August 28, 2023
7 mins read

ከአለም አቀፍ የጠለምት አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ድጋፍ ኮሚቴ የተሰጠ የአቛም መግለጫ

Fyg4buZXsAIjJKr 1 1

ነሓሴ 21 ቀን 2015 አ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስቴር የሆኑት  አብርሐም በላይ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ የአሸንዳን ባእል ምክኒያት በማድርግ ለትግራይ ህዝብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያላስገባ ብሄራቸውን ማዕከል ያደረገ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነት በአዋረደ መልኩ ያስተላለፉት መልዕክት ከአንድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስተር ነኝ ከሚል ሰው የማይጠበቅ፤ ሃላፊነት የጎደለው፤ የያዙትን ሀላፊነት የማይመጥንና አሳፋሪ መልዕክት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

“የአከባቢው የማንነት እና ወሰን ጥያቄ በተመለከተ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል ካለ በህግ እና በህገ መንግስቱ መሠረት እንዲመለስ እየተሰራ ይገኛል” ፤ በማለት የተገለፀዉ የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት እና ራያ ህዝብ ከ4 አስርት አመታት በላይ ያካሄደው ትግል የካደ በመሰረቱ ትህነጋዊ የሆነ አስተሳሰብ ነው፡፡

– “የተፈናቀለ ህዝባችን’’ የሚለው አገላለፅ ወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ማህበረ-ሰብ ያፈናቀለው ህዝብ የለም፡፡ ይልቁንስ የጠለምት ፤ ወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አማራ በመሆኑ ብቻ በትህነጋዊ በጅምላ ሲገደል፣ ሲፈናቀል እና ሲሳደድ በአጭሩ ማንነትን የማፅዳት ዐለምአቀፍ ወንጀል የተካሄደበት፤ በማንነቱ ምክንያት ግፍ እና መከራ ሲቀበል የኖረ ህዝብ ነው፡፡ በቅርቡ በጠለምት፤በማይካድራና በራያ ሕዝብ የተፈፀመው የጦር ወንጀል/war crime and crime against humanity/መጥቀስ ብቻ በቂ  ነው፡፡

– ሪፈረንደምን በተመለከተ በእርሱ አባባል ትግራይ የሚገኘው “የተፈናቀለ ህዝብ”  ወደ ወልቃይት ጠገዴ ጠለምት በመሄድ በህዝበ ውሳኔው ተሳታፊ እንዲሆንና ውሳኔው ወያኔ በሚፈልገው መልክ እንዲጠናቀቅ በማስብ ነው፡፡ የማንነት ጥያቄው የአማራ ህዝብ አካል የሆነው የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ህዝብ ጥያቄ እንጂ ከትግራይ ክልል የምጣ ተፈናቃይ ለምን ሪፈረንደም ይሳተፋል?

-የጠለምት ህዝብ ከ1983 በትህነግ ከተወረረበት ጊዜ ጀምሮ ለፌደረሺን ምክር ቤትና ለአማራ ክልል መስተዳደር ያለ ማንነታችን እና ያለ ፍላጎታችን በትግራይ ክልል ተካልለናል፤ ማንነታችን አማራ ነው በማለት ህጋዊ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ስለዚህ የማንነት ጥያቄ በሚመለስባቸው አግባብ መሰረት በአስቸኳይ ፌደሬሽን ምክር ቤት ህዝቡን በማነጋገር እና ጥናት በማድረግ ምላሽ መስጠት ይገበዋል፡፡

-ባለጉዳይ እና ባለቤት ነኝ የሚል አካል በማለት የተገለፀው አባባል ሰፊውን የአማራ ህዝብ አይመጥንም፡፡ የአማራ ህዝብ የወሰን እና ማንነት ጥያቄዎች በህጋዊ መንገድ ምላሽ እንዲሰጠው እየጠየቀ  እንዳለ ይታወቃል። ስለሆነም ምንስቴሩ ሁለቱም ክልሎች በእኩልነት እና ፍትኃዊነት መመልከት ሲገባቸዉ፤ ለተመደቡበት ክብር እና ፕሮቶኮል በማይመጥን መልኩ የወሰን እና ማንነት ጥያቄዎች ባለባቸው አካባቢዋች ያሉ የአስተዳደር መዋቅሮች መፍረስ አለበት በማለት የተገለፀዉ፤ የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ህዝብ ውድ መስዋዕትነት እና ዋጋ በመክፈል በደሙ ያገኝውን ነዖነት የሚክድ ነው፡፡

በመሆኑም ሚንስቴሩ የተሰጣቸውን ስልጣን እና ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ለግል ፍላጎታቸው እና ለህውኃት መቆማቸው ያስመሰከሩበት መግለጫ ነው፡፡ ይህንን በመገንዘብ አስቸኳይ የአማራን ህዝብ ታላቅ ይቅርታ እንዲጠይቁና ለንግግራችው እርምት እንዲወስዱ  በአንክሮ እንጠይቃለን፡፡ የጠለምት፤ የወልቃይት ጠገዴና የራያ ሕዝብ የማንነትና የወሰን ጥያቄ በሪፈረንደም ሳይሆን የሚፈታው በፖለቲካና በህጋዊ መንገድ በመሆኑ መንግስት ለተጠየቀው ጥያቄ ፖለቲካዊና ህጋዊ መንገድ ምላሽ እንዲስጥበት በአጵንኦት
እንጠይቃለን።

በመጨረሻም የጠለምት የማንነትና የወሰን ጥያቄ መንግስት እንደሚለው በ ሕዝበ-ውሳኔ መሆን እንዳለበትና ተጠማኝን በድምጽ መስጠት ባለእርስት ለማድረግ  ማንነት በደም፤ በትውልድ፤ የሚወረስ የማይቀየር የማይናወጥ ሆኖ እያለ ሕዝባችንን የሌለ ማንነት በድምጵ ብልጫ/በኮሮጆ በሚሰበሰበው ብጥስጣሽ ወረቀቶች ለማጭበርበርና ሕዝባችንን ለዳግም ባርነትና ስደት፤ እርስታችን ለወራሪና ለመጤ አሳልፈው ለመስጠት ውስጥ ለውስጥ የሚሰሩ አንዳንድ ተቛማትና ሙሁራን ነን ባዮች የጠለ ተወላጆች በጥቅማ ጥቅምና በስልጣን ተደልለው  ሕዝብን እያወናበዱ እንዳሉ በተጨባጭ የደረስንበት በመሆኑ ከዚህ እኩይ ተግባራቸው እንዲቆጠቡና ሳይረፍድ ከሕዝባቸው ጎን እንዲቆሙ ለማስጠንቀቅ እንወዳለን።

አማራ ነን አልን እንጂ አማራ እንሁን አላልንም።
ህልውናችን በትግላችን
ከአለም አቀፍ የጠለምት አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ድጋፍ ኮሚቴ

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

Go toTop