለድምጽ አልባ እና አቅም አልባ ወገኖቹ  ለታይታ የሚቆጭ…. ራሱን ትልቅ ለማድረግ፣ ከፊት ሆኖ ለመታየት እና ለመግነን ማናቸውንም አይነት ክፋት ከመፈጸም ልቡ ተው የማይለው ሰው።  ሲል ሄኖክ ይገልጸዋል። እኔም ጃዋርን ከዚህ በተሻለ አልገልጸውም።

ሲጀመር እየተካሄድ ባለው የኦሮሞ ወንድሞቻችን የመብት ትግል ውስጥ የእነ ጃዋር እጅ መግባቱ አብዛኞችን ጥርጣሬ ውስጥ ከትቷል። ምክንያቱም ግልጽ ነው። የኦሮሞ ወጣቶች እና ገበሬዎች ስለ መብት ሲሟገቱ የእነ ጃዋር አጀንዳ ደግሞ ሌላ በመሆኑ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ግንቦት 20- የመከራ የስደትና ዘረኝነት አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ

የኦሮሞ ተማሪዎችና ገበሬዎች ይዘውት የተነሱት ጥያቄ አግባብ ያለውና በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊደገፍ የሚገባው ጉዳይ ሆኖ ሳለ ሌላው ወገን ዳር ቆሞ የመመልከቱ ምስጢር ግልጽ ይመስላል። እነዚህ ወገኖች መብታቸውን  ለማስከበር የማያባራ  ትግል እያደረጉ ባሉበት ወቅት እነጃዋር በረጅሙ ምላሳቸው ሌላውን ወገን የሚያስበረግጉ መፈክሮችን ይዘው ብቅ አሉ።  “ኦሮሚያ ለኦሮሞ!” እና “የክርስትያኑን አንገት መቁረጥ!”  መፈክር!

እርግጥ ነው። ጃዋር ረጅም  ምላስ አለው። ወገን የሚሻው ደግሞ ረጅም ምላስ ሳይሆን ረጅም  ጭንቅላት ነበር።  የሁለቱ  ልዩነት የትየለሌ ነው። ረጅም ጭንቅላት አርቆ ሲያስብ ረጅም ምላስ ደግሞ ከሩቅ ይስባል። እንደ አለመታደል ሆኖ ባለ ረጅም ምላሶች የህዝብን የመብት ጥያቄው እየነጠቁ በራሳቸው አጀንዳ ይተኩታል።  እናም የዚህ ትግል ውስጥ  ሌላው ወገን  ተመልካች ብቻ እንዲሆን ያደረጉት ጃዋር እና በሱ የፖለቲካ ቅኝት ውስጥ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ  ናቸው። እነዚህ ሰዎች ይዘውት የተነሱት መፈክር ሌላውን ወገን ባያስበረግግ  ነበር የሚገርመው። አንዳንድ ቦታዎች የጃዋርን መፈክር የያዙ ሰልፈኞችን  የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ማሰማራታቸውን ማስተዋሉ ለዚህ ማስረጃ ይሆናል።

በአንድ ወቅት  በጃዋር የሚመራ ይህ  ቡደን ዋሽንግተን ዲሲ ስቴት ዲፓርትመንት በር ላይ ቆሞ፣  “Ethiopia out of Oromia”!  “ኢትዮጵያ  ከኦሮሚያ ጥውጣ!”  እያለ ፈረንጆችን ይማጸን  የነበረበትን ማስረጃ ከዩቱብ ላይ መመልካት ይቻላል።

በሌላ ግዜ ደግሞ “…እኔ በምኖርበት አካባቢ ቀና የሚል ክርሲያን ከተገኘ አንገቱን  በሜንጫ ቆርጠን እንጥላለን::”

ሲል የአይሲስን አንገት  ቆረጣ በአደባባይ ያበሰረ ሰው ነው።    እዚህ ላይ ልብ በሉ። ወንጀል የሰራን ክርስትያንን  ሳይሆን “ቀና የሚል” ከተገኘ ነው እናርዳለን ያለው። ልቡ ያሰበውን እና አእምሮው የሚትያሰላስለውን ነው ያፈነዳው። የተናገረው በስህተት እንኳን ቢሆን ንግግሩን ባስተባበለው ነበር።

ከዶ/ር መረራ ጉዲና ጋር አንድ ምሽት በአምስተርዳም ስንጫወት፣ “በእርግጥ ጃዋር መሃመድ የክርስቲያን  አንገት  እቆርጣለሁ ብሎ ተናግሯል?” ሲል ጠየቀኝ። አብሮን የነበረው ገረሱ ቱፋም  “ንግግሩን  ከኮንቴክስት መረዳት አለብን…”  እያለ ሲያስረዳ  ሞከረ። ገረሱ ቱፋ በዩኒቨርሲቲ  ለኦሮሞ መብት ሲታገል ቆይቶ በኋላም በአስመራ በኩል ሞክሮ  ሲያበቃ በሆላንድ በስደት የሚኖር ወጣት ነው።  ኮንቴክስቱ ባይገለጽልንም  ከዩትዩብ ላይ ያወጣሁት ቪድዮ አንገት በሜንጫ ስለመቁረጥ በግልጽ አማርኛ አስቀምጦታል።  በዚያ እለት ነበር የኦሮሞ ሕዝብ በብዛት የሚኖረው በሸዋ እንድሆነና ይህም የክርስትና እምነት ተከታይ  መሆኑን ዶ/ር መረራ ያስረዳን።

በእነ ማልኮሜክስና በእነ ማርቲን ሉተር ምድር ቁጭ ብሎ አይሲስን አንገት መቅላት ወንጀል መናገሩ አይደለም የሚገርመው። ይህንን በአደባባይ በኩራት ሲናገር ህግ ባለበት ሃገር ዝም መባሉ እንጂ።

አል ጃዚራ ላይ ወጥቶ ኢትዮጵያዊነት በላዩ ላይ እንደተጫነበትም ደስኩሯል። ይህንን ዲስኩር ከሱ ውጭ ከሌሎች የኦሮሞ  ልሂቃን አልሰማንም። በማንነት ቀውስ ውስጥ ካለ ሰው ይህንን መስማቱም ሊደንቀን አይገባም። ይልቁንም ይህንን ከነ በቀለ ገርባ ፣ ከዶ/ር  መረራ፣  ከበአሉ  ግርማ ፣  ከሎረት ጸጋዬ ገ/መድህን፣  ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ወይንም ከአቶ ቡልቻ ደመቅሳ አንደበት ብንሰማው እበር የሚከብደን።      በእንደዚህ አይነት የጥላቻና የዘረኝነት እምሮው  የታወረ  ሰው  እመራዋለው የሚለው አመጽ ላይ ለማበር የኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃደኛ ባይሆን ሊደንቀን አይገባም።  ከየትኞቹም  የኦሮሞ  ልሂቃን  እንዲህ አይነት  የኦሮሞ ሕዝብን ክብር የሚነካ ንግግር ሰምተን አናውቅም። “ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ትውጣ” “የክርስትያኑን አንገት በሜንጫ እንቆርጣለን” ሲል የትኛው የኦሮሞ ወገን ወይንም የትኛው የሙስሊም  ህብረተሰብ  ጃዋርን  እንደወከለው አናውቅም።  ልቡን ሞልቶ ሲናገር ግን የኦሮሞን ህዝብ ከሌላው ወገን ነጥሎ ለማስመታት የታቀደ አደጋ ላይ ሊጥለው እንደሚችል ግልጽ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኤርያልን የገደለው!!!! .........

የፖለቲካውን ምህዳር ጠቆጣጥረው ዘረኝነትን እና ጥላቻን ሲሰብኩ ምን እናደርጋለን? ንቆ መተው ወይንስ ቀይ መብራት ማሳየት?  ቤንጃሚን  ፍራንክሊን፣  ስለጥቃቅን  ነገሮች  ሲናገር፣  “በጥቃቅን ነገር ተጠንቀቅ፤ ትንሽ ፍሳሽ – ትልቅ መርከብን ታሰምጣለች።” ብሎ ነበር።  በእርግጥ  መርከቡ ሊሰምጥ የሚችለው  ውሃ መርከብ  ውስጥ እንዲገባ  ስንፈቅድላት  ብቻ ነው።

የጃዋርን አካሄድ ሳሰላስለው ቦካሳ ይታወሰኛል። የትም አይደርስም  የተባው  የማእከላዊ  አፍሪካው አስር አለቃ  ቦካሳ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ አመጣጥ አላቸው። ሁለቱም በማንነታቸው የሚያፍሩበት የበታችነስ ስሜት ውስጥ የኖሩ ናቸው። ሁለቱም  የማንነት ቀውስ ውስጥ የነበሩ ናቸው። ጃዋር  በአንደበቱ  እንደነገረን  የአማራ እና  የኦሮሞ፣  የክርስትያን እና የሙስሊም ቅልቅል ነው። እንደዚህ የተበሳተሩ  ብዙ አሉ። አብዛኞቹ ታዲያ በማንነታቸው ይኮራሉ።   እንደ ጃዋር ያሉ ጥቂቶች ግን የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ቢገቡ አይደንቅም።  አባት እና እናቱን የማያውቀው ቦካሳ  ከ 12 አመቱ ጀምሮ የማንነት ጥያቄ  ሲያንገላታው የነበረ ሰው ነው። የም ሆኖ የትም አይደርስም እየተባለና የተናቀ ወታደር ነበር።  የሃገሪቱ  ርእሰ ብሄር ይሆናል ብሎ ያሰበ አልነበረም።  አስር አለቃ ቦካሳ በለስ ቀንቶት እ.ኤ አ. 1966 በመፈንቅለ መንግሰ ስልጣን ይዞ ሲያበቃ  የማእከላዊ አፍሪካን ህዝብ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ፈጀ ሀገሪቱን እንዳልነበረች አደረጋት።

ሰዎች ለአዶልፍ  ሂትለርም  የነበራቸው አመለካከት  ከዚህ የተለየ ልነበረም። አንድ  የጀርመን ታሪክ ተመራማሪ  ሁኔታውን ሲገልጸው “They all had one thing in common – they underestimated Hitler” ነበር ያለው። ሁሉም  የሚጋሩት አንድ ነገር ነበር።  ሁሉም  ሂትለርን ንቀውት ነበር። በመጨረሻ  ሂትለር የጀርመን  አዲሱ  ቻንስለር ሆኖ ብቅ ሲል የናዚ ፓርቲ አባላት በደስታ እና በእንባ ተቀበሉት።  በሀገሪቱ  ህግ ሳይሆን በሂትለር  አምላኪ ሆኑ።  የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ሳይሆን የጃዋር አምላኪዎች እያደረጉ እንዳሉት ማለት ነው።  ጃዋር “የእልቂቱን ትእይንት በኔ ሂሳብ እያያችሁ ተዝናኑበት” ያለውን  አጢነው አይመስለኝም። በደፈናው ስለሚያመልኩት እንጂ።

ቦካሳም ሆነ ሂትለር በጥላቻ የመጡ ስለነበሩ ከምደር-ገጽ ጠፍተው ታሪክ ሆነው አልፈዋል። ጥለውት የሄዱት አሻራ ግን እስካሁን አለ።

23 Comments

  1. Thank you Kinfu.

    Especially how he manipulated ESAT, Hiber radio etc….was, “Fool me once, shame on you. Fool me twice, shame on me.” May be ESAT, Hiber radio …..was trying to bridge differences. But this guy uses them at his discretion and he is master manipulator. He obivliusoy court them to advance his filthy ethnic/religion fanatic agenda. And he exploited them very well to ADVERTISE himself. He balantantly claimed this on his Facebook page and YouTube posted video stating that he is an “expert” and that “they need me more than I do”. We hope this time they learn a BIG lesson. Otherwise they will keep repeating the above famous quote of Randall Terry.

    God bless Ethiopia!

  2. Kinfu Assefa:

    It seems to me, you have expressed your fear and hate of the Oromo through the highlander take down and badmouthing of Jawar. Jawar is an embodiment of all Oromos who earned to be a Managing Director of the Oromo Media Network. Your continued tripping at the expense of the hate for Dr. Berhanu Nega and now Jawar makes me suspicious that you maybe a Woyane agent.

    To all other readers:

    I call upon all opposition political and armed groups to design a plan to liberate Ethiopia from Woyane Thugs by noting the state of Oromo uprising and the anticipated military confrontation with Eritrea. It is a very critical time for a coordinated action!

    I believe the opposition has to take note of the possibility of war breaking out in the near future if not any day now. This could bring or create both an opportunity and challenge for both the armed (OLF, ONLF, Arbegnoch Ginbot 7) and non-armed (ODF, Semayawi, Medrek, UEDF) opposition – not to be caught offguard, it is imperative on the part of the opposition to understand the timing and its implication and lead the Ethiopian people to freedom and democracy from the yoke of woyane tyranny.

    The opportunity comes from the fact that the enemy of my enemy is my friend – and the positive engagement of the opposition with the government of Eritrea is a testimony in that regard. This certainly creates a solid foundation and access to coordinate the military engagement of Woyane by OLF, ONLF, Arbegnoch Ginbot 7 and Eritrean forces – through spying on woyane forces and military strategy and sharing the information with Eritrean forces, by campaigning among the non-Tigrean portion of the Ethiopian Defense Forces to turn the gun onto Woyanes, by cutting supply routes within Ethiopia, by striking at woyane establishments within Ethiopia, by calling on the Amhara and Southern Region to join the Oromo mass uprising, call on students and teachers to protest, to strike against all woyane thugs and criminals who are killing and maiming people in Oromia, Gambella, Amhara, Ogaden etc, to strike against woyane prisons and free all prisoners of conscience. If the opposition is determined to work and plan on the general themes mentioned above, Woyane will be history within weeks – and the TPLF thugs and other criminals will be brought to justice!!!

    The challenge on the other hand is to be aware of the wolves in sheep skin within the opposition – the likes of Elias, Abebe Belew, Tekle Moresh etc.

  3. Kinfu,
    You think you are attacking Jawar, right? Did you notice that you are attacking Oromos who agree with Jawar’s opinion as his disciples who have no a mind of their own.
    First of all, Jawar is just echoing reports coming from the protesting Oromo youth directly from Oromia. Jawar’s role is just to air what has been sent to him. You are trying portray Jawar as the maker and shaker of the Oromoprotest. You are doing this deliberately to down play the sacrifices our kids are making. Second, Jawar is entitled to his opinion. The movement that has engulfed the Oromo country has its roots going ass far back as the 1960s and 70s coinciding with the inception of the OLF which is also your arch enemy.
    Mind your business! Jawar is just one out of millions and he is equally as enthusiastic as his Oromo peers in this revolution. The only difference is that Jawar is fast, he has the tools to disseminate what Oromos are doing and aspiring for. he is not leading the movement nor does he drive it in to bloody confrontation. You are condemning Jawar who post the dead body of Oromo children. But you are okay with the beasts who killed these children. Who the hell are you, idiot?
    Stop the mockery of down playing the fundamental demands of the Oromo Revolution. It has been there long before a Jawar or a Kinfu. If we think Jawar is crossing the line, it is up to us (Oromos) to discipline him. You have no business in here other keep barking.
    አፈር ብላ!!

  4. The ugly part of Ethiopian politics is always to fight each other. That gives TPLF 25 years to stay in power. Even we don’t know how to use the politics of the enemy of my enemy is my friend ,we dont know when to write some thing negative. Its good to focus on the cancer of Ethiopia TPLF before spreading in all part of the country.
    Thanks zehabesha for posting my comment

  5. U r really Stupid. u tried to push the weakness of other socalled unitarist groups to Jawar, how Trah u are, u are jealousy, u cant evaluate jawar with ur pity and dirty mind. Viva Jawar Mohammed

  6. Kinfu,
    Most of the time, your articles fail to recognize the legitimate struggle of Oromo people. I remember, when OMN was founded,it was not NEWS for you,rather you wrote about the disagreement between Jawar and Mohammed Ademo. Because Jawar’s doesn’t agree with you on Ethiopian politics doesn’t mean he is wrong ( you even questioned the validity of his degree).To me this is not a fair game. Let us play it fair!

  7. Kinfu Assefa,

    You exposed your ignorance and admitted how much you know of the Oromo people when you stated your conversation with Dr. Merera. That kind of mind set is the culprit for Ethiopia’s long political problem. It so happens that you are one of the architects of EPRP, if I understand it correctly. True to your organization’s strategy for over 40 years, the MO has been to encourage character assasination of people and organizations you don’t agree with. You “hanged” Dr. Haile Fida because he was an Oromo and a very charistmatic and strategic leader of our time. He was a very moderate political leader at the time until he was killed by the Derg. So you and your cohorts had to reduce him, kill him if you could in order to burry an Oromo politician. So it became clear that anti-Oromo poltical activists used that system of character assasination on any Oromo that comes upon the political platform of Ethiopia. Now there are Amhara extremists including you who have been calling for Jawar’s head. TPLF is now included in the game. So to support your hypothesis you have to create a caricuture of Hitler and Bokassa for Jawar. It doesn’t matter whether your childish game has any relevance. The reason is simple. Jawar and the elites of other marginalized people are distancing themselves and the population they come from your mold of Ethiopia. You are being left bare-handed. On the contrary, Jawar has been able to create a medium of communication among Oromos that have been denied to Oromos within the country and from outside. That is a pain for exclusive Ethiopianists. That is also for the same reason why Jawar has become a very prominent Oromo activist. He is a bright guy. People like you cannot even stand on the same platform as he is educationaly, politically..etc. So you want to bring him down to your level. One thing we know is that Jawar could be your son. You are an old timer whose time has gone by. That is not to deny that Jawar has his mistakes as a human being, but to call for the TPLF’s help to deal with Jawar is too extreme. On the other hand, you have no moral standing to tell the Oromo people what is right or wrong for them. What is clear is that people like you are no different from the TPLF who is currently engaged in mass killings. To be sure we will survive this atrocity with our head held high with the sacrifice of our people for a cause greater than induividual life.

    • PLEASE BE OBJECTIVE. ALL KINFU WROTE WAS FACT ON THE GROUND. THE TRUTH SPEAK FOR ITSELF. WHY DIDN’T YOU ADVICE JAWAR TO STOP MAKING RACIAL AND RELIGIOUS DEVICIVE STATEMENTS?

      JAWAR OPENED HIS STINCKING MOUTH AND SHOWED THE WORLD HIS MIND AND HEART. NOW WHEN SOMEONE TELLS THE TRUTH, YOU ARE FEELING THE PAIN.

      WHETHER YOU LIKE IT OR NOT, ALL OROMOS NEED TO READ KINFU’S ARTICLE AND THINK AGAIN.

  8. ጃዋር የኦሮምን ህዝብ እንደ ሃውዜን ለማስጨፍጨፍ ነው ምኞቱ
    ክንፉ ልክ ነህ
    እመሰግናለሁ

  9. እንዳንተ አይነት ምሁር፤ የድረ ገፅ ላይ ጀግና፤ አንተ የበግ ለምድ የለበስክ ተኩላ፤ ዛሬ የኦሮሞን ትግል እና ታጋይ ለማንኳሰስ፤ አማራና ኦሮሞን ደግሞ ለማቃቃር አንተና መሰሎችህ የምታደርጉት መንደፋደፍ በፍፁም አይሳካላችሁም፤ አማራና ኦሮሞ በደምም ጭምር ተዋህደዋል፤ ተዋልደዋልም፡፡ ጀዋር ምሁርና እውነተኛ ታጋይ የመሆኑን ሀቅ ላንተና ለመሰሎችህ ለመንገር ጊዜ አልፈጅም፤ ነገር ግን ስላንተ አላዋቂነት ጥቂት ለማለት እገደዳለሁ፤ ጀዋርን ለመተቸት ስትል ያንተን ባዶነት (ድሮም ባዶ ነህ) ነገርከን! በሰለጠነው ዓለም ውስጥ ሆነህ ምንንና ማንን፤ እንዴትና በምን አግባብ መተቸት እንዳለብህ ያላወቅህ፤ ግብረ ገብነት የሚጎድልህና ስለ ፖለቲካ ሰምተህ እንጂ አይተህ (ተመሳስለህ ከማስጠቃት ውጪ) የማታውቅ ድንጋይ ራስ መሆንህን ነገርከን!ለመሆኑ ወገኖችህን መሰለል ተውክን? በምርጫ 97 ዋዜማና ማግስት በወገኖችህ ላይ የሰራሀውን ሸፍጥ እስከ ዛሬ አልተናዘዝክምን? ንስሃ እንደመግባት ይባስ ብለህ ሀጢዓትህን ለምንም ትቆልላለህ? ጀዋር ክፋም ለማም ለወገኖቹ እየሰራ፤ እየታገለ ነው፤ እንደ….ወገን መስሎ ወገኖቹን እየሰለለ በየወገኖቹ ቤት በደረቅ ሌሊት ከፊት ቀድሞ ወያኔን እየመራ እልፍ አእላፍ ታጋዮች ወንድሞቹን በማስገደል፤ በማሳሰርና (ተመሳስሎ አብሮ በመታሰርም ጭምር)ወያኔ የሚጥልለትን ፍርፋሪ አይለቅምም፡፡ ይህን ስል ማንነቴን እንደምታውቅ በእርግጥ አውቃለሁ፤ እንተዋወቃለንም፤ ስለዚህ ጉዳይ ወደፊት በሰፊው እዚሁ ድረ ገፅ ላይ የጋዜጣ ቆሎ ላደርግልህ ቃል እገባልሃለሁ፡፡

    • ክንፉ እውነቱን ተናግሮ ጃዋርን ገደለው ነው የሚባለው

      ጃዋር ከዩንቨርሲት ዲግሪ ሳይሆን ዲንጋይ መጫኑን እስታውቕል

      ጃዋር ተዋርዶ የኦርምን ህዝብም ያዋረደ : በቅናት ተቃጥሎ በደም ፍላት ያበደ : ለሰው ህይወት ደንታ የሌለው ኦሽባሪ ነው

    • አቶ መስፍን ስለ አንተም ሆነ ስለ ምትቃወመው የኔ ያለህ ሰዉ ሰለማላቃቹህ በናንተ ላይ የምሰጠዉ አስተያየት የለኝም። በ ጁሃር የሚባል ሰው ግን፡ በተደጋጋሚ ከሚጽፈውና ከሚናገረዉ እንደተገነዘበኩት ግን የ ኦሮሞ ቤሄረሰብ ወዳጅ ወይም ተቆረቃሪ አይደለም በ ኢትዮብያ ያለዉ ገዢ ፖርቲም ጠላት አይደለም። እሱ የሞስሊሙ ማህበረ ሰብ ተቆርቃሪ በመምሰል ከሆነለት ታዋቂነት አግኝቶ ስልጣን ማግኘትና በ ሞስሊምና በክርስትና ሃይማኖት ግጭት ፈጥሮ ሃብት ማካበት ነዉ፡፡ እን ጁሃር የመሰሉ የ ሰዉ ሞት ምንም ደንታ የ ማይሰጣቸዉ ሰዎች ከዳር ሆኖ እሳቱን ማራገብ እንጂ እሳቱ አንደሚያቃጥል መሞከር አይፈልጉም፡፡ እሳቱ ከቀዘቀዘ በኃላ ግን ስልጣን ለ መያዝ ይሞክራሉ፡፡ ስለዚህ ወንድሜ መስፍን አስተያየት ስትጽፍ ሰዎች ስለምትወዳቸው ወይም ስለምትጠላቸው ሳይሆን፡፡ ጽሑፋቸው ወይም ንግግራቸዉ ካለው ጠቀሜታ እና ጉዳቱ ያገናዘበ ቢሆን ጥሩ ነው፡፡ በ ዓለም የሚኖረ ህዝብ አንድ ፈጣሪ ና አንድ አባት አንድ እናት ነው ያለው፡፡ የ ቃንቃ ልዩነት የ መጣዉ በ ሃጥያታችን ብዛት ነው፡ ይቅርታ ከተሳሳትኩ ወንድሜ መነስፍን፡፡

  10. Although your ignorance has bounds, wish to share with you and the likes of you the following itemized points….
    የኦሮሞ ሕዝብ ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄዎች ለድርድር እና ለልመና የሚቀርቡ አይደሉም።
    *****************************************************************************
    አንዳንድ ወዳጆቼ የኢትዮጵያ መንግሥት የኦሮሞ ሕዝብ እየጠየቀ ላለው:
    1ኛ፣ በጉልበት እና ሕግን ሽፋን በማድርግ የተዘረፈው የኦሮሞ ሕዝብ መሬት እንድመለስ፣ የወረራው መሠረት የሆኑት ሕጎች እንዲሻሩና የዘረፋ ተቐማቶቹ እንዲፈርሱ፣
    2ኛ፣ ኦሮምኛ ከአማርኛ ጎን ለጎን የኢትዮጽያ ፌድራል መንግስት የሥራ ቐንቐ እንዲሆን፣
    3ኛ፣ አድስ አበባ እንደ ሌሎቹ ትላልቅ የኦሮሚያ ዞኖች የዞን ደረጃ ተሰጥቷት፣ አማርኛ እና ኦሮምኛ የሥራ ቐንቐ ሆነው በኦሮሚያ ሥር እንድትተዳደር፣
    4ኛ፣ በግፉ ለተገደሉና ለታሰሩ የኦሮሞ ልጆች ካሳ ተከፉሎ ገዳዮችና አሳርዎች ለፉርድ እንድቀርቡ፣
    5ኛ፣ የኦሮሞ ሕዝብን ለ140 ዓመታት ከኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የለየው ሥረዓት ተሽሮ ፣ ሕዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፖሊሲ እንድወጣ፣
    6ኛ፣ የኦሮሞ ሕዝብ በክልል ደረጃ ከፌዴራል ተላላኪዎች እጅ ወጥቶ ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድርና በፌዴራል ደረጃ ኢትዮጵያን በድርሻው ልክ ተወክሎ እንድያስተዳድር፣

  11. Kinfu Asefa, Abebe Belew, Tekle Moresh, Girma Kassa and other Oromo haters:

    JAWAR is an embodiment of all Oromos. All Oromos are JAWAR. Despite your unrelenting venom and campaign against a courageous Oromo leader, Oromos stand by Jawar. So just go away suckers – The under belly of your hate propaganda is an expression of the wish to repeat your forefathers fascistic and genocidal acts towards the Oromo.

  12. ********* ሦስት ውሸቶች ተደምረው አንዲት ዕውነት አይወጣቸውም:: ********
    [የባላባቱ አጼ ኃይለ ሥላሴ]+[የወታደራዊው ደርግ]+[የሽፍታው ጉጅሌ]=በቃ!በቃ!በቃ!..ሕዝባዊ መንግስት.።

    ወቸገል ዜናዊ ከሞተም በኋላ፣ዛሬም ሐቁን አንነጋገርም ? ? ?ብታምኑ ባታምኑም ቀመር ጅቦች በፀብ ጊዜ ሰውነታቸውን በመንፋት አካለ-መጠናቸውን በሰባ አራት በመቶ ማሳደግ ይችላሉ።

    በቃ !!! ብለን በትግላችን የመረሩ ተግባሮችን መውሰድ ከጀመርንበት ጊዜ አንስቶ ዛሬም እዚያው ከመከራ ውስጥ አልወጣንምና ዝም ልንለው የማይገባ፤”የት ነበርክ?የት ነበርሽ?”ተብለን የምንጠየቅበት የትውልድና የሕዝብ ያደራ ግዴታ ተጭኖብናል። በኢትዮጵያዊነታችንም እነዚያ የጨለማው ግልምቢጥ-ዘመናት አልፈው ለጋራ ዕድገት አሁንስ ቀኑ ሊነጋልን ነው ስንል፤ይኼው ዛሬ አዘቅጡ ውስጥ ተጨማልቀን ያኛው መንግሥት ከዚህኛው ይሻላል እያልን ብናበላልጥም ጉጅሌዎቹ ፍቅራችንን በሰላማችን ጠቅልለው አንድነታችንን በዘር እና በጎሳ እየተበተቡ ተስፋችንን በቅጥር አባሎቻቸው አጨልመውብናል።በእኛ የወኔ-ቢስነት ጉጅሌን አምርረን በቃ!!! ስላላልን የኢትዮጵያውያንን የሰቆቃ ዘመን አራዝመንዋል።እናም ዘንድሮም የባንዳ ልጆች የጉጅሌ ቡድን አባላትን እየፈለፈሉ በኢትዮጵያዊነት ሥም ኢትዮጵያን ሊያፈራርሷት፤አንዴ በዘር፣ሌላ ጊዜ በጎጥ፣አልቻል ሲላቸው በሐይማኖት እያማካኙ በየሰኮንዷ በሥልጣንና በገንዘብ ምሁራንን እየደለሉ ባደባባይ ከውስጥና ከውጭ ይቆፍሯታል።ይህንን ሐቅ አይናችን እያየ እና አጠጋባችንም ሆነው ሲገድሉንም ሆነ ሲያስገድሉን በዝምታ እናያቸዋለን።
    ይልቁንም በወገኖቻችን ላይ ጣታችንን እየቀሰርን ጉድፍ ስንሰነጥር እነሆ እርስ-በርስ እ-ያ-ባ-ሉ ‘ን ሌላ የመከራ ዘመን ላይ አድርሰውናል።እነኚህ በይሉኝታ-ቢስነት ድሮም የምናውቃቸውና ፣< > ብለን ፊት ለፊት አምርረን ያልተናገርናቸው”ጉጂሌዎች” ዛሬ ዛሬማ ብለው ብለው በትዕቢት ተቆዝረውና በጊዜ ጥላ ስር ተደብቀው የ”ባለሽልንግ ፓርቲ”አባላት እንደቻይናዎቹ ርካሽ የልሳን ጠረባ-ቡድን አቋቁመው በነብስ-ወከፍ ሕሊናችንን ለመግደል በቡድን እየተጠረነፉ የትም ተበትነዋል።ስለእነዚህ ጉደኞች ሌላው እንዲናገርልን እኛም አፋችንን በጥቅም ጠርቅመንዋል፤በ”እኔ ላይ አልደረሱም” ብለን እንደበግ እያመነዠግን በየተራችን እስክንታረድ ድረስ አፋችንን ዘግተናል።
    እነዚያ ሃያ ሶስት ዓመታት ልሳነ-ቢስ ያደረጉን ከድምር የዘመናት ስቃይ በከፋ ማንነታችንን እና ነፃነታችንን እየገደሉ መሆኑ ግን ፍፁም አልታወቀንም።እንደውም በየዋህነት ውስጥ ተዘፍቀን፣”ወያኔዎች ሳያውቁ ነው፤ወይም ባንዳዎች ነገ ይሻሻላሉ አሊያም “ኢሃድጎችን”እስኪ ለሚመጣው ዓመት ብቻ “ለልማታቸው ሲባል”እንጠብቃቸው”፣ እየተባባልን፦በዶላርና በፓውንድ ባንኮች እራሳቸውን ሲያለሙ እኛ ግን በባዶ ተስፋ፦”የእኛ ልማት ነው እያልን፣ወደገብረ-ጺዮን ቤት የተዘረጋውን አስፋልትና እና የእነ ተስፋዝጊን የሆቴል ሕንጻ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰራለት ነው እያልን፤ስንት የኢትዮጵያውያንን አጥንትና ደም ገበርን? ? ? ባጠቃላይስ በስላም ሥም ስንት እና ስንት የጠፉ ነፍሶችን በግፍ-ደም የታሪክ ስልቻ ውስጥ ቋጠርን ? ? ?

    በተለይም በውስጡ ተላላነትን የፀነሰው ”””የዋህነት””’ህላዌን አሳጥቶ፤ከተንኮል ፍላጻ ከወጣ እና ተስፋን ጨልጦ ከጠጣ፣ሰብዓዊነትንም ያሟጥጣልና ወደሚጨበጥ— ተላላነት— ተቀይሮ ለባላንጣው አካል የሰይጣናዊነት ባህርይን ያላብሳል።ይህንንም የተሟጠጠ ሐቅ ወደተላላነት በተሸጋገሩ የዋሆች ለመገንዘብ ቀላል መስዋዕትነት ብቻ የሚያስከፍል ቢመስልም በህዝቦች አሃዝ እና የንቃተ-ህሊና ደረጃ ተመዝኖ አጋጣሚዎች ካልመጡ በስተቀር ለድሉ ውጤት መዳረስ ጥቂት ዓመታት ብቻ አይወስኑትም።በእነዚያ የባዶ-ተስፋ ዓመታት ነው አገራችን ኢትዮጵያ በዘመናት የሰቆቃ ኑሮ ውስጥ ሕዝቧ ዛሬም ድረስ የሚዳክረው።በእስከዛሬው ያለውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ታሪክ ጠንቅቀው የሚያውቁ ሁሉ፤ከድጡ ወደማጡ እየዘቀጠ(በቀዳማዊ ኃይለ-ሥላሴ የሥልጣን ዘመንም ሆነ በወታደራዊው የህብረተሰባዊነት መንግሥት አሊያም በባንዳዎች የጉጅሌው ዘረኛ ሥርዓት) በሦስቱም የመንግሥታት ስርዓት ዘመናት ሕዝቡ በየዋህነቱ ተረግጦ እና ብዙ መስዋዕትነት ከፍሎ —-የዋህነቱ በተላላነት ተቀይሮ—-ውድ የሆኑ ልጆቹን አጥቷል።እናም ሁለቱ መንግሥታት ማለትም የቀዳማዊ ኃይለ-ሥላሴ እና የወታደራዊው ደርግ የወጣት ትውልድ አሳጥተውን ከነተስፋቸው ሞተው ተቀብረዋል።የአሁኑ ይባስ ደግሞ ወደ ሞት ገደል እየተክለፈለፈ ሊወድቅ የተቃረበው የጎጠኛው ወታደራዊ አገዛዝ ሥርዓት ከታሪክም ሳይማር፤የነቁ አባላቱንም ተ-መ-ክ-ሮ ሳያደምጥ ከእነሱም መካከል ጥቂቶቹ ወደ ገደሎቹ ሳይወረወሩ”አጥፍተናል፣ዘርፈናል፣በድለናል፣ወደ ሕዝቡ ተመለሡ!!!የባሰ በደም አትጨማለቁ፣በግድያ ነብስ አትስረቁ፣ነገ ያሰቅላችኋል!”እያሉ ቢመክሯቸውም የማይነጋ መስሏቸው፦ዛሬም ጨለማን ተገን አድርገው፣ማጭበርበርን በብልጥነት ፤ መግደልን በጀግንነት፣ማረድን በደፋርነት፣መስቀልን በዳኝነት፣መዝረፍን በባለፀግነት እያጣጣሙ፤በኢትዮጵያ ሕዝብ መቀለዱን በአደባባይ ተያይዘውታል።ይህን ሐቅ የሚክድ ደግሞ ከራሱ ከጉጅሌው ቡድን አባላት በስተቀር ማንም አይኖርም።
    ቁም ነገሩ የገዳይ ቡድን ለመሆናቸው በዕምነት ክህደት ጉዳይ ይረጋገጥ ለማለት ሳይሆን፤የገዳይ ቡድን ስለሆኑ ምን እንደምናደርጋቸው በግል ተገንዝበን ተራችን ደርሶ ሳይገሉን በፊት ለመታገል ቆርጫለሁ ብሎ መወሰኑ ላይ ነው።ይህም በቀይ የደም-ሴል ተለይቶ የተሰመረ መስመር ከፍተኛ መስዋዕትነት ስለሚጠይቅ የታመቀን የሕዝብ አመፅ ይጠይቃል፤ለዚህም ደግሞ ባንዳዎች መቃብራቸውን እየቆፈሩ ነውና መቼነቱ የጊዜ ጉዳይ ነው።

    በመቼነቱ እነማን እንደሚሰቀሉ፣እነማንስ እንደሚረሸኑ፣ወይም ዕድሜ-ልክ እስር ቤት እንደሚቸነከሩ ማንም ዛሬ ሊወስን አይችልም፤እርግጠኛ መሆን የሚቻለው ግን፤እነዚያ ባደባባይ በግፍ የተደፉትም ሆኑ በድቅድቅ ጨለማ በድብቅ የተረሸኑት ውድ የኢትዮጵያን ልጆች ያለኮፒ የተፈጠሩ ናቸውና ወንጀሉን ለፈፀሙትም ሆነ ላስፈፀሙት መቀጣጫው እንዳለ ሆኖ የእነሱ ክቡር ሬሳቸው ከተቀበሩበት ተፈልጎ አደባባይ ይመጣና ፍትህ የሚያገኙበት ቀን እየተቃረበ መሆኑ የማንክደው ሐቅ ይሆናል።ገዳዮችም ሆኑ የሥርዓቱ አራማጆች የትም አገር ቢሄዱ ሥም ዝርዝራቸው በሕዝብ የተለቀመ በመሆኑ በሰሜን አሜሪካ ቢጀቦኑም ሆነ በኤሮፕ ወይም በአረብ አህጉራት የድብቅ ሕይወታቸውን ቢጀምሩ፦አሊያም ባማሩ ሕንጻዎቻቸው ውስጥ ዱካቸውን አጥፍተው ቢንደላቀቁም በመንጠቆ እየተለቀሙ ብርብራ እንዳሰከረው አሳ የሕዝብ ደም እያደፈቃቸውና ካሉበት እያቅበዘበዛቸው በሕዝብ ክንድ ሊደቆሱ ተጎትተው በግድ እየታነቁ ወደ መንጸፈ ደይን ተግዘው ቁልቁል ገደል ይወረወሯታል።
    ይህን የነገረ-ነብስ (ሎጂክ) ትንታኔ በምሳሌ አስደግፈን በግልፅ እንየው።
    ለግንዛቤ፦
    ከመሠረታዊው-ጉዳይ እንደምንረዳው እኛ የሰው ልጆች የምድርን ክብነት ለማወቅ በግድ ወደ ጨረቃ ሄደን ሳይሆን በሳይንሳዊ ስሌት እዚሁ ምድር ላይ ሆነን ማረጋገጥ ችለናል።እናም በጉጅሌው የባንዳዎች “መንግሥት ነኝ”ባይ ሥርዓት እንደምናየው የነገ ትውልድ ላይ የሚሸርበውን መሠሪነት ማወቅ ለተቸገሩ ሁሉ በነገረ-ነፍስ(በሎጂክ)የተረዳን “የዓይን ለዓይን መደነቋቀል” ትግል ካልሆነ በቀር”ይህ የአምባገነን ዘረኛ ሥርዓት ፍጹም አይገባውም”ተብሎ እና አምኜበት ሁሉም እንደችሎታው ይታገል ዘንድ “ባደባባይ የበኩሌን ቆርጬ”ተናግሬአለሁ።

    በውቅቱ ትግላችን ከወያኔ ጋር ብቻ ቢሆን ኖሮ ሰሚ አለንና አገር ጥለን አንወጣም ነበር፤ዳሩ ግን ከሰማንያ አምስት ፕርሰንት በላይ በወያኔ ማጭበርበር አብዛኛው ሕዝብ ተወናብዶ የጉጅሌውን ቡድን በሰላም እና ማረጋጋት ሥም ደግፎ አስር ፐርሰንቱ ምሁራን ደግሞ የባንዳ ልጆች ቡድንነቱን እያወቀ እኛን ሲገዘግዘን ዝምታን በመረጠበት ሁኔታ ቅራኔው ከጠላት ጋራ ብቻ አልነበረም።ከወዳጆቻችን ጋር ጭምር በደም ማፍሰስ ግጭት ሊፈጠር ይችል ነበር እና የዚያንም ጊዜ ቢፈጠር ለዘመናት የማይታረም የወንጀል ስህተት ያስፈፅመን ነበር።እናም እኛ ኢትዮጳውያን ሃያ ሶስት ዓመታት በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ሆነን በትንሽ አመፅ ለሰላም እጃችንን ዘረጋን፤ ምን አገኘን?ግድያ፤ በጠራራ ጸሐይ ባደባባይ እና በጭለማ በህቡዕ አሜን ብሎ ተራ-በተራ እንደበግ እያመነጀግን መታረድ ነው። “…እስኪ ን-ገ-ሩ-ና”ብሎ ባደባባይ በሰላም ሲሟገት ሰሚ ያጣውን ኢትዮጵያዊ ወጣት እነአንዱዓለም አራጌን ብቻ እናንሳና ፖለቲከኛ የሰላም ታጋዩ ብለው በግፍ አጎሩት።ይኼው እኛን በለሁለት ሰንጥቆ ማለትም:ለይቶላቸው ያመጹትን እና በሰላም ተደራድረን እንሞክር በሚሉ ከፈለንና ማጭበርበሩን አጧጧፈው።አንዳንድ ለሆዳቸው ያደሩትንም ኢትዮጵያውያን ምሁራንን በደረቱ ላይ እየለጠፈ በነሱ ልሳን አዋቂና የተማረ፣ የተመራመረ፣ አብራሪ፣ ፈላስፋ፣ ቀያሽ መሐንዲስ፣ ሲፈልገውም በሽማግሌነት አስታራቂ፣ ተደራዳሪ እያስመሰለ እና እያጭበረበረ ዓመታትን አስቆጠሯል።

    ትግሉም እያመረረ ተጉዞ የሰዎችን ሕይወት በመቅሰፍ ደመ-ከልብ ሲያደርግና ያገራችንን ሆዳም ምሁራን ህሊና በጥልቅ ሲያቆስል፣እነሱም በሙያቸው መለገም ጀምረው ለስደት እየተዳርጉ ተራበተራ በስደተኛነት”ዲያስፖራነት” ቀርተዋል።ከመካከላቸውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ነን ያሉ እና በአላማ የፀኑ ዛሬም በስደት ላይ ሆነው የዜግነት መለያ ቢለብሱም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ከተራ የገንዘብ መዋጮ ጀምሮ በሰላማዊ-ሰልፍም ባደባባይ ቆመው ይታገላሉ።በዚህ የጉጅሌዎች አረመኔያዊ ጭካኔና በሚታይ ሰቆቃ አገራችንን እየታመሰች መንፈሳዊ አባቶቻችንን እንኳ ሳይቀሩ ለስደት ዳርጓል። ከነዚህ የግድያ መሰሪነት ነው ሰላማዊ ንግግርን ይቀበላሉ ብሎ ለሃያ ሦስት ዓመታት በትዕግስት እና በ”ሰላማዊ መንገድ” ተብሎ ደህና ነገር መጠበቅንም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተስፋ አሞኝቶ ከትግል በማራቅ ወኔ-ቢስ አድርጎ ለመግዛት ያሰሉት።እናም ተሳክቶላቸው የኢትዮጵያውያንን ትግል የጀግናው ውድ የኢትዮጵያ ልጅ ታማኝ በየነ ትግል ብቻ አድርጎ ለማስቀረት ስንት የበሰሉትን ብርቅ የኢትዮጵያ ታጋይ ልጆች መንገዳችሁ ተሳስቷል፣ሰላማዊ አይደለም፣ወይም ጦርነት ናፋቂነት እና የመሳሰሉትን በራሱ ህሊና ራሱን አስሮ እንዲሸመቅቅ “ምን አገባኝ?”እንዲሉ አድርገዋቸዋል።ለምሳሌ :፳፭፼ ያህል ኢትዮጵያዊያን ከሚኖሩባት ዩናይትድ ኪንግደም ፲፮፼፰፻ በለንዶን እየኖሩ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የድጋፍ ጥሪ ወይም ለአንዲት ፓውንድ የሕዝብ ድምፅ የመሆን መዋጮ የሚንቀሳቀሱት በመቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ግለሰቦች ናቸው።ይህም በየትኛውም ዓይነት ስሌት ሆነ በተፈለገ ምክንያት ቢደገፍ ሕሊናን ያሸማቀቀ ተግባር መሆኑን እንገነዘባለን።እንደዚህ ለምን ሆነ ብለን ጥናት ብናደርግ ብዙ ምክንያቶችን ከመደርደር በስተቀር ቀላል እና ጥናት ቢደረግበት አስገራሚ ውጤት ላይ የምንደርስበት ዐቢይ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።በየትኛውም መንገድ ቢሰላ ግን ስለኢትዮጵያ ሐገሩ የማይቆረቆር ኢትዮጵያዊ የለምና ከጉጅሌው ያገዛዝ ሥርዓት ይልቅ የተሻሉ ብዙ መልካም ነገሮች ሊመጡ እንደሚችሉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይስማማል።መንገድ ሰራን ብለው ፪ ሚሊዮን ብር በሙስና ተመዘበሯል፤አሊያም ግድቡ በአፍሪቃ የሚወዳደረው የለም ብለው አፍሪቃውያንን ለችግር በሚዳርግና የግድቡ ባለቤት የሆንነው ኢትዮጵያውያን በጉዳዩ ዳተኞች ተደርገን ያለጨረታ ያውም መሠረታዊ ቅራኔ ካለን የጣሊያን መንግሥት ጋር በመዋዋል የማይነጥፍ ገንዘባችንን ማባከን፤ሲብስም ዕምነታችንን እና ነጻነታችንን ሊዳፈሩ በተፈቀደላቸው ቻይናውያን፣የአረብ አገሮች እና የሕንድ ወረርሽኞች የገበሬዎቻችንን ቤተሰብ እየበተኑ መሬታችንን ለ፺፱ ዓመታት ኮንትራት ሲሰጡ ይሁንታችንን በዝምታችን ፈቀድንላቸው፤ምን ተረፈን ገና ተከፍሎ የማያልቅ የትውልድ ዕዳ።

    ስለደርግም ሆነ ስለ ኃይለ ሥላሴ ሲነሳ “ዲሞክራሲ” የተባለችውን የዕውቀት መለኪያ ብቻ ለሕዝብ እንዲሰጡት ሳይሆን፣ ከሕዝብ ሰብዓዊ መብቶች ውስጥ አውጥተው እንዳይወስዱ ባደባባይ የተነገራቸው።ሆኖም ኃይለ ሥላሴ በቆመጥ፣ደርግ ደግሞ በጥመንጃ እንደከለከሉን አብዛኛዎቻችን በታሪክ እናውቀዋለን።አሁን ያለው አምባገነኑን የጉጅሌ ቡድን ግን የራሱን መስፈሪያ አምጥቶ ለሚወደው እና ለሚጠላው እያለያየ በፈለገው መንገድ በችርቻሮ እንደምፅዋት ያድላል።ከነዚህም መካከል ብዙ ያገኙት ኑርልን እያሉት ሲያጅቡት ጥቂት የደረሳቸው ደግሞ ይጨመርልን ብለው አንዳንዴም እያሙት ለጥቅማችው ይከራከራሉ።የተቀረነው አብዛኛዎቹ ሕዝብ ግን ማን ሰጪ አደረገው? በድምፅ ብልጫ መጠላቱን ባደባባይ ያረጋገጥንበት ሰነድ ያለ ሲሆን ዲሞክራሲ እና ነጻነት የየራሳችን ሰብዓዊ መብቶቻችን እንጂ አንጠይቅም ብለን የሰረቀንን በትግል ልናስመልስ በተለያዩ ስልቶች እየተወጋን ነው፤እናም በአገራችን ሆነን እንዳናስመልስ በሰላማዊ መንገድ እንደራደራለን በማለት የነበሩንን መሳሪያዎች ለቅሞ ጉጅሌው ለራሱ ብቻ መሳሪያ ይዞ ጀግና እኔ ብቻ ነኝ ቢልም ባዶውን ሆኖ እንዴት እንደሚብረከረክ ከድተውት ከቡድኑ ከወጡት የምሥክርነት አባሎቹ መረዳት ይቻላል።ዛሬም የመጨረሻውን የመቃብር ጉድጓድ በሚቆፍርበት የገደል አፋፍ ላይ ሆኖ ልክ እንደደርግ ምንም እንዳልተፈጠረ ባጀት ያፀድቃል፣ኮንስትራክሽን ይፈራረማል፣የልማት ቃለመጠይቆችን ያካሂዳል፣የተለያዩ ኮርሶችን በየአቅጣጫው መከፈቱን ያስተዋውቃል፤ዕውነቱ ግን የጉጅሌው ሥርዓት ቀብር መዳረሱ ነው።

    የጉጅሌው ቡድን አባላት ከበስተጀርባው ለባዕዳን የአማካሪዎች ጠረጴዛ በማዘጋጀት ሰይጣናዊ የተንኮል ምክራቸውን በኢትዮጵያ ሕዝብን ትግል ላይ በረዶ የሆነ መሰሪ በህዝብ መገናኛ ፕሮፖጋንዳ ያዘንቡበታል።እንዚህን በማስታወቂያ የተደገፉ የመርዝ ጥበብም እንደ እንጀራ እየጠቀለሉ ሕዝቡን ያጎርሱታል።በዚህም ምክንያት ቢያንስ በስደት ላይ ያለው ኢትዮጵያዊ እንኳ የመናገር ነጻነት እያለው እንደሌለው አድርገውት በስደት የስለላ ሰንሰለት ውስጥ መተብተባቸውን አሳምነውት በኢትዮጵያ ሥም የተከፈቱት የኤምባሲ ጽህፈት ቤቶች የራሱ እንዳልሆነ የባለቤትነት መብቱን አሳጥተውታል።

    የሚያሳዝነው በስደት ላይ ያለነው ኢትዮጵያውያን አለመረዳዳታችን ሳይሆን ቢያንስ ችግረኛውን የኢትዮጵያ ሕዝብ እኛ/እኔ ዕውነትን ለማሰማት እንርዳለሚሉት ተራ እገዛ ለማድረግ አለመፈለጋችን ነው።እነዶክተር ብርሃኑ ነጋም በግልፅ እንዳስቀመጡት ቀን ከሌሊት በሁሉም አቅጣጫ መታገል ይኖርብናል፤አለበለዚያ ለሶስተኛ ጊዜ የተከሰተው የአምባገነን ገዢ ሥርዓት ሥልጣነ-መንግሥት መጨረሻው ይራዘምና ሰቆቃችን ለትውልድ ይተላለፋል፤ምኞታችንም ላም አለኝ በሰማይ ሆኖ ይቀራል።

    በዚህም ምክንያት ነው ሳይረፍድባቸውና ሕዝብን ይቅርታ ብለው በጊዜ ልብ እንዲገዙ ከህሊናቸው ይታረቁ የምንለው።አለበለዚያ ቕዽም ከሞተ ሐብታም፥አሁን የተወለደ ድሃ እንደሚሻል የምናሳውቅበትን ጊዜ እናሳያቸዋለን፤ለምን ቢሉ በተስፋው ውስጥ የሚኖር በመሆኑ ማንነቱን እናረጋግጣለንና። “ምንም ባይኖረኝ፣ተስፋ አለኝ።”እንዳለው ባለተውኔቱ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ-መድህን ወዬሳ ወይም እንደ እነእስክንድር ነጋ የሰላም ትግልን ስልት ማጣጣም፤ የታጋሽነታቸው እና የየዋህነታቸው ድምር በተላላነት ካላስመደባቸው በስተቀር አሊያም ሌላ የሰቆቃ ዘመኖችን ካላስቆጠረባቸው በተስፋቸው ውስጥ የማያዩት ፍቅር ይወለድ ይሆናል።እኔ ግን ብያለሁ ሁለት የተዋሹ ሥርዓቶችን አይቻለሁና በዕድሜዬ ይህ በቅርጹ ሦስተኛ በይዘቱ ግን አዲስ ያልሆነው የጎጠኞች ወታደራዊ አገዛዝ የተለየ አይደለምና ከአምባገነኖች ታምራትን አልጠብቅም፤ከመንፈሳዊ ሕይወት እንጂ፦ለምን ቢባል ሦስት ውሸቶች ቢደመሩም እንኳ አንድ ዕውነት አይወጣቸውምና።

  13. መስፍን አደብ ግዛ እንጅ ጁዋርን ማምለክ ትችላለህ ሰዉ መስደብ ግን ጥሩ አይደለም:: ጁዋር የተወለደበት ቀን ጁዋርን ቅበ ቀብተህ ማምለክ መብትህ ነዉ አሁንም ክዚህ የተሻለ አይደለም::

  14. አሜሪካን ተቀምጣችሁ ቆንጆ መኪና ቆንጆ ቤት ውስጥ እየኖራችሁ

    የጠበበ የዘረኝነት አስተሳሰብ ያላችሁ የጃዋር ተከታዮች እባካችሁ እስኪ

    እንዳላችሁበት ፈረንጅ አገር አስቡ ፡፡

    መቼ ይሆን ከእንቅልፋችሁ የምትነቁት ?

    አሜሪካ መኖር ወይም አውሮፓ ውስጥ መኖር አእምሮ አስተሳሰብ ካልተቀየረ ብትሞቱ ይሻላል፡፡

  15. The Oromo quest for freedom from suppression, repression and exploitation is not a question of blood relations! You need not be a pure Oromo to oppose blatant violation of human rights. You need not be Oromo to oppose the governmnet when it targets a certain group (be it ethnic, religious or political affiliation) it sees as an enemy and a potential danger to its total control on the political, economic and miltary spheres, and unleashes wanton killings, mass imprisonment and torture.

    For the Oromo, the brutalization of the TPLF is not the first crimes perpetrated against them in the name of one Ethiopia. The current Oromo youth are the 4th generation of Oromos being harrassed and killed just for being oromo. They were not free from physical or psychological harrassment unless they deny their identity or hide it behind the veil of ethiopiawinett as you do now. The question is, Why is it impossible to keep one’s identity as Oromo (or somali, sidama, …) and be an Ethiopian by citizenship? To be a citizen of say Britain or Germany, you are not required to be british or german by blood. You have to pay allegiance to the democratic constitution of the respective country. You have to abide by the laws and regulations and respect the culture and norms of the country.

    Well, in Ethiopia, not only that democracy is absent (except in the names of the country and almost all political parties), but also a plural thinking and tolerance to the right to have a different opinion than the prevailing one. Intolerance to differing opinion comes not only from the ruling elite. It is pervasive even on the ethiopian social media.

    The Oromo do not believe on purity of blood. Had it not been so, they would have not developed and perfected the culture of “Guddifachaa”, “Moggaasaa”, and “Luba-baasa”. “Guddifachaa” is adopting a child with full right and duty of being a child to his parents; “Moggaasaa” is the integration of a non-Oromo family, clan or group and grafting onto the Oromo clan system following a thorough and solemn ritual and oath of allegiance to equality, fraternity and brotherhood; the integration is freely initiated by the non-oromo group. “Luba-baasa” is the integration of the adopted group into the Gada class system. That is how the Oromo became such a great homogeneous nation. The Oromo culture is based on freedom, equality and brotherhood long before the proponents of the french revolution marched under this motto.

    The quest of the Oromo for freedom is not a blind desire for secesion but a quest for respect for their unabridged right to be free from any political and cultural oppression, and the right to determine their own fate. If that right – a true cultural, economic and political autonomy in the form of true federation – can not be respected within the bounds of Ethiopian, they uphold the right to build an independent Oromia. As far as I know, that is the principle the OLF is promoting – enable the Oromo and Oromians (including non-oromos living the true spirit of ijoollee Oromia) to freely voice what type of government and association with other nations and peoples in Ethiopia they want to have, in a referendum free of any form of pressure from any group. That is the true spirit of democracy.

    In such Oromia, you won’t be harrassed for expressing your opinion, whether you are 100% or 0% Oromo. The principles of freedom, equality and fraternity will be the spirit of governance, a politics of grass-root democracy based on Gadaa culture. It may seem too ideal, but that is my dream for all those who would live in future Oromia, and if possible in the whole of Ethiopia.

    Until then I would say:
    “Give us the fortitude to endure the things that can not be changed, and the courage to change the things which should be changed, and the wisdom to know one from the other.” Oliver J. Hart

  16. Ato Kinfu, stop belittling Oromo cause. You need to stop having a finger in every pie/yergo zinb atihun. Mind your own business.Your writing is full of verbosity and hatred. You better tell your people to rise up against Wayane to save themselves. Walqayit is disappearing fast and being chunked off into Tigrean ownership in front of your eyes. Your people are becoming landless. Eventually, you are the most losers at the end of the day.You better stop writing nonsense about the Oromo. Second, stop cursing Jawar Mohammed.As a political activist, he has been doing a great job. Many people love him no matter what. There are millions of Jawars.
    Wether youn like it or not the Oromo people are a formidable political force in today’s Ethiopia. No one can kill our spirit for freedom

Comments are closed.

Share