ኦህዴድና ስሙን የቀየረው ኢህዴን – ሰይፈ ምካኤል

ኦሮሚያን የሚመራው ዛሬ በርካታ ለውጦችን አስመዝግቦአል ይህን ስል ህወሀት ከፈጠራቸው ድርጅቶች ሀቁ “ከዝንጀሮ ቆንጆ. . . “ የሚባለው እንደተጠበቀ መሆኑ ይታወቅልኝ ማለትም ሁሉም ገዳዮች ዘራፊዎችና የኢትዮጵያ ጠላቶች መሆናቸውን ዘንግቼው አይደለም።

_የአማርኛ መጠሪያ የነበራቸውን የቦታ ስሞች ወደ ኦሮምኛ ለውጥቶታል

_በከፊል በኦሮሞ ታሪክ ጎልተው በሚታዩ ጉዳዮች ደግሞ የፈጠራ ተረት ላይ ተመርኩዞ የት/ት ስራት ያካሂዳል

_የክልሉ ሕዝብ 88% ብቻ ኦሮሞ ሆኖ ሳለ በክልሉ ሕገ-መንግስት ቕንቕን በተመለከተ ኦሮምኛ ግዛትን አስመልክቶ ደግሞ ክልሉ ውስጥ ያሉ ሌሎች

ብሔረሰቦች ራሳቸውን በቕንቕቸው እንዳይማሩና የመገንጠል መብት እንዳ ይኖራቸው ድንጋጌ አውጥቶአል

_የኦሮሞ ክልል ስፋት ወደፊት በሂደት ከሌሎች ክልሎች ወደ ኦሮሚያ የሚካተቱ መሬቶችን ያካትታል ይላል

_በርካታ አስፋልት የተላበሱ መንገዶች ወያኔን አግባብቶ አስገንብቶአል እያስገነባም ይግኛል

_ሁለት የግልገል ጊቤ ሀይል ማመንጫዎች የዲዴሳ ግድብና ሀይል ማመንጫ የናዝሬት ሁለት የንፋስ ሀይል ማአመንጫዎች እውን አስደርጎአል ሌላም አሁን በኢሉባቦር ግንባታው እንዲጀመር የተሳካ ስራ ስርቶአል

_ክሰበታ እስክ ጅቡቲ የሚዘልቀውም የባቡር መስመርና ወደ ናዝሬት የሚወ ስደው ፈጣን መንገድ የኦሕዴድ ስኬቶች ናቸው

_አማራውን አባሮና አማራውን የሚያጥላሉ ሐውልቶችን ገንብቶ ክልሉን የአንድ ጎሳ መኖሪያ እያደረገ ይገኛል

_በርካታ ፋብሪካዎች እንዲቕቕሙ በማድረግ ላይ ይገኛል

_ሕዝቡ የኦሮሞ አቕሙ እንዲዳብር አድርጛል ታሪካዊ ባሕላዊ በአሎች እንዲከበሩ ስርቶአል ወጣቶች በአ አ መስፋፋት ያሳዩትን ተቃውሞ መጠቆም ለዚህ ምስክር ነው ወዘተ. ኢሕዴንስ ምን እያደረገ ይገኛል?

_የቦታ ስሞችን ታሪክን አመሳክሮ ለውጥ አላደረገም

_92% አማራ ሆኖ ሳለ በክልሉ ያሉ ጎሳዎች እስከመገንጠል የሚደርስ መብት በክልሉ ሕገ-መንግስት እንዲካተት አድርጛል

ተጨማሪ ያንብቡ:  እኛ በኛ እንኩራ

_የክልሉን ግዛት በየአጋጣሚው ለትግራይ አሳልፎ መስጠትንና አማራውን አናሳ የማድረግ ስራ ይሰራል

_አማራውን ትምክህተኛ ነፍጠኛ የጨቕኞች ተከታይ መዝባሪ ወዘተ የሚሉ ስድቦችን ለጥፎበት በታሪኩ እንዳይኮራ እያንቕሸሸው አንገቱን ደፍቶና ተጎሳቅሎ ኑሮውን በመከራ እንዲገፋ አላማ ነድፎ ይሰራል

_በሌሎች ክልሎች የማይተገበር ኢህዴን በአማራ ክልል ከየትኛውም ቦታ የመጣና በክልሉ 2አመት ብቻ የኖረ ልከ እንደ ክልሉ ተወላጅ ተቆጥሮ አርሶ ሸቅሎ ወዘተ መብቱን አስከብሮ መኖር እንዲችል ደንብ ደንግጎአል በዚህም መሰረት ከ60ሺህ በላይ ትግሬዎች በአርማጭሆና መተማ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸው ዛሬ አካባቢው አገራችን ስለሆነ ከትግራይ መቀላቀል አለበት ብለው መሳሪያ አንስተው ያካባቢውን ተወላጅ አማራ ማፈናቀልና በይፋ የይገባኛል ጥያቄ አቅርበዋል።

_አማራው ግን ለበርካታ ዘመኖች ከኖረባቸው አሩሲ ሀረርጌ ጅማ ጅጅጋ ወለጋ ጋምቤላ ጉራፈርዳ ቀማሺ መተከል አምቦ ወዘተ መጤ ተብሎ ተጨፍጭፎና ቀሪው ደግሞ ሲባረር ኢህዴን አማራውን “አላገሩ ማን ሄደህ ኑር አለው የሰው አገር ለቆ መውጣት አለበት” በሚል ነበር ለጉዳዩ ምላሽ የሰጠው።

_አማራው የምናለብኝና የምናገባኝ ባህል በማዳበር ራሱን የመከላከል አቅሙን በመስለብ ፈሪና ምንቸገረኝ ባይነት እንዲያጠቃው ኢህዴን ለህወሀት ቀኝ እጅ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል ለምሳሌ በረከት ስሞኦን ባንድ ወቅት “አማራው ሁን ያልነውን ይሆናል አድርግ ያልነውን ያደርጋል” ማለቱ ትዝ ይለኛል

_በት/ት ወጣቶች ታሪካቸውን እንዲጠሉና ወያኔን እንዲያመልኩ በማንነታቸው የሚያኮራ አቕም እንዳይኖራቸው ማድረጉን መመሪያው አድርጛል ስለዚህም ክልላቸው ሲበጣጠስም ሆነ ታሪካቸው ሲቆሽሽ በማንነታቸው ላይ የተከፈተባቸውን ጦርነት መቕቕም ያለመቻልና ደካማ ንቃት እንዲኖራቸው የኢሕዴን ካድሬዎች አልመው ይንቀሳቀሳሉ

_በዚህ ረገድ የአማራነት አመለካከት በክልሉ ውስጥ በምንም አይነት ባለፉት 23አመቶች እንዳይኖርና ጎጃሜው ባካባቢው ሌላውም እንደዚሁ ጎጃሚያዊና አካባቢያዊ ውሱን ንቃት ብቻ እንዲያንጸባርቅ ያለመ ስራ በካድሬዎቹ እውን በማድረግ ለህወሀት ጥቅም ከፍተኛ አስተዋጾ ኢህዴንድበት አበርክትዋል

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይቅርታ የማስጠየቅ ሱስ - ይሄይስ አእምሮ

_ዛሬ ዘርፈ ብዙ ስር ነቀል የግዛት ለውጦች በሚካሄድበትና እየጠፋ ባለው የአማራ ክልል ህወሀት ጉዞው የሰመረለት ስለ ጎንደር መበጣጠስ የአማራ ውድመት ነው ብሎ በቁጭት የሚነሳ ጎጃሜ ወሎዬ ሸዌ በመጥፋቱ ነው። ከዚህ ሁሉ የሚያሳዝነው ጎንደሬዎች ራሳቸው አለፋ ሲጎመድ ቕራ ተቆርጦ ለሱዳን ሲሰጥ ሁመራን የመሰለ የሰሊጥ ሀብታም ቦታና ወልቃይትን ህወሀት ሲወስድ ዝም ማለቱና “በቡሀ ላይ ቆሮቆር” እንዲሉ ዛሬ ልቡ ያበጠውና ጎንደርን የመቆራረጥ ህልሙ የበረታው የትግራይ ታጣቂ የአርማጭሆንና የመተማን ወዘተ ወረዳዎች ሲጠቀልል እጃቸውን አጣጥፈው የመቀመጣቸው ጉዳይ ሲሆን ምን እስኪሆኑ እንደሚጠብቁ ለተመልካችም ግር የሚል ጉዳይ ሆኑዋል።

_ክልሉ ጭቃና አቧራ ለብሶ ከድህነት ማቅ እንዳይወጣ ኢሕዴኖች የወያኔን አላማ ግቡ ለማድረስ ሌት ተቀን በባንዳነት በቁርጠኝነት በመስራት ላይ ይገኛሉ

_ተስፋ የሌለው ክልል እንዲሆን በጎጥ በቀበሌ በከተማ በወረዳ በዞንና በክልል ካቢኔ ቢሮዎች የህወሀት ካድሬዎች ተሰግስገውበታል እንደዚህ አይነት አሰራር የሚተገበረው በአማራ ብቻ ነው በሌሎች ከልሎች ትግሬዎች ያሉት በደህንነትና ፕሮፓጋንዳ ላይ ብቻ ነው

_ድርጅቱ በትኩረት የሚያለማው ከጎጃም ተቆርሶ አዊ በተባለው ዞን ላይ ሲሆን አማራው ከጣና በለስ የስኻር ልማት ተጠቃሚ እንዳይሆን ከአለፋ ጣቁሳ መሬት ተቆርሶና አማራዎች ተፈናቅለው ጃዊ በሚል አዲስ ወረዳ ለአዊ ተሸልሞአል ይህ ደግሞ ህወሀት አማራውን ቅስሙን ለመስበር ካለው አላማ ጋር የሚጣጣም የኢህዴን ዋነኛ የስራ አካል ነው

_ከግንቦት2007 ምርጫ ተከትሎ ወይም ከምርጫው አስቀድሞ ጠገዴ ጠለምት ሰሮቃ አብደራፊ መተማ አለውሀ አዲአርቃይ በይፋ ወደ ትግራይ እንዲቃለሉ በፌደራል ጉኡዳዮች በክልሉና በህወሀት መካከል የፊርማ ስነ-ስራት እውን ይሆናል

ተጨማሪ ያንብቡ:   አዲስ አበባ ወይስ አዲስ አባባ? - ኤፍሬም ማዴቦ

_በመቀጠልም ቕራን ወደ ቤኒሻንጉል በማዛወር አማራ ከሱዳን ጋር የነበረውን ጥንታዊ ድንበር ይቀማል ትግራይና የአባይ ግድብ ድንበርተኞች ይሆናሉ በመጨረሻም ህወሀት አማራውን በጣጥሶ ለማጥፋት ያለውን አላማ በአገልጋዩ የቀድሞው ኢህዴን ያሁኑ የአማራ ባለሙሉ ስልጣን ገዢ እውን ያደርጋል “አዲዮስ አማራ”

_የአማራ ምሁራን በሙሉ በተጨማሪም ራሳችሁን ጎጃሜ ወሎዬ ወዘተ እያላችሁ የምትጠሩ ጠባቦች የአማራውን ሕዝብ ለዚህ አሳዛኝ የታሪክ ጥፋትና ስተት አልተባበር ብላችህ ስላበቃችሁት ተጠያቂው ህወሀት ሳይሆን ራሳችሁ በመሆናችሁ ሀፍረታችሁን በቁማችሁ ዋጡት።

_ኢህዴን የሚለውን መጠሪያ የተጠቀምኩት ድርጅቱ ክልሉን እንዲያስተዳድር በህወህት ገጸ በረከት ሲሰጠው የተላበሰውን ስም ስላልተቀበልኩት መሆኑን አሳውቃለሁ።  ታዛቢ ነኝ የካቲት 2/2007 !!!

 

5 Comments

  1. Waw@moresh wegene got answer for you.do you mind,if you think moresh is the answer .www.moresh information center.and we know.ya ahiya balli kegib ayasitilim..do not worry about amhara,bla bla…we all know just go to moresh wegene.info.amhara is ticking bomb.

  2. …. ሥምን ማን ያወጠዋል? ሻእቢያህወአት/ ማገብት/ ወያኔ/ ተሓህት/ ኢህአዴግ … ድረጅት..ግንባር..ንቅናቄ.. እያለ ይዘልቃል…በዚያውም ላይ ተለጣፊ አጋር ሲል በቅርፅና መጠን ለየት ያሉ ኮንግረስ፣ ፌደራል፣ዴሞክራሲ ሰል በአራት ማዕዘን..በቋንቋ በግንባር ላይ ጠባሳ..በቅንድብ ላይ ጭረት፣ በአፍንጫና በከነፈር መጠን፣በቀለም ድምቀትና ጠይምነት፣ በአመጋገብና በክልላዊ አለባበስ በዜማና በጭፋሮው እያቧደነ በሩቅ የመለያ የመጠበቂያ የማንነቱን ልዩነቱን ለማጉላት አንድነቱን ለመስለብ አስችሎታል…
    ***በእርግጥ የራስን ሥልጣንና ሀብት ለማስከበር ሌላውም ውስን ፍርፋሪን ተጥሎለት ፊቱን እንዲያዞር በህወአት እና በኦህዴድ መካከል ሠርቷል ግን ከንባታና ጋምቤላ ጉራጌ ላይ ግን አልሠራም… አናሳ ድሮ የማይታወቁ በህወአት የተፈጠሩ በእኛ ለእኛ የምትኖሩ ያለእኛ መኖር የማትችሉ የምትጠፉ ብሔር ብሄረሰብ ተብለው ተፈርጅዋላ …”ልማት ስለሌለ ልጆቻችን ተሰደዋል!’ ብለው ሰላማዊ ሰልፍ ባልወጡ ነበር… አብዛኛው የእነኝህ ክልል ዜጎች የአውሬ እራት የአዞ ቀለብ ሆነው በዱር በገደሉ ጠፍተው በሰው ሀገር እንገታቸው በሜንጫ ባልተቀላ ባልተደበደቡና ባልተደፈሩ! —- ትኮስ ድንች ቀልድ እዚህ ትግባ… ” አለቆቻችሁ የሰጧችሁ ትዕዛዝ ሲፈጃችሁ እኛ ላይ ጣላችሁት እኛ የት እናድርሰው? ተቃጠልን! አለ….”እዚያ ገንዘብ ገኘ እዚያ ለማ እዚህ ምን አለ? ይህ ‘ተከልለውና ተከልክለው’ ለጭፈራ ብቻ የሚጠሩትን እስታዲየም ብቻ የሚገነባላቸውን ካድሬ የሚያሽቆጠቁጣቸውን በክልልህና በቋንቋህ ብቻ ተናገር ተብለው የቁም እሥር የተፈረደባቸውን የዋህ ሕዝቦች ይመለከታል…
    *** እዚህ ላይ ኦህዴድ ስኬታማነቱ ከላይ እንደተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ አንዳንድ ግዜ የአዞ ዕንባ እያነባ የቁራ ጩኽት ማሰማቱ “መከላከያውና ፖለቲካል ኢኮኖሚውን መቆታጠር ብቻ ቀረኝ” ሲል ሜንጫ ይሰበቅ ሲል ..በሌላ በኩል “እኛ ወደእናንተ እንጂ እንመጣለን ቋንቋም ባሕላችሁም እኛን ስለማይመስል ወደእኛ አትስፋፉ ይልና በሌላ በኩል ምንም ዕድገት አልተደረገልኝም ከፌደራል ጥቅማጥቅም ታጋኛለህ ተብዬ ተስፋ ተደርጎልኝ ቀረብኝ ሲል ሕዝቡን ማደናቆር ጭራሽም የበሬ ግንባር ቦታ ይዞ ከመጨፈር ውጭ የሌላውን ዜጋ ማንነት አክብሮ መኖሩን የዘነጋው ይመስላል.. በሕዝብ ቁጥር ብዛት ብቻ ዜግንት ልዩ በረከት የሚያወርድ አድርጎ ከሌላው ብሀየር የተጋባውንና ተዋለደውን ሁሉ የሚያራክስ ብሄርና ሃይማኖትን የሚያጭበረብርና የሚያጥበረብር የብዝሃነትን አፍራሽ ፕሮፓጋናዳ በትውልድ ማስረፅ ‘እራስን በራስ ማስተዳዳር’ ‘የሰፈርክበትና የያዝከው ሁሉ ያንተ ብቻ’ ነው የተምታታ ግንዛቤ እንዲኖር ብዙም ባይሆኑ ጥቂት የማይባሉ ፅንፈኛ ጠባብ አመለካካቶች ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትን አለዚያም ተመፅዋች ባለህበት ሂድ ለትውልድ ማውርስ ይሆናል ። ምንም እንኳ ፈጣን ቀለበታማ አሳላጭ የጥቂቶች መክበሪያ ዕድገት ቢኖርም ካለፈው ሃምሳ ዓመት ጉታች አማለካከት ዓለም የደረሰበትን የተሻለ በጋራ ሠርቶ ለማደግ ብሩህ ትውልድ ካልተፈጠረ እንደድህነት ድንቁርናና ኋላቀርነት መለያችን ሆነው ይቀጥላሉ።
    *** ሌላው ኢህዴን(ኢትዮጵያ ሕዝብ ደሞክራሲ ንቅናቄ) ከኢትዮጵያ ይልቅ(በአመለካካት)የአማራ ብሄርን አፋኝና ተቆጣጣሪ በእሻቢያህወአት ተጠፍጥፎ የተሠራው ብአዴን ..በክልሉ ቢራ ፋብሪካና እግርኳስ አስታዲየም በመገንባት ወያናይት! ሲል እራሱን ይሸጣል።በእርገጥ ጎንደሬ ከሸዋ ከሚጋባ ከትግሬ ቢጋባ ይመርጣል ሲባል ፈንድቆ ነበር.. ወሎ ግን የሸዋና የጎንደር ንጉሶች ሰለባ ነበር ሲባል ሲፈነጥዝ ኦሮሞ ነበርክ ሲሉት ሲያጉረጠርጥ ሲያለቅስ…ሸዋ መሪዎችህ ጨፍጫፊች ወሎን ያስረቡ፣ ትግሬን የበደሉ፣ ኤርትራን ያስገነጠሉ፣ ሲሉት ትናንትን ዛሬም በባዶ እግሩ በባዶ ሆዱ ለሀገር እንድነት አጥንትና ደሙን መስዕዋት ከፍሎ ለፊውዳሉ በጭሰኝነት ሲረገጥ ለዛሬው ባለሀብት ካድሬ የበይ ተመልካች ሆኖ ሶስትኛው ትውልድም ላይ ሲሰደብ፣ ሲበደል፣ሲገለል፣ አሁንም የልሃጭ ማራገፊያ ሆኗል።ለወያኔ ሥልጣን መያዝ መንገድ መርቻለሁ ሥንቅ አቀብያለሁ በወሎም በሸዋና ጎንደር እውቅና አልነበረኝም የሚለው ጎጃም እውቅና አግኝቶ በመጨፈር ከአባይ ዳር በዘፈን አንደኛ ሆኗል አማራን መሳደብ የሚፈልጉ ብአዴን ካድሬ መድርክ የሚሰጣቸው እዚያ ነው።”ከጎጃም ተቆርሶ አዊ በተባለው ዞን ላይ ሲሆን አማራው ከጣና በለስ የስኳር ልማት ተጠቃሚ እንዳይሆን ከአለፋ ጣቁሳ መሬት ተቆርሶና አማራዎች ተፈናቅለው ጃዊ በሚል አዲስ ወረዳ ለአዊ ተሸልሞአል”
    – ለመሆኑ ዓማራው የለም! ተባለ ብለው በተረትና ምሳሌ የተቀናጡብን አማራሪዎች የት አሉ ት ነበሩ? “የዚህ ፅሑፍ እውነታ _” የአማራ ምሁራን በሙሉ በተጨማሪም ራሳችሁን ጎጃሜ ወሎዬ ወዘተ እያላችሁ የምትጠሩ ጠባቦች የአማራውን ሕዝብ ለዚህ አሳዛኝ የታሪክ ጥፋትና ስተት አልተባበር ብላችሁ ስላበቃችሁት ተጠያቂው ህወሀት ሳይሆን ራሳችሁ በመሆናችሁ ሀፍረታችሁን በቁማችሁ ዋጡት። ” ነገረው በለው! ።ከምስጋና ጋር!!!!!!

    • እንክርቶ ምነው ስለዘመዶችክ በለው ከለው አተርክልንም? ዝምብለህ ማጠልሸትን ማድመቅ ስትችልበት! አማራው ባክ በ ጫንቃው ላይ ሆነው ያጎበጡትን ትብያዎች አራግፉዋል! በ ኢትዮጵያ ስም ጭንቅላታችን ላይ ጉብ ብለው እንደ አልቂት ሲመጡን እና ሲያስመጥጡን የነበሩ ኢትዮጵያዊ የሚል ስም ለራሳቸው ለጥፈው አማራውን አጥንት ሲግጡ የነበሩ ላይመለሱ በ ብሄር ብሄረሰብ መብት ስም ከተደበቁበት መንጥረን እንደ ቆሻሻ ጠርገናችዋል! ወያኔን ለ ኛ ተወው! እነሱን በ ሆዳቸው አስረናችዋል! እምለው ከገባክ ነው! ጽዋው ሲደርስ እንደ አህያ ቢጋለቡ እና ቢቀጠቀጡ የትም አይሄዱም ደግሞም ወድያውም አይከሱብንም! መላው ያለው ከ እኛው ነው! እማታቀውን ነገር አትዘባርቅ! መሃይም!

      • አዎን፡ ልደቱ አያሌው ወሎን ማስተዳዳር ሲጀምር ሁሉ ነገር ይሆናል አተላ ልፋጫም የድሃ ልጅ!
        (፩)”አማራው ባክ በ ጫንቃው ላይ ሆነው ያጎበጡትን ትብያዎች አራግፉዋል!”
        **ከዚያማ ብአዴን ከኤርትራ ከከንባታ ከከፋ ጠፍጥፋችሁ ሥርታችሁ ቂጥህን ሲያስመነጥርህ እያየን ነው።
        ፪) “ወያኔን ለ ኛ ተወው! እነሱን በ ሆዳቸው አስረናችዋል!
        ***ወያኔ በላን ጋጠን እያልሽ ሁልሽም ቂጢሽናን አፍሽን ትከፍቻለሽ.. ወሎን እንደሁ አስረክባችሁ ታጨበችባላችሁ!
        ፫)ጽዋው ሲደርስ እንደ አህያ ቢጋለቡ እና ቢቀጠቀጡ የትም አይሄዱም ደግሞም ወድያውም አይከሱብንም! -** ፳፫ ዓመት ምን አተረፋችሁ?ጭነው ይጋልቧችሁ የለምን? ወይስ በብሄር ብሄረሰብ ሂሳብ ስለሚገዟችሁ ፈንድቃችሁ ማንነታችሁ የጠፋችሁ ‘የእኛ ለእኛ በእኛ’ ተስማምቷችሁ ከከተማ ከተማ በመኪና እየጫኑ ቢራ እየጠጡ ሲያላግጡባችሁ እናንተ ደጅ አስታዲየም እነሱ ወፈር እንዱስትሪ እንሱ ቤት ነች ጤፍ እናንተ ወፈር ጫት ስለበዛ አላህ እያላችሁ! ድቤ ትመታላችሁ? ደደቢት በረሃ ድረስ በሰልፍ ሄዳችሁ ታለቅሳላችሁ! ታየ ጉዳችሁ…ይልቅ ወያኔን አክብራችሁና ወዳችሁ ኑሩ! ቃሊቻ!

Comments are closed.

Share