August 29, 2023
4 mins read

በሕዝባችን ላይ የማያባራ ሁኔታ የሚፈፀመውን ማንነት ተኮር ጭፍጨፋ የዘር ማፅዳት የዘር ፍጅት ግድያና ጅምላ ማፈናቀል

ለኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስትር

አዲስ አበባ

ጉዳዩ:- የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን ይመለከታል

እኛ ስማችን ከዚህ ማመልከቻ ጋር አባሪ የተደረገው ቁጥራችን 34 የሆንን አማሮች በሕዝባችን ላይ የማያባራ ሁኔታ የሚፈፀመውን ማንነት ተኮር

ጭፍጨፋ የዘር ማፅዳት የዘር ፍጅት ግድያና ጅምላ ማፈናቀል እንዲሁም መንግሥታዊ አቅሞችን በመጠቀም ጭምር የሚፈፀሙ ዘር ተኮር መዋቅራዊና

ሥርአታዊ ሁሉን አቀፍ ጥቃቶችን በመቃወማችን የሕግ የሞራልና የተፈጥሮ ኃላፊነታችንን በመወጣታችንምክንያት ተደራራቢ የሆኑ ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች

ጥሰቶች እየተፈፀመብን ይገኛል::

፩: ያለምንም ወንጀል አማራነታችን እንደወንጀል ተቆጥሮ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሕግን ባልተከተለ መንገድ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ታፍነን በጅምላ ታግተን እንገኛለን::

፪: በፀጥታ ኃይሎች እገታ በተፈፀመብን ወቅት ከፍተኛ ድብደባ አማራነታችን እየተጠቀሰ አዋራጅ ዘለፋ ስድብና ዛቻ ተፈጽሞብናል::

፫: በፌድራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ ከታገትንበት ጊዜ ጀምሮ ብሔር ተኮር ዘለፋ ማስፈራራት የግድያ ዛቻ እንዲሁም በጨለማ ክፍል ማሰርን ጨምሮ ቤተሰብ ማንገላታትና ዛቻ የዕለት ተዕለት ሰቆቃ ሆነውብናል::

ከዚህ በከፋ መልኩ መሳሪያ የታጠቁ የፀጥታ ኃይሎች በሕይዎት የመኖር መብታችንን ለመንጠቅ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የከፋ ተጋላጭ አድርጎናል::

፬: ፍርድ ቤት የመቅረብ የሕግ ጠበቃ የማማከር የሃይማኖት አባት የማግኘት እንዲሁም በቤተሰብና ጎብኝዎች የመጠየቅ ሰብአዊ መብቶቻችን ሙሉ

በሙሉ ተገድበው ይገኛሉ::

በመሆኑም የፍትህ ሚኒስቴር ከላይ በዝርዝር ያስቀመጥናቸውን እጅግ አስከፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ባስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግባቸው በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት እንዲወጣ እየጠየቅን ይህ አቤቱታ በግልባጭ የተደረገላችሁ ሀገራዊአህጉራዊና አለማቀፋዊተቁአማት የኢትዮጵያ መንግሥት አለማቀፍ የሰብአዊ መብት መርሆችን አክብሮ እንዲንቀሳቀስና በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፅመውን ማንነት ተኮር ጥቃት እና ጭፍጨፋ እንዲያቆም ታሪካዊ ኃላፊነታችሁንትወጡ ዘንድ እንጠይቃለን::

ከሠላምታ ጋር

የማይነበብ ፊርማ

ግልባጭ:

ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

ለኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት

ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት

ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት

ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን

ለኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቁአም

ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን

ለአውሮፓ ህብረት

ለተመድ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን

ለዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት

ለብሪታኒያ መንግሥት

369647808 715460857266245 7244258926934520547 n

369579884 715460900599574 8358943059858009957 n

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop