ቆሜ ነው እምሞተው ( አሥራደው ከካናዳ )

/
ለነፃነት፤ ለእኩልነትና ለወንድማማችነት፤ ለሚታገሉ የለሕሊና እስረኞችና ለኢትዮጵያ ትንሳኤ ለሚዋደቁ የፋኖ ጀግኖች መታሰቢያ ትሁንልኝ ::
ለነፃነት፤ ለእኩልነትና ለወንድማማችነት፤ ለሚታገሉ የለሕሊና እስረኞችና ለኢትዮጵያ ትንሳኤ ለሚዋደቁ የፋኖ ጀግኖች መታሰቢያ ትሁንልኝ ::

አልጠብቅም ሞትን – ተኝቼ ባልጋዬ ፤
እኔው እሄዳልለሁ – ፈረሴን ቼ ! ብዬ ፤
አልፈልግም ዋሻ – የምደበቅበት ፤
አልፈልግም ጢሻ – የምሸሸግበት ፤
አልሰብርም አንገቴን – አላዞርም ፊቴን ፤
አይዝልም ጉልበቴ – አላጥፈውም ክንዴን ፤
እጠብቀዋለሁ – ደረቴን ነፍቼ ፤
በኩራት በድፍረት – አንገቴን አቅንቼ ፤
አልንበረከክም – ቆሜነው እምሞተው ፤
የጀግና ልጅ ጀግና መሆኔን ይወቀው !!
በ’ንባ አልታጠብም – ቁጭብዬ አላለቅስም ፤
ጉልበቴን አጥፌ – አልንበረከክም ፤
አልጠብቅም እሱን – ወደኔ እስቲመጣ ፤
እኔው እሄዳለሁ – ወደሱ እንዳይመጣ ፤
ኩራቴን ይረዳው – ድፍረቴን ይወቀው ፤
ተጋድሜ አልሞትም – ቆሜነው እምሞተው !!

አልጠብቅም ሞትን – ማታ በጨለማ ፤
እንዲወስደኝ ብዬ – ሰው ሳያይ ሳይሰማ ፤
አለምንም ከቶ – ዛሬን እንዲተወኝ ፤
ዘግይቶ እንዲመጣ – ዕድሜ እንዲለግሰኝ ፤
ወይ እንደ ባለጌ – እያሞላቀቀ ፤
ሞት መጥቶ እስቲወስደኝ እያጨማለቀ ::
ጭራሽ !
እጠብቀዋለሁ – በጠራራ ፀሐይ ፤
መሃላዬ ይሁን – ቃል ለምድር ለሰማይ ፤
ዳግም ድል አድርጌ – እስክነሳ ድረስ ፤
ቆሜነው እምሞተው እንደ ክርስቶስ ::
አገኛለሁ ብዬ – ትርፍራፊ እድሜ ፤
አልጠብቅም ከቶ – እኔ ተጋድሜ ፤
ወደሱ እሄዳለሁ – ወደ’ኔ እንዳይመጣ ፤
ግንባሬን አላጥፍም – የመጣው ቢመጣ ፤
ተኝቼ አልጠብቅም – ሞት መጥቶ እስቲወስደኝ ፤
እኔው እሄዳለሁ – በቁሜ እንዲያገኘኝ ::
ለመኖር ጓጉቼ – አልንበረከክም ፤
ዛሬን ተወኝ ብዬ – አልለማመጥም ፤
አልንበረከክም – ቆሜነው እምሞተው ፤
የጀግና ልጅ ጀግና መሆኔን ይወቀው !!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ማሩኝ›› የምትልበት ከመምጣቱ በፊት ‹‹በቃኝ›› በል!

ኅዳር 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ( November 17. 11. 2023 )

 

1 Comment

  1. አቶ ታድዮስ ታንቱን ለዚህ እንግልት የዳረጋችሁ ስቃዩ እናንተ ላይ ይድረስ፡፡ ኑሯቸውን ሳይደላቸው ኑረው ላገር ስላሰቡ ይሄ ሁሉ መከራ ሊደርስባቸው ይገባል? ስብሃት ነጋን በክብር ሸኝቶ እኝህን ድጋፍ የሌላቸው ዜጋ እንዲህ ማንገላታት አግባብ ነው? አብይ ምንም የሃይማኖት እሳቤ ውስጥህ የለም በባህልም ተበድለሃል፡፡ እንዲሁ አይቀጥል መቼም፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share