በአሲድ የተደፋባት ትግስት ቀብሯ ተፈጸመ

በአሰቃቂ ሁኔታ አሲድ ፊቷ ላይ የተደፋባት ወጣት የቀብር ስነ-ስርዓት መፈጸሙን የዘ-ሀበሻ ጋዜጣ ዘጋቢ ከአዲስ አበባ ገለጸ። እንደ ሪፖርተራችን ገለጻ ቁጥሩ ብዛት ያለው ሕዝብ በቀብር ስነስር ዓቱ ላይ በመገኘት ሃዘኑን የገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይም የሟችን ሁለት ልጆች በመርዳት ላይ ሕዝቡ ሲያወራ እንደነበር ተናግሯል። በውጭ ያሉ ሰዎችም የሟችን ሁለት ልጆች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉና መልካም ዜጋ እንዲሆኖ ለማድረግ መረባረብ እንዳለባቸው ከአዲስ አበባ የደረሱን አስተያየቶች ጠቁመዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሟች ትግ እስት ጉዳይ የአዲስ አበባ ጋዜጦችን እና መጽሄቶችን ከፍተኛ ሽፋን ማግኘቱ ታውቋል። በዚህም መሠረት ቅዳሜ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ስለትግስት መኮንን ሞት የሚከተለውን ጽፏል። ለውድ አንባቢዎቻችንና ጋዜጣውን ማግኘት ለማይችሉ ስካን አድርገን አቅርበናል። ይመልከቱት፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  “የአሸባሪው ታጣቂዎች ትግራይ የኢትዮጵያ አይደለችም የሚሉ ጽሁፎችን በየግድግዳው ጽፈው ሄደዋል
Share