የፍረጃ ፖለቲካ አይጠቅመንም!  መልስ ለሁኔ አቢሲኒያ ( ግሬስ አባተ)

በመጀመሪያ ይህን ፅሁፍ የምፅፍልህ ሌላውን ወገን ወግኜ ሳይሆን ይህ አካሄድ በመሰረታዊነት ትግሉን የሚጎዳ ስለሚመስለኝ ነው፡፡ በምንም ጉዳይ ትግሉን አንድ ኢንች በሚጎዳ ነገር ዝምታን አልመርጥም፡፡ ሲጀመር ሰራዊት ፍቅሬንና የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉን በአንድ ሚዛን ላይ የሚቀመጡ ግለሰቦች አንዳይደሉ በደንብ የምታውቅ ይመስለኛል፡፡ የቆሙለት አላማ በራሱ ይህንን አስረግጦ ስለሚነግረን በዚህ ላይ ጊዜ ማባከኑ ትርጉም የለውም፡፡ የመረጥከው ርዕስ በራሱ ሶስቱን ለይተህ ማቅረብህ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ ያልመረጥናቸው ስትል ቀሪዎቹን ወይ መርጠሃቸዋል ወይ ይሁንታ ሰጥተሃቸዋል ማለት ነው፡፡

(ግርማ ሰይፉ)

ያልመረጥናቸው ከምትል ይልቅ በምን መስፈርት ተመረጡ ብትል ጥሩ ይሆን ነበር፡፡ መብትህም ስለሆነ ! እንደምታውቀው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ የተቋውሞው ፖለቲካ ብቸኛ የፓርላማ ተወካይ ናቸው፡፡ እንደምታውቀው የተቃውሞ ጎራው የግድቡን ጉዳይ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ መዋሉ በተለይም የአረቡ አብዮት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመጣ ለማስቀየሻ የተመዘዘ እና በቂ ጥናት ሳይደረግበት ወደ ስራ በመገባቱ እንጂ የሚቃወሙት ግድቡ ለምን ተገነባ በሚል አይደለም፡፡ ስለዚህ አቶ ግርማ የፓርላማ አባል በመሆናቸው ብቻ የዚህ ልዑክ አካል መሆን ቢችሉ ብዙም የሚገርም አይደለም፡፡

ግድቡን አስመልክቶ የስርዐቱ አንዱ ችግር እንደውም ሌላውን ወገን አግልሎ የራሱን ፕሮፓጋንዳ መጫወቻ ማድረጉ ነው ትልቁ ችግር፡፡ ስለዚህም ይህን ግብዣ ማድረጋቸው እንደ ጥሩ ጅማሬ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ ሁኔታው ይህ ሆኖ እያለ በተለይም ከውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ጋር ተጨባብጠው ፎቶ መነሳታቸውን አስመልክቶ ‹‹የልኡካን ቡድኑ ውስጥ አቶ ግርማ ሰይፉ የሚል ስም ተሰማ…፤ በዚህ በርካቶች ተገረሙ ወይ እቺ አገር ሲሉም አዘኑ›› ይህ የተጋነነ ነው፡፡ ከዚህ ግድብ ጋር ተያይዞ ስርዐቱ በሚፈጥረው ፕሮፓጋንዳ ስንቶች በተቃውሞ ፖለቲከኞች እንዳዘኑ ብነግርህ እንዳይገርምህ፡፡ አንተ እንዳልከው ማዘን መገረም ሳሆን ህዝቡ ጋር ያለው ከዚህ በተቃራኒ እንደሚሆን እምነቴ የፀና ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በጎጠኝነት የታጀበ ከፍተኛ የስልጣን ሽኩቻ በብአዴን መንደር አለ - መስከረም አበራ

547 የስርዐቱ አባላት ባሉበት ፓርላማ የሚቻለውን ማድረግ የቻለ ግለሰብ ነው፡፡ ሰው የሚችለውን ሁሉ ያደርጋል፡፡ አንድ ድምፅ ይዞ የጎላ ለውጥ የሚያመጣበትን ምክንያት ከቻልክ ንገረኝ? እንዲሁ ሌላው ለሰራ ክሬዲት መንፈግ ካልሆነ በቀር ይህ አንድ ድምፅ ይዞ እንደሌሎች ለወከላቸው ህዝብ ሳይሆን ለፓርቲቸው ተጠሪ የሆኑ 545 ሰዎች ባሉበት ፓርላማ ያንን ያህል ጠንካራ ስራ አልሰሩም ተብሎ ሊወቀሱ አይገባም ባይ ነኝ፡፡ ከቻልክ ፖለቲካውን ከስሜትና ከጥላቻ በዘለለ ለማየት ሞክር፡፡ ፍረጃ ላለፉት ምናምን አመታት የሄድንበት ስለሆነ ያንን መድገም ካልሆነ በቀር የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡

ወደ ፍረጃ መሮጥህ ተገቢ ያልሆነ ነው፡፡ ቆይ አንተ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉን እንዴት አድርገህ ነው ምታያቸው? እስከሚገባኝ ግለሰቡ በሰላማዊ ትግል ለውጥ አመጣለሁ ብለው እየታገሉ ያሉ ግለሰብ ናቸው፡፡ አንተ ሰላማዊ ትግል ለውጥ ኤመጣም ልትል ትችላለህ፡፡ መብትህም ነው፡፡ ይህ ከሆነ እውነታው አቶ ግርማን ጨምሮ ሰማያዊ ሆነ አንድነት ውስጥ ያሉ የፓርቲ አባላትን ሕወሃት/ኢህአዴግ ጠላታችሁ ነው ወይ ብትላቸው? የምን ጠላት ነው፡፡ በሰላማዊ ትግል ጠላት የሚባል ነገር የለም ይሉሃል፡፡ባለው የህግ ማእቀፍ ውስጥ ሆኖ በሰላማዊ ትግል እየታገለ እንዴት እንደጠላት እንዲተያይ ወይም ግብዣ ሲቀርብለት ከጠላቶቼ ጋር እንዲል ትጠብቃለህ? የሚታገለው እኮ በሰላማዊ መንገድ ያለውን ስርዐት ለመቀየር ነው፡፡

ግለሰቦች የሚሉትን አስመልክቶ ፖለቲካው ላይ አቧራ ባናስነሳ ይሻለናል፡፡ አሁን መሬት ላይ ያለውን እውነት ይዤ ለመሞገት እንጂ ስለ አቶ ግርማ ጥብቅና ለመቆም አይደለም፡፡ ስለግለሰቦች መቶ ሺ ጊዜ ብንከራከር ለውጥ አናመጣም፡፡ አሉት የተባለው በራሱ ያን ያህል ለውንጀላ የሚቀርብ አይደለም፡፡ አንተ ራስህ ያቀረብከውን ልጥቀሰው ‹‹ይህ የአሁኑ ሰንደ ቃላማ ለእኔ ከበፊቶቹ ይሻለኛል፤ ሁሉም የታሰሩት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች ንፁህ ናቸው ብዬ አላምንም›› ያለውን ጠቅሰሃል በናትህ ፖለቲካውን ከስሜት በዘለለ ተመልከተው፡፡ በዚህ ሁኔታ ከቀጠልን አንድም ኢንች ወደፊት መራመድ አንችልም፡፡ ቀደም ብዬ አንዳልኩት ይህን አለ እከሌ እከሊት ይህን አለች የሚባል ፖለቲካም የለም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከዕዉነት ሽሽት…አስከ የት ? - ማላጂ

አሁን አሉት የተባለውን ከዚህ ቀደም አቧራ ተነስቶ ብዙ ሲባል አስተውያለሁ ነገሩን በቅንነት ማየት ነው የሚሻለው፡፡ የግለሰብ መብት በቅድሚያ እንዲከበር የሚታገል ድርጅት እንዴት ይህን ተናገርክ ብሎ ሊከሰው ይችላል፡፡ እንዳንተ ቢሆን ይህ ሰው ሂስ ማውረድ አለበት፡፡ በአንድነት ቤት ግን ይህ አይሆንም፡፡ ቃሉ በራሱ የሚለው እኮ ‹‹ይህ የአሁኑ ሰንደ ቃላማ ለእኔ ከበፊቶቹ ይሻለኛል›› እናስተውል! ለአንድነት አይደለም ያለው ‹‹ለእኔ›› ነው፡፡ ይህ መብቱን ታድያ ማን ሊከለክለው ይችላል? ለምሳሌ እኔን ብትጠይቀኝ ምንም ሌለበትን አረንጓዴ፣ቢጫ ፣ቀዩን ነው ምልህ! ግርማ እንዲህ ስላለ ግን ምንም ልል አልችልም መብቱ ነው፡፡ ለምን እኔ የመረጥኩትን ካልመረጥክ እንዴት ልለው እችላለሁ? ይህን ከቻልክ ብታስረዳኝ?

የታሰሩትን አስመልክቶ የሠጠው ለኔ ምንም የሚያስከፋ ነገር የለውም፡፡ ምንድነው ያለው ‹‹ሁሉም የታሰሩት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች ንፁህ ናቸው ብዬ አላምንም›› አሁንም እዚህ ጋር ሲገልፅ አንድነት ምናም ሳይሆን እራሱን ወክሎ ነው ሚናገረው፡፡ ይህ ማለት ግን የታሰሩት ሁሉ ወንጀለኞች ናቸው ማለት አይደለም፡፡ አልያም የታሰሩት በሙሉ ንፁሃን ናቸው ማለት አይደልም፡፡ ለምሳሌ ሁሉም ነፃ ናቸው ለማለት ቃሊቲን ጨምሮ በአገሪቷ ውስጥ ያሉ ሁሉም እስር ቤቶች ውስጥ ያሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞችን በሙሉ ማወቅ ያስፈልጋል ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ አንተኑ ልጠይቅህ በዝዋይ ምን ያህል ፖለተከኛና ጋዜጠኛ ታስሮ ይገኛል? ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ… እያልክ የምታውቃቸውን ብቻ ትጠራለህ እንጂ የማታውቃቸውን ከየት አምጥተህ ትጠራልኛለህ? ስለማታውቃቸውስ ጥብቅና ልትቆም ትችላለህ? ስለዚህ ‹‹ሁሉም›› ያሉበት ሁኔታ ስህተት ሊሆን አይችልም፡፡ ለምሳሌ እኔን ብትጠይቀኝ ብዙ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሉ ልገምት እችላለሁ ተናገር ብባል ግን አሁንም እንዳንተው እስክንድር፣ ርዕዮት ነው ልል የምችለው እንጂ የታሰሩት ሁሉ ንፁሃን ናቸው ለማለት በአገሪቷ ውስጥ ያሉ እስረኞችን ሁሉ ማወቅ ይጠበቅብኛል፡፡ ይህ ደግሞ የማይቻል ነው፡፡ ይህ ከሆነ እውነታው የሰጡት አስተያየት እንዴት ስህተት ሊሆን ይችላል?

ተጨማሪ ያንብቡ:  አማራ በድርድር የሚፈታ ችግር አልገጠመውም! ይነጋል በላቸው

እንዳልከው የልዑካን ቡድኑ ውስጥ ስለተካተቱ ግለሰቦች ይመጥናሉ አይመጥኑም በሚለው መነጋገር እንችላልን፡፡ ብንነጋገር እንኳ የመምረጥ እድሉ አልሰጡንም፡፡ ወይንም ህዝቡ እንዲመርጥ እድል አልተሰጠውም፡፡ ይህ ማለት ግን በጭፍኑ እዛ ውስጥ ያሉ ሁላ ከአንድ ምንጭ የተቀዱ ናቸው ማለት ጅምላ ፍረጃ ከመሆን ውጪ አያልፍም፡፡ እንዳልከው በዚህ ልኡካን የተካተቱ ግለሰቦች በስልጣን ዘመናቸው አንተ የጠቀስካቸውን ጨምሮ በርካታ ወንጀሎችን ሰርተዋል፡፡ እየሰሩም ይገኛሉ፡፡ የተከበሩ አቶ ግርማ ከዚህ ልዑክ ጋር አብረው መሄዳቸው እንዴት ሆኖ ነው ከነዚህ አምባገነኖች ጋር መተባበር ተደርጎ የሚወሰደው? የልዑኩ አላማስ ምንድን ነው? የሚለውን ጨምረህ ብትመልስልኝ አወዳለሁ፡፡

ቀደም ብዬ ያልኩትን መድገም ነው የሚሆነው፡፡ ግርማ ወደ እዚህ ልዑክ ሲሄድ እንዳልኩት በፓርላማ አባልነቱ እንጂ አንድነት ፓርቲን ወክሎም አይደልም፡፡ ይቅርታ የሚጠይቀውስ ምን አድርጌያለሁ ብሎ ነው? አንድነት ፓርቲስ ግለሰቡን የሚቀጣው በምን መስፈርት ነው? ፓርቲውስ መግለጫ የሚሰጠው በምን ምክንያት እንደሆነ አብራራልኝ፡፡ አሁን የመጣች ፋሽን አለች ግለሰቡ ይህን ተናገረ ይህን አሉ ያም በአመራር ደረጃ ያለ ስለሆነ የፓርቲው አቋም አድርገን እንወስዳለን የምትል ቀልድ፡፡ ለጊዜው አትመጥንምና ተዋት፡፡ ስለጉዞው ለምን አልነገረንም ለሚለው ከፈለገ የሚለን ይኖራል ሊገደድ የሚችልበት አመክንዮ የለም፡፡ ማንም እንደሚረዳው ብቸኛ መቀመጫ እንዳለው አባል መካተቱ ብዙም የሚገርም አይደለምና፡፡ አትሳሳት ፓርቲው ግን መልስ እንዲሰጥ አትጠብቅ፡፡ እዚህም እዚያም ለሚነሳ አቧራ ፓርቲው መግለጫ በመስጠት ጊዜ ሚያባክንበት ሁኔታ ተገቢነቱ አይታየኝም፡፡

ጥሩ ጊዜ ተመኘሁ!♡

https://www.facebook.com/gracet.sewoch/posts/9048768128693

8 Comments

  1. ተባረክ ተገቢ ምላሽ ነዉ የሰጠሐዉ:: ከመሬት ተነስቶ እንዲህ ነዉ እያሉ በመፈረጅ የለለ ስም ማዉጣት መልካም እየሰሩ ያሉትን ግልሰቦች ሞራል ይነካል:: ተገቢ ያልሆነ ትችት ከገንቢነቱ ይልቅ አፍራሽነቱ የጎላ ስለሆነ እየተድርገ ለለዉን ትግል እንዳይጎዳ ብንጠቀቅ መልካም ነዉ….ወንድሜ የሰተጠሃዉ መልስ በጣም ተስማምቶኛል

  2. Thank you for the nice and nonjudgmental comment. Individual like Mr. Girma are focused on, what is good for Ethiopia and ethiopian. His struggle is not to replace TPLF by another hater dictator but to build. Democracy in Ethiopia.
    Lately all attacs directed to Girma is lead by hater chauvinist to weaken the struggle for true democracy based on individual rights.
    Guys open your eyes time changed.

  3. A futile attempt to defend another Kehdetu. Shame on you trying to tell us that weyanie is not an enemy. Letting aside the 1997 massacre, the Gambella atrocious killing, thousands of disappearances, killings and torcher of our Muslim brothers•/sisters, your party’s gallant leadership members Andualem, Habtamu, all the reporters languishing in jail, our dear sick sister Reyote Alemu and all Muslim leaders etc.
    • Dislocation of thousands of our people from the place where they used to live for years
    • Expulsion of everyone from their place of work
    • Looting of our country’s property etc….
    And last but not least the recent biting and incarceration of the peaceful demonstrators in Addis and the killing of 5 innocent people at Bahr Dar. Unless we call these monsters, enemies of our people whatelse should you want us to call them. Mousellini had done nothing compared to what these evils did in the course of two decades. So, please go and tell them how great they are and sing to that demised rotten leader of theirs’ and definately you will be given free land, money and their left overs.

    As per Girma he doesn’t deserve to be a leader in the party that belonged to Andualem and Habtamu. Andenet party has to take quick corrective action and purge this individual and cleanse the part otherwise its existence as party will be questionable and will be doomed to fail.
    The struggle is neck and neck and you should not let blacksheeps to infiltrate your leadership heirarchy. Be courageous enough to say a spade a spade. Girma is to the pack of wolves
    and Andenet belongs to the people.

    • I’m not affiliated to any party. I would definitely decide to make my decision eventually. In the meantime I would support all parties, movements, factions, student and youth movements, who make arduous contribution to free our country from the evils and carpetbaggers. They don’t belong to Addis and our country for that matter. I support Semayawi, I respect Andenet for challenging the enemy peacefully day in day out. I believe imploring and dinning with the enemy is betrayal of the imprisoned young gallant leaders of both parties. No negotiation whatsoever with weyanie. No kind words! They just have to go!!!!! Period. Whether they build bridges, roads, dams doesn’t matter at all. We have had enough of them.

  4. ጥሩ አስተያየት ነዉ:: አነ የጠላሁትን ካልጠላህ … የሚል አስተሳሰብ የትም አያደርስም

Comments are closed.

Share