የእስክንድር ነጋ መልዕክት ከቃሊቲ እስር ቤት – “ለህዝባዊ እምቢተኝነት ሁኔታዎች ተመቻችተዋል”

የእስክንድር ነጋ መልዕክት ከቃሊቲ እስር ቤት

በሰላማዊ ትግል ውስጥ ሁለት አብይት የትግል ስልቶች አሉ፡፡ አንደኛው ገለልተኛ የዴሞክራሲ ተቋማትና ህግጋት ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ የሚደረግ ህዝብን ያሳተፈ ምርጫ ነው፡፡ ምርጫ ሲባል ዝም ተብሎ ለማስመሰልና የአምባገነኖችን የስልጣን እድሜ ለማራዘሚያነት የሚደረገውን አይጨምርም፡፡ ምርጫ ሲባል ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ያሉት ነው፤ መመዘኛዎችን ባሟላ መልኩ የሚደረግ ምርጫ፣ ምርጫ ሊባል ይችላል፡፡

አምባገነን ስርዓቶች ምርጫ ሲያደርጉ አስተውለናል፤ ግን የይስሙላ ነው፡፡ ግብጽ በሙባረክ ጊዜ ምርጫ ታደርግ ነበር፡፡ ብዙ አምባገነኖች ምርጫ አደረግን ይላሉ፡፡ ኢህአዴግም ምርጫ አደረግሁ ይላል፡፡ በእነዚህ ስርዓቶች የተደረጉት ምርጫዎች ግን ዴሞክራሲያዊ ሆነው አላየናቸውም፡፡ በዚህ ምክንያት ምርጫን እንደ ሰላማዊ የትግል ስልት አማራጭ አድርገው ይመለከቱ የነበሩ ዴሞክራሲያዊ ኃይላት ፊታቸውን ወደ ሌላኛው ስልት እንዲያዞሩ ይገደዳሉ፤ እሱም ህዝባዊ እምቢተኝነት ነው፡፡ በግብጽ የሆነው ይኸው ነው፡፡

አንድ ነገር ማስተዋል አለብን…የምርጫ ስልት ተዘጋ ማለት ሰላማዊ ትግል አበቃለት ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንስ ወደሌላኛው ምዕራፍ ተሸጋገረ ማለት እንጂ፡፡ ምርጫ ሲያበቃለት ህዝባዊ እምቢተኝነት አማራጭ ይሆናል፡፡ አሁን በኢትዮጵያ ሁኔታዎች ለህዝባዊ እምቢተኝነት ተመቻችተዋል፡፡ አሁን ህዝቡ በምርጫ ላይ ያለውን አሰራር አስረጅ ሳያስፈልገው ራሱ አይቶታል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በኋላ አማራጩ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንደሆነ መገንዘብ ግድ ይለናል፡፡ ህዝባዊ እምቢተኝነት ህጋዊና ሰላማዊ የትግል ስልት መሆኑን ዓለም ይገነዘባል፡፡

በዚህ ወቅት ስለህዝባዊ እምቢተኝነት የሚሰሩ አካላት ካሉ መንገዳቸው ልክ ነው፤ ሊገፉበትም የሚገባ ነው፡፡ በእርግጥ ህዝባዊ እምቢተኝነት ላይ በቅድሚያ መግባባት ላይ መድረስ ያለባቸው አካላት አሉ፣ ዋነኛዎቹ ‹አክቲቪስቶች› ናቸው፡፡ አክቲቪስቶች መግባባት ላይ ደርሰው ህዝቡን የማነቃነቅ ስራቸውን በጋራ ቢያከናውኑ አንድነቱን ያጠናከረ እንቅስቃሴ መተግበር ይቻላል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሥውሩ (ገጽ አልባው) ሕወሐት - ኢኑሻ አየለ

እስካሁን በተገለጸው የ2007 ‹‹ሀገራዊ ምርጫ›› (በትምህርተ ጥቅስ አስገባልኝ) ውጤት እጅግ ደስተኛ ነኝ፡፡ አዎ፣ የተለያየ ፍላጎትና ጥቅም ያላቸው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ተስማምተው አንድ ፓርቲ መረጡ ቢባል ለሰሚውም ቀልድ ነው፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ያልሆነ ውጤት ነው፡፡ ይህ የሚያሳየው ኢህአዴግ ለማጭበርበር እንኳ አቅም እንዳጠረው ነው፡፡ ለዚህም ነው በውጤቱ ደስ የተሰኘሁት፡፡ ውጤቱ በግልጽ የሚነግረን ከዚህ በኋላ ለሚመጣው ህዝባዊ እምቢተኝነት ዋናው ገፊ ምክንያት ኢህአዴግና የኢህአዴግ ስርዓት መሆኑን ነው፡፡ እናም ህዝባዊ እምቢተኝነት በኢትዮጵያ ‹ጀስቲፋይድ› ነው፡፡

በእርግጥም አሁን ያለው የኢህአዴግ ስርዓት ለራሳቸው ለኢህአዴግ አባላት እንኳ አሳፋሪ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ የማስመሰል ካባው እንኳ አላስፈለገውም፤ ሁሉንም ነገር ከርችሞታል፡፡ እናም ቀጣዩ ትግል የነጻነት ትግል ነው፡፡ ይህን የነጻነት ትግል ዳር የሚያደርሰው ማሳረጊያ ደግሞ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ህዝባዊ እምቢተኝነት ኢህአዴግ ራሱ መርጦ ለህዝቡ የተወው እንደሆነ መረዳት አለብን፡፡ የታፈነ ህዝብ ሲነሳ ማዕበል ነው፣ አምባገነኖችን ይጠራርጋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አፈና ህዝባዊ እምቢተኝነት አይቀሬነቱን በግላጭ ያረጋግጣል፡፡

2 Comments

  1. Even Eskinder has full democracy right to write what he wants to deliver to his power monger group. Most of you bark as dogs and visit Europe & American embassies to force EPRDF to resign and hand over the political power to old and outdated northern ethnics as if your are the only concerned people to the whole nation otherwise our country will be erased from the world map or the so called Ethiopia will be vanished from the earth. By this type of fooling people, your ethnic ruled by force and made our country the most backward country and the poorest one due to your ignorance politically unable to organize the whole nation and nationality to best and rational different political group that represents their view but on the contrary you were forcing people to adopt your culture and language . This type of force made our country to exercise armed struggle to over through the political burden and Finley came to success to form self ruled federal states. The new federal state prevent the democratic right of the people from the outdated shouvinist power mongers those who plans to creat civil war . We know Eskinder who he was during Derg. If he was after democracy he would have struggled agains the fascist Derg but he was one of the fascist who planed how to eradicate EPRP. Unless you lined your self to the right political line , you may loose your life when you observe people are after the genuine political parties and your agitation against the right politics is nothing.

  2. All what you extremist shoa-ians are doing is, just barking, ranting and venting ruthlessly.
    And this is what one, fair minded man can expect for you guys to do, given that you are remnants of the buried and crushed dergue regime.

    Anyways, RIP!

Comments are closed.

Share