የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አማሮቹን ያፈናቀልነው በስህተት ነው አሉ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አህመድ ናስር

ባለፉት ሁለት ሳምንታት በሺህ የሚቆጠሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ከቤንሻንጉል ክልል ተፈናቅለው በጎጃም ፍኖተሰላም አካባቢ እንዲሰፍሩ የተደረገው በስህተት መሆኑን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገለፁ። የተፈናቀሉት በሙሉ ቀደም ሲል ወደነበሩበት እንዲመለሱ መወሰኑንም አስታወቁ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አህመድ ናስር በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ሰሞኑን ከክልሉ እንዲፈናቀሉ የተደረጉ የአማራ ተወላጆች በሙሉ እንዲመለሱ መወሰኑን ገልፀዋል።
በክልሉ ከአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከኦሮምያ ከመሬት ጥበት፣ ከአፈር ምርታማነት ማጣት ጋር በተያያዘ የተሻለ መሬት ፍለጋ ሰዎች ወደ ክልሉ እንደሚገቡ የገለፁት አቶ አህመድ ነገር ግን ሰፈራው በሕገ-ወጥ መንገድ ሲፈፀም መቆየቱን አስታውሰዋል።
“እኛ የምንቃወመው በሕገ-ወጥ መንገድ በደን ውስጥ እየገቡ ደን እየመነጠሩ ሰፈራ ማስፋፋቱን ነው። ይህ ደግሞ ለክልሉ ብቻ ሳይሆን እንደ ሀገርም አደጋ አለው” ያሉት አቶ አህመድ “በሕገ-መንግስታችን መሠረት ማንኛውም ሰው ለስራ ቢዘዋወር ችግር የለውም” ብለዋል።
ነገር ግን አሁን ከክልሉ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት ለምን እንደሆነ ርዕሰ መስተዳደሩ ተጠይቀው ከታች ያለው አስተዳደር ስህተት በመፈፀሙ ነው ሲሉ አምነዋል። አስተዳዳሪዎቹ ሕዝቡን ያፈናቀሉት ሕገ-ወጥ ሰፈራውን ከነባሩ የመለየት ስራ ላይ ተናቦ የመስራት ችግር በማጋጠሙ ነው ብለዋል።
“አስተዳደራችን አካባቢ ስህተት ተፈፅሟል። መፈፀም ግን አልነበረበትም። ነገር ግን እንደ ክልል መንግስት በሕገ-ወጥ መንገድ የሰፈሩትን መቆጣጠር አለብን። ኅብረተሰቡ በፈለገው ጊዜና ወቅት እየተነሳ ደን እየመነጠረ መስፈር አስቸጋሪ ስለሆነ ስርዓት መያዝ አለበት የሚል አቋም አለን” ያሉት አቶ አህመድ ስህተት የፈፀሙ የአስተደደር አካላት ላይም ግምገማ በማካሄድ ማስተካከያ እናደርጋለን ብለዋል።
በጉዳዩ ላይ ከአማራ ክልል ባለስልጣናት ጋር ምክክር መደረጉንም ያስታወሱት አቶ አህመድ ችግሩ በድጋሚ ሊፈጠር የማይችልባቸውን ቀዳዳዎች ለመድፈን ከአማራ ክልል መንግሥት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱንም ተናግረዋል።
እስካሁን ባለው ሁኔታ ወደ 1 ሺህ 346 አባወራዎች ከ3 ሺህ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲፈናቀሉ መደረጉን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ችግሩ ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ጋር የተያያዘ መሆኑንም አስረድተዋል።
“በክልላችን አንዳንድ ቦታዎች ሰዎቹን ወደ አካባቢው ካስገቡአቸው በኋላ የሚታይ ችግር አለ። በተለይ ከመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ችግር አለብን። በየጊዜው እናጣራለን፤ እንጠርጋለን፣ እንገመግማለን ችግሩን ግን ሙሉ በሙሉ ማፅዳት አልተቻለም” ሲሉ ተናግረዋል።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወደ ክልሉ መግባትና መውጣት የሚያስችል ሕገ-መንግስታዊ መብቱ የተከበረ መሆኑን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም ከአማራ ክልል ወደ ክልላችን ለስራ በሚገቡበት ሁኔታ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን አመልክተዋል። ይሁን እንጂ የክልሉ ደን እንዳይወድምና ጥበቃ እንዲደረግ ከአማራ ክልል ጋር ከስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።
በትናንትናው ዕለት በፍኖተ ሰላም ከተማ ተፈናቃዮችን ወደመጡበት አካባቢ ለመመለስ 11 መኪኖች መዘጋጀታቸውንና ተፈናቃዮቹን የሚያጅቡ የፌዴራል ልዩ የፖሊስ ኃይል መታጀባቸውን የዓይን ምስክሮች ገልፀዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አስገደ ገ/ስላሴ ለህክምና አሜሪካ ገቡ

10 Comments

  1. Mr Ahmed ,you are illegally also on the power. This governer has to go to school again to learn to more about the difference between what he says mistake and what we say this is a crime.

  2. At least he accepts responsibility, but I believe that the mistake was done by Federal (TPLF/EPRDF) I don’t believe without the permission of the federal government the regional government will NOT do as big as this displacement. However, the Shaebia infested (TPLF) is the ordering and reversing the decision, but the apologizing party is the regional (puppet) government.
    TPLF never ever accepts its mistakes.

    • You are right Kiros. The problem is there are tens of thousands Tigrayans in Benishangul-Gumuz, in Southern Ethiopia engaged in lucrative businesses. There literally none from other ethnic groups in Tigray region doing business. Tigrayans are taking jobs from locals in Gumuz in gold trade, in bamboo production, etc.

  3. Thousands of people have been displaced and lost their belongings, families, suffered and so on,…now they telling us that was a mistake? what a joke! what about going to jail for life? Where is justice? playing with peoples life is just a simple mistake? These people needs to go to hell, burn in hell…

  4. The Tigre who are settelled in Amara land in: wolkait; Kebtya; Humera and Setit estimated to be around 750.000 Tigre will be deported in the future:

  5. Well, if they really have been returned to their home that will be fine. But we have still the following questions:
    1/ they should get back their property intact.
    2/. The Federal government should announce to the public how many Amhars have been killed and how many houses have been burnt and bring the criminals to justice.
    3/ If the Federal government doesn’t do this we have to do our own research and bring the criminals and the Federal government to International Criminal Court for the genocide they have committed agains the Amhara.
    4/ Both the local and Federal government should vow to protect the Amahars from another round attack.
    5/ Those who have been displaced from Guraferda also should be returned and compenseted for their loss.
    6/ Whatever hapens, we the Amharas will never and ever forget what hapened to our people and should not losen our belt. We knew what TPLF is cooking for the Amhara and knowing that we should always be alert and watchful. We should organise ourselves for survaival otherwise TPLF has clear plan to exterminate the Amhara first then Ethiopia and build Greater Tigrai on the garave of the Amhara and Ethiopia. Fellow Amhara brothers and sisters, do not relax, we are in a grave danger. Organise yourselves, otherwise our race will be history. Do not be fooled by the return of some Amharas to Benishangul. This is for the timebing. They will do it in some other ways after some time in a subtle way. Do not forgate what they have done to us so far and do not forgate what they have planned to us. When you forgate this and start to relax, then you will be finished.

  6. ok then he has to face charges for his dumest action,who is going to pay their loss,how about the lost lives.what a shame!!!!!!!

  7. No matter what this stooge and Robot says , The master mind of this high profile crime are : Melese Zenewi, Sebhat Nega ,Abay Tsehye ,Seye abreha ,Seyoum Mesfen and the rest woyane hard cores will face trial and recieve their poetic justice .

Comments are closed.

Share