የቀሲስ በላይ የገቢው ምንጭ ምድን ነው ?

መረጃ ፦ የገቢው ምንጭ ምድን ነው ?

ቀሲስ በላይ የሚሰራው ቤተክህነት ነው ፣ የቤተክህነቱ ደመወዝ ሁሉም የሚያውቀው እውነት ነው ፣ በቅሩቡ 15 ቀን አይሆንም በኢትዮጵያ ብር 40,000,000 ( አርባ ሚሊዮን ብር ) የፈጀውንን ቤቱን ሰርቶ ከገባ ይህ በእንዲህ እንዳለ

በአፍሪካ ኅብረት ግቢ ውስጥ የውጭ ሃገር ገንዘብ ማስቀመጥ ይቻላል። ቀሲስ በላይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፓትርያርኩና ከአቡነ አብርሃም ቀጥሎ ዋና ባለልጣን ሲሆን ከሀገር ቤት አልፎ አሜሪካ አካውንት ከፍቶ $5,000,000 ሚሊየን ዶላር በትላንትናው ዕለት ወደ አካውንቱ ሊያስገባ ሲል

የባንኩ ሰዎች ፈሩ ደነገጡም ሲመጣም የኦሮሞ ደኅንነቶችን አጃቢ ይዞ የመጣው። የባንኩ ሠራተኞች ጨነቃቸው። ቆይ አንዴ ይጠብቁን ፕሮሰስ እያደረግንሎት ነው አሉት ከዛም እዛው እንደተቀመጠ በፌዴራል ፓሊስ ተይዞ ታሰረ ፦ ነገ ከጀርባው ባሉ ሰዎች ጥረት በዋስ ሊፈታ ይችላል ቤተክህነቱ ግን ይህንን ዘራፊና ወንበዴ በመንግሥት ስም እየነገደ ያለን ወንጀለኛ ከስልጣኑ ሊያግድ ይገበዋል ፣ ቤተክህነቱ ሰው ካለው ጉዳዩን ጊዜ ሳይሰጠው እሁንም አጣርቶ የዚህ ሰው የገቢ ምንጭ ምንድን ነው ? ከጀርባው ማን ነው ያለው ? ኔቶርኩን ከኢትዮጵያ እስከ አሜሪካ ዘርግቶ ከፍተኛ የገንዘብ ምዝበራ የሚፈጽምው እሱ ማን ነው ?

እርግጥ የመረጃ ምንጮቻችን እንደነገሩን አንዳንድ ጳጳሳትም በተመሳሳይ አሜሪካ አካውንት ከፍተው ዶላር እያከማቹ እንዳሉ ጠቁመውናል ይህም ወደፊት ተጣርቶ በመረጃ የሚገለጽ ይሆናል ፦ በተራው ሠራተኛ ላይ ቀንበር እየጫኑ ማንነታቸውን በገንዘብ ያደለቡ ህገወጦች ላይ ቤተክህነቱ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው ለመጠቆም እንወዳለን ።

ሳባ
@EthiAmhara
ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያውያኑ በአላሙዲ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ተቃውሟቸውን አሰሙ

3 Comments

  1. From Zemedkun’s page

    “…ኦሮሞነቱ ጊዜ የሰጠው፣ የጃዋር፣ የአቢይ አሕመድ፣ የአዳነች አበቤ፣ የሽመልስ አብዲሳ የጡት አባት፣ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት መሥራች፣ የፈይሳ አዱኛ ታቦት ቀራጭ፣ የኮሬ ነጌኛው አባል፣ የኦህዴድ የፓርላማ ተመራጭ፣ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድቤት ዳኛ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ቀውሲ በላይ መኮንን 6 ሚልዮን 50 ሺ ዶላር በውጭ ሀገር ወደሚገኘው ባንክ ዶላር ሲያዘዋውር ቁጥጥር ስር መዋሉን ቀደም ሲል ዘግቤ ነበር። ዘገባዬን ፋና ዛሬ አረጋግጦልኛል። ”
    “…ለበላይ መኮንን ኦሮሞነቱ ያድነዋል። አቢይ አህመድ ይደርስለታል ተብሎ ይጠረጠራል። በላይ ሲያዝ “ቆይ አንድጊዜ አቢይ ጋር ልደውል” ያለውም እኮ የሚያውቀው፣ የሚተማመንበት ነገርም ስላለው ነው። ዳኞቹም፣ ፎሊሶቹም፣ ዐቃቤ ሕጎቹም በአንዲት ስልክ ከጥፍራቸው ውስጥ ማስደበቅ ይችላል። የውጭ ምንዛሬ ሃራራ ያለበት አገዛዙ ለመውረስ ካልፈለገ በቀር፣ …”

  2. ‘ቀሲስ ‘ በላይ ቄስ ነኝ ማለቱ ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ብቻ ሳይሆን ለማንም አማኝ ማፈሪያ ነው። ካለፈው ታሪኩም በጣም ደካማ ዜጋ ነው። ይቺ ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን ይህን ነጋዴ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መሪ ማድረጓ ምን ያህል እንደ ወደቀች አንድ ምስክር ነው። ራሷን ከዚህ ዓይነት ማፈሪያ ፍጡር ማጽዳቱ አስቸኳይ ግዴታ ነው። ይህን ሰው የኦርቶዶክስ ቤተ ክህነት መሪ አድርጋ ተሸክማ፣ በየአድባሩ የሚስጠው ስብከት ዋጋ የለውም። ይህን ሰው የሾመው ሲኖዶሱ ከሆነ፣ አስቸኳይ ምንጠራ መጀመር ያለበት ከሲኖዶሱ ነው። በነጋዴ የምትመራ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ክብር ሊኖራትና ልትሰማ አትችልም።

  3. ሳባ 40 ሚሊዮን ብር 6 ሚሊዮን ዶላር ምን አላት ሰውዬው የድንቁ ደያስና የጁዋር መሃመድ ኔት ዎርክ ውስጥ ያለ አብይ ኦርቶዶክስን እንዲያተራምስ የወከለው ሰው ነው፡፡ ጁዋር መሃመድ ሰውን አሳርዶ ደም አቃዥቶት ድረሱልኝ ቢል ጁዋርን የማታውቅ ኦርቶዶክስ እኔም አላውቃትም ያለ ደፋር ነው፡፡ ኦቦ ጁዋር በአንጻሩ እኛ አካባቢ ክርስቲያን ቀና ቢል በሜንጫ አንገቱን እንመታለን ያለ ነው ፡፡በዚህ ድርጊታቸው ቀሲስ በላይ ቀሲስ ቀማኛ ተብሎ ቀደም ብሎ ወደ ከርቸሌ መውረድ ይገባው ነበር; ነገር ግ ን ማን ማንን ይሰር? ከላይ ሽመልስ አብዲሳ አብይ መሃመድ ሆነና ህዝቡ የእግዚሃርን ፍርድ እየጠበቀ ነው፡፡ ዘራፊውና ገዳዩ ስብሃት ነጋ ተለቅቆ ጻድቃን ገ/ተንሳይ 900 ሚሊዮን ብር አጥቁሮ ወስዶ ጠግበው ያልበሉት ሰው አትግደሉ ብለው የተናገሩት አቶ ታድዮስ ታንቱ ታስረዋል፡፡ እንዲህ ነው የብልጽግና ኢትዮጵያ፡፡ አቡ አከሌ ኡስታዝ ምናምን የሚሏቸው ኢትዮጵያ ኑረው ከአረብ በላይ አረብ የሆኑትንም ማስተንፈሻ ይስጥልን፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share