ለመላው የክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፥ – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፪ሺህ፯ኛ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

ነገ ኢየሱስ ክርስቶስ በምድራችን በአካል የተገለጸበትን ፪ሺህ፯ኛ ዓመት እናከብራለን። እግዚአብሔር ወልድ በምድር በአካል ከእኛ ጋራ በታየበት ዘመን ያስተማረን ትልቁ ቁምነገር ፍቅርን ነው። በተቃራኒው እኛ የዘመኑ ኢትዮጵያውያን በመካከላችን ፍቅር ጠፍቶ እንበጣበጣለን። በስደት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሌላው ቀርቶ በእምነቱ ሥፍራ እንኳን ሰላም ካጣ ቆይቷል። የዚህ ሁሉ ብጥብጥ እና ፍቅር መጥፋት ምንጩ የትግሬ-ወያኔ እና እሱን መሰል ፀረ-ኢትዮጵያ ዓላማ ያላቸው ድርጅቶች እና ልሂቃን ናቸው። ስለዚህ እኒህን የጥፋት ኃይሎች በጋራ ትግላችን ግስጋሴያቸውን ልናቆመው ይገባል። ክርስቲያኖች ከኢየሱስ ክርስቶስ ምሣሌ መማር ካልቻልን እና ካልተፋቀርን መከራችን ይረዝማል፣ ሥቃያችንም አያባራም። የትግሬ-ወያኔ እና መሰል አጋሮቹም እንደሠለጠኑብን ዘመናት ይቆጠራሉ።

ለዚህ መፍትሔው ፈጣሪያችን በፍርድ ቀን ሲመጣ የሚጠይቀንን ጥያቄዎች፥ ማለትም፦ “ስታመም ጠይቃችሁኛል? ስራብ አብልታችሁኛል? ስታረዝ አልብሳችሁኛል? ስታሠር አስፈትታችሁኛል? ስጠማ አጠጥታችሁኛል?” የተባሉትን ሠርክ እናስታውስ፣ በተቻለንም መጠን የሕይዎት መመሪያዎቻችን ለማድረግ እንጣር።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን እንኳን ለበዓለ-ልደቱ አደረሣችሁ፣ አደረሰን፣ ይላል። በዚህ አጋጣሚ ድርጅታችን ማስተላለፍ የሚፈልገው ጥሪ፦ ባለፉት ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት በትግሬ-ወያኔ ግፈኛ እና ናዚያዊ አገዛዝ ከምድረ-ገፅ የጠፉትን በቁጥር ከ፭(አምሥት) ሚሊዮን የማያንሱ ዐማሮች እናስታውስ። በገዛ አገራቸው ከቅኝ ተገዢዎች በከፋ መልክ ሰብዓዊ መብቶቻቸውን የተነጠቁትን ኢትዮጵያዊ ዐማሮች እንታደግ።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይባርክ!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሕዝባዊ ዕንቢተኝነት ለኢትዮጵያ ትንሳኤ!

1 Comment

  1. ውይ 5000000አማራ በወያኔ ማለቁን አልሰማንም ነበር ወይስ ኢትዮጵያ ሁሉ አማራ ነው?

Comments are closed.

Share