ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ

ቁ. 2

በተለያዩ ዘመናት በአገራችን ወደ ሥልጣን የመጡት ገዥዎች፤ ሕብረተሰባችን ከፋፍሎ ለመግዛት እንዲያመቻቸው የዘር ግንድ እየቆጠሩ አንዱን ከሌላው የተሻለ አስመስሎ በመሳል፤ አንደኛውን በሌላኛው ወግን ላይ በስነልቦና ቂም እያናከሱ፤ የግፍ ግዛት ዘመናቸውን አሳልፈው አሁን ከአለንበር ዘመን ደርሰናል። በአሁኑ ጊዜ በሥልጣን ላይ የተፈናጠጠው መንግሥት ደግሞ ገና ከጅምሩ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በረቀቀ ተንኮል የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር ሐረግ ከፋፍሎ ለመግዛት እንዲያመቸው አንቀጽ 39ኝን በሕገመንግሥት አጽድቆ ለረዥም ዘመን በጋራ ሕብረተስባዊ ገመድ ተሳስረው የኖሩትን ኢትዮጵያዊያን በጎሳ በመከፋፈል በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ያሉ ብሔረሰቦች ተፈጥሮአዊ የሆነውን እና ሊከባበሩበት የሚገባውን ማንነታቸውን ጦርና ጋሻ አድርገው እንዲዋጉበት በማድረግ ነው የሥልጣን እድሜውን እያራዘመ ያለው።
(ጎንደር ፋሲል ግምብ – ፎቶ ፋይል)
ታዲያ ይህ መንግሥት ለአገራችን ሰላም ያመጣል በሚል ከፋፍሎ ለመግዛት እራሱ በቀመረው የጎሳ ክልል ቀቢጸ ተሥፋ “በብሔሮች” ራሥን በራሥ የማሥተዳደር ሥም፤ አብሮ የኖረውን እያራራቀ፤ ተፈቃቅዶ ይኖር የነበረውን እንደጠላት እያሥተያዬ፤ አካባቢያዊ ሰላምን እያደፈረሰ፤ እርሥ በርሥ እያጋደለ ያለው ትልቁ ችግር በአገራችን ላይ የተደነገገው ህገመንግሥታዊ አደጋ፤ ከሃያ ሦስት ዓመት በኋላ ህግ አውጭውን አካል እና መንግሥታዊ መዋቅሩን በማሥጨነቅ እርስ በራሱ ሲያተራምስ እያየን ነው። በመሆኑም፤ ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣነው እና በድህረ-ገጽ ለማሳነበብ እንደሞከርነው ሁሉ፤ አሁንም በድጋሚ የምናሥገነዝበው፤ መንግሥታት መጥተው፤ መንግሥታት ሲያልፉ፤ የማያልፈውን የቅማንት እና የአማራ ህብረተሰቦች የጋራ ታሪክ ዘመኑ ባመጣው የጎሳ ፖለቲካ ጉንፋን መሰል አሥተሳሰብ እና ድርጊት የኋላ ታሪካቸውን ማጥቆር እና የወደፊቱንም ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ማጨለም አይገባም እንላለን።
ሰለዚህ ይህን አገር አፍራሽ፤ ሰላም አደፍራሽ የሆነውን አንቀጽ 39ኝን እንደ መብት ማስከበሪያ በመጠቀም የቅማንት የማንነት እና ራሥን በራሥ የማሥተዳደር ጥያቄ ያነሱ የቅማንት ተወላጅ ወገኖቻችን ያልተገነዝቡት ነገር፤ ተዋልዶና ተጋብቶ፤ አንድ ሐይማኖት አምልኮ ለረዥም ዘመን ከኖረው ወገናቸው ጋር አብሮ የማያኗኑር መሆኑ ነው። ቅማንት እና አማራ ጊዜ እና ቦታ አንድ ላይ ያሥቀመጣቸው ብቻ ሳይሆኑ፤ እጅግ ብዙ የጋራ ችግር እና ደሥታን ጽዋ አብረው የተጎነጩ፤ ረዥም የታርክን ጎዳና አብረው የተጓዙ፤ እምነትና ቋንቋ ባንድ ገመድ ያስተሳሰራቸው ሕዝቦች መሆናቸውን ነው። ይህ ሲባል ግን፤ መለሥተኛ ችግሮች ተከስተው አያውቁም ማለት አይደለም። በሁለቱ ህብረተሰቦች መሃከል የነበረው ችግር ግን፤ በሁለት ወንድማሞች መካከል ከሚከሰት ችግር የተለዬ አልነበረም። ስለሆነም ነው በየጊዜው የሚፈጠሩ መለሥተኛ ችግሮቻቸውን በጋር እየፈቱ እና መቻቻልን መሰረት አድርገው የአንድነታቸውን ታሪክ ጠብቀው ከዚህ የደረሱት። ወደፊት ማደግና መቀጠልም ያለበት በዚሁ መንገድ ነው። ይህ ደግሞ በማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ያለ እና የሚኖር ነው።
ይህን ሥንል ግን፤ የቅማንት ብሔረሰብ ወገኖቻችን ይህን ጥያቄ ያለ ብሶት አነሱት በማለት በጭፍን ለመኮነን አይደለም። ሆኖም፤ በኛ እይታ፤ አሁንም በድጋሚ ማሥገንዘብ የምንፈልገውው፤ ችግሩ የመልካም አሥተዳደር በደል እንጂ፤ ለቅማንቱ ችግር ምንጭ አማራው አይደለም። ለአማራውም ችግር ምንጭ፤ ቅማንቱ አይደለም። ይህ የአሥተዳደር በደል ቅማንቱ ራሱን ሥለከለለ ይፈታል ብሎ ማሰብ፤ እጅግ ሥህተት ነው። በመላ አገሪቱ የተንሰራፋው የአሥተዳደር በደል፤ በመላ አገሪቱ ሳይፈታ፤ ለአንድ ጎሳ ብቻ ነጻ እና ዲሞክራሲያዊ መብት እንደ መና ከሰማይ ሊወርድ አይችልም። እሁን እዬተሄደበት ባለው መንገድ ሊመጣ የሚችል ለውጥ ቢኖር፤ በአካባቢው ባልተወለዱ ባልሥልጣኖች ከመበዝበዝ ይልቅ፤ ከራሳችን በተወለዱ መሪዎች መበዝበዝን ነው። ምክንያቱም በዬትኛውም የአገራችን የጎሳ ክልልን እንደ ነጻነት ቆጥረው በተግባር ለማዋል የሞከሩት አካባቢዎች ያተረፉት ሃቅ ይህ ሲሆን አይተናል እና።

ተጨማሪ ያንብቡ:  " የነ ጃሥ ዋር "ታላቁ ሤራ ፤ በኃይማኖት ግጭት ፤ ተጀምሯል። - ሲና ዘ ሙሴ  

ስለሆነም፤ በሰሜን አሜሪካ የምንኖር ጉዳዩ ያገባናል የምንል የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጆች፤ በአገር ቤት የተወሰኑ የቅማንት ተወላጆች፤ ያነሱት የማንነት እና የራሥን በራሥ ማሥተዳደር ጥያቄ አለመመለሥ ምክንያት በተወሰኑ ግለሰቦች መካከል እርሥ በርሥ መተነኳኮስ መጀመሩን ሰምተን እጅግ በጣም አዝነናል፤ ቀጣዩም አሳስቦናል። የዚህን ጥያቄ አደገኛነት ባለፈውም ጠቁመናል፤ እሥከ የት ሊዘልቅ እንደሚችልም አመላክተናል። አሁንም በድጋሚ ያለፈውንም ሆነ የወደፊቱን የጋራ ባህላችን እና የጋራ አካባቢያዊ የኑሮ ዘይቤ አበላሽቶ እና መጥፎ አሻራ ጥሎ የሚያልፍ መሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።

አሥተሳሰቡ እና ድርጊቱ፤ ሁሉንም የሕብረተሰብ አባሎች የማይወክል እንደሆነ ብናውቅም፤ የሁኔታው መከሰት ግን፤ በራሱ አሥደንጋጭ እና አሳዛኝ፤ እንዲሁም አሳፋሪም ጭምር ነው። ይህ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግሥት ባመጣው የጎሳ ወጥመድ ውስጥ የገቡ ወገኖች የሚያራምዱት አስተሳሰብ አስከፊ ውጤት ሊሆን የሚችለው፤ መንግሥታት መጥተው፤ መንግሥታት ሲያልፉ፤ የማያልፈውን የሁለቱ ህብረተሰቦች የኋላ ታሪካቸውን ማጥቆር እና የወደፊቱንም ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ማበላሸት ብቻ ነው።

እንዲህ አይነቱ ለማንም ወገን የማይጠቅም ልብ የሚኢያሻክር ድርጊት በአስቸኳይ መቆም አለበት። ይህን በማለታችን እንደ ድፍረት ሊያሥቆጥርብን አይገባም። እኛም ለተወለድበት አካባቢ፤ ለተፈጠርነበት ህብረተሰብ የሚበጀውን የቅርብ እና የሩቅ ራዕይ የማመላከት ግዴታ አለብን እና። ይሁንና፤ በሁለቱ ሕዝቦች ውሥጥ የሚገኙ ሽማግሌዎች፤ አዋቂዎች፤ እና ምሁራን ሁኔታውን አግባብ ባለው እና በሰከን መንገድ ይፈቱታል ብለን እናምናለን። ከሁሉም በላይ የአካባቢውን ሰላም እና መረጋጋት ታሳቢ አድርገው በሁለቱ ህብረተሰቦች መሃከል ሰላማዊ ንግግር ተጀምሯል የሚል ሰምተናል። ይህ ጅምር ከወዲሁ የሚበረታታ ሲሆን፤ የጋራ ወገኖቻችንን የቆዬ ፍቅር የሚያረጋግጥ ክሥተትም ጭምር በመሆኑ፤ ጠንክሮ እንዲቀጥል በአክብሮት እናሳሥባለን። እኛም የአብሮነት ሂደቱ እና በአካባቢው ሰላማዊ ኑሮ እንዲቀጥል የምንችለውን ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ ነን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የንጹሃን ደም ያሰከረው አሸባሪው ህወሃት መቀበሪያውን እያፋጠነ ነው! - በሚራክል እውነቱ

በተጨማሪም፤ ማንኛውም ግለሰብ፤ ቡድን፤ ድርጅትም ሆነ የመንግሥት አካል በሥሜት ተገፋፍቶ እና ባለማወቅ ወይም ሁኔታውን ለተለዬ የግል አላማ አሥቦ የሚንቀሳቀስ ቢኖር፤ “አንተ ሰላም እንድትውል ጎረቤትህ ሰላም ይሁን” እንዲሉ፤ የሚፈጠረው የሰላም መደፈረስ ሁሉንም የሚጎዳ በመሁኑ ከመጥፎ ተግባር እንዲቆጠብ ለማሳሰብ እንወዳለን። ህዝቡም፤ የላይ የታች ሳይባባል በአንድ ሆኖ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱትን ትክክል አደላችሁም ማለት የሚገባ መሆኑን ጊዜው እያመላከተ ነው። አገር በሰነፎች እንደማይገነባ ሁሉ፤ ሰላምም በነገረኞች አይረጋም እና።

በዚህ አጋጣሚ ሁለቱም ህዝቦች መገንዘብ ያለባቸው አጠቃላይ ሁኔታውን እና የሰሞኑንም ቤተሰባዊ አለመግባባት የፈጠረው የመንግሥት ፖሊሲ እና አሰራር መሁንን ነው። “ውኃው ሂያጅ ደንጊያው ቀሪ” እንደ ሚባለው ሕዝብ ይኖራል መንግሥት ግን ያልፋልና። የሚያልፍ መንግሥት ዘላለማዊ የሚኖር የታሪክ ጠባሳ ጥሎ እንዳያልፍ መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው። እያንዣበበ ያለው ችግር ከፍ ሲል የኢትዮጵያ ዝቅ ሲል ደግሞ የጎንዳር ሕዝብ ችግር ነውና አብረን ተባብረን ወደ ሰላም እና የዘር ክልል ያልበከለው ሁለንተናዊ የአንድነት ወንድማማቻዊ ጎዳና እንምራው።

በመጨረሻም፤ “እርቅ፤ ደም ያደርቅ” እንዲሉ፤ የተጣላውን እያሥታረቀ ለዘመናት ራሱን ጠብቆ የኖረ ህዝብ፤ ዛሬም የገጠሙትን ችግሮች በለመደው ባህላዊ የሽምግልና ጥበብ እየፈታ ወደፊት እንዲቀጥል ጥርጥር የለንም። ለሁሉም ወግኖቻችን እና ሕዝባችን፤ ሰላሙን እና ደህንነቱን የምንመኘው ከልብ ከሚመነጭ ፍቅር እና አክብሮት ጋራ ነው።

ጉዳዩ ይመለከተናል ከምንል የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጆች፤ ሰሜን አሜሪካ።

7 Comments

  1. keshim diaspora, how do you know that the question is not public question? you really don’t have the right to say so as long as you are not putting any effort for the people development. you are land scavenger. let come and take a land from poor farmer. this is what we saw from diaspora. what is the problem with Amara people if we get the recognition we have been denied by successive governments of Ethiopia? Can’t we live together after all? you re living in US where you really don’t have any connection with!. Still we all love each other. Amara are our brothers and sisters!

    Please leave your stupid propaganda!

  2. Thank you very much indeed: the tplf is doing everything to destruct the Ethiopian people attention from its criminal activities in every life of our people. the Tigre fear and hate the people of Gondar therefore they hire some innocent individuals local y and want divide and re write the history of our people. what is the real difference of the so called kimant from the mara/ aren’t they inter merried and speak the same language? the issue was religion and now all of them worship the same god and why they want return back and divide the people. be hold !! the tplf will go sooner or later but the people remain and we must think wiser not to follow the tplf trick and think twice what the division will create among our people. The tigre divide us and has looted our wealth of humera wolkait and tegede and now they gave us an old homework hahah…. at the end of the day the tplf and its hired sabouters will regret the most Ethiopia shall survive.

  3. ኮሜንት ለመስጠት በስድብ አይጀመርም ስህተት እንካን ቢኖርበት በትህትና ልትነግረው ስትል ስድብ መቅደሙ ለምን አስፈለገ በፅሁፍህ የተማርህ ትመስላለህ የተማረ ሰው ደግሞ አይሳደብም ምክንያቱም የሚሳደቡ ተናግረው ማሳመን የማይ ችሉ ስለሆኑ ።
    ከምነቃቀፍ ስህተቱን ብናሳየው የበለጠ እንገነባዋለን መማማርን ብናዳብር ህዝባችንን ከችግርና ከውድቀት እናድነዋለን።

  4. We have to be careful that Ehadeg cadres wanted to divide Amharas among themselves to make them weak and racists. Wake upball Amhara, stay united and fight against woyane.

  5. Dear “Keshim” you are Mad! why? where is your logical reason for the establishement of kimant zone? can this be a good solution? Don’t you think Kimants will suffer more than Amhara if civil wars started due to border & other clashes (if kimants separated)? Anyways don’t be fool- —

  6. Yalesh mesloshal tebeltesh alkeshal ! Only talk and talk end less talk. Try to do some thing practical as a solution other wise shar up!! 25 years of wereeee!

  7. Dear Amhara, Have you been restricted from your right to movement within your territory? why are you considering that being recognized and having definite territory mean being bounded to that line? IS really amahara is limited only within Amhara region? if you really recognized being amhara and having a specific region for it, what is your problem if others have thier own? Why don’t you consider those boundaries as equator and longitudinal line? Please Don’t force me my attitude towards you guys!
    Please don’t be too selfish! We used to have boundries and you know it definately if you are really Amhara living around, and Don’t blame TPLF(infact I don’t like them), rather blame your people who are racially biased and stereotyping other innocent peoples.

Comments are closed.

Share