በፊፋ የሃገራት የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ አራት ደረጃዎች ዝቅ አለች

በፊፋ ወርሀዊ የሃገራት የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ አራት ደረጃዎች ዝቅ ማለቷን የፊፋ ድረ ገጽ አስታወቀ። ብሄራዊ ቡድናችን በደቡብ አፍሪካው አፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎው ያስመዘገበው ደካማ ውጤት ለደረጃው መውረድ የፊፋ ድረ ገጽ እንደምክንያትነት አቅርቧል።
በውድድሩ ላይ ካደረጋቸው ሶስት ጨዋታወች በሁለቱ ተሸንፎ፣ 7 ጎል ገብቶበት አንዱን አቻ ከወጣና 1 ጎል በውድድሩ ካገባ በኋላ የየካቲት ወር ደረጃው ቀድሞ ከነበረነት 110ኛ ወደ 114ኛ አሽቆልቁሏል።
በአፍሪካ ዋንጫው ሳትጠበቅ ለፍፃሜ የደረሰችው ቡርኪናፋሶ 37 ደረጃዎችን ስታሻሽል የአፍሪካ ሻምፒዮኗ ናይጄሪያ ባለፈው ወር ከነበረችበት 52ኛ ደረጃ ወደ 30 ተቀምጣለች።
የአፍሪካን ደረጃ የሚመሩት እንደየቅደም ተከተላቸው ከአለም 12 እና 19ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ኮትዲቯርና ጋና መሆናቸውን ያስቀመጠው የፊፋ ሰንጠረዥ የፊፋን ወርሀዊ የደረጃ ሰንጠረዥ ስፔን ፣ ጀርመንና አርጀንቲና ከፊት ሲመሩ ፥ እንግሊዝም ሁለት ደረጃዎችን አሻሽላ 4ኛ መሆን ችላለች ፣ ፈረንሳይና ብራዚል አሁንም 17ኛ እና 18ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ሙሉ ሰንጠረዡ ይኸው እንድወረደ፡

1Spain15900
2Germany14370
3Argentina12810
4England11602
5Italy1157-1
6Colombia1129-1
6Portugal11291
8Netherlands11080
9Croatia10591
10Russia1055-1
11Greece10200
12Côte d’Ivoire9992
12Ecuador9990
14Switzerland993-1
15Mexico9680
16Uruguay9500
17France9290
18Brazil9240
19Ghana8657
20Belgium8640
21Sweden863-2
22Denmark8251
23Chile8157
24Bosnia-Herzegovina8142
25Mali8130
26Czech Republic7973
27Norway780-3
28Japan779-7
29Montenegro7562
30Nigeria74722
ተጨማሪ ያንብቡ:  ጠበቃቸውን እንዳያገኙ የተከለከሉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን ገለጹ

1 Comment

  1. FIFA is run by a corruption ring and I would not be bothered where they paced our team in their chart. they should sort out their scandal before they could judge others.

Comments are closed.

Share