September 23, 2022
5 mins read

አርበኛ እና ፋኖ ዘመነ ካሴ ያለምንም መዘግየት በአስቸኳይ እንዲፈታ፣ (ዓለም አቀፍ የአማራ ህብረት)

zemene 2መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም

አማራው ብሎም ኢትዮጵያ ጦርነት ላይ ባለችበት በአሁኑ ሰዓት ይህን ህዝብን አስተባብሮ ጠላትን ድባቅ ሊመታ የሚችል መሪ ማሰር ትልቅ ስህተት ነው:: አርበኛ ዘመነ አገራችንን ለማፈራረስ ቆርጦ የመጣውን ጠላት ወደመጣበት አፍሮ እንዲመለስ ብዙ ዋጋ የከፈለ የአገር ባለውለታ መሆኑ እየታወቀ ለእስርና ለእንግልት መዳረጉ አማራ ክልልም ሆነ ኢትዮጵያ ህዝብን ማስተዳደርና መምራት በማይችሉ ስብስቦች እንደተያዙ አንድ ማሳያ ነው::

የተፈጠረውን አለመግባባት በሽምግልና እና በእርቅ ለመጨረስ ከመግባባት ላይ ከደረሱ በኋላ ክህደት በመፈፀም ተሸምጋዩን ለእስር መዳረግ ኢሞራላውና ከፍተኛ ነውርም ከመሆኑም በላይ ይህ በሴራ የተከናወነ እስር ብዙ መዘዝ የሚያመጣ አደገኛ አካሄድ ነው:: ሽምግልና ለአማራ ህዝብ ሺህ አመታት ያስቆጠረ የተከበረ የግጭትና አለመግባባት መፍቻ እሴቱ መሆኑ እየታወቀ አገዛዙ በተንኮል አርበኛ ዘመነ ካሴን ማሰሩ ከህዝቡ እሴትና ባህል ጋር መላተሙ መሆኑን ይረዳው ይሆን? ወጣቱስ አገዛዙ በወሰደው የክህደት እርምጃ ተደናግጦ ከጀመረው ሁለንተናዊ የህልውና ትግል ያፈገፍጋል ብሎ ገምቶ ይሆን? በእኛ እምነት የአርበኛ ዘመነ ካሴ መታሰር የተደራጀውን ብቻ ሳይሆን ተዘናግቶ የነበረውን ማህበረሰብ ወጣት አዛውንት ሳይል ወደ ትግሉ እንዲቀላቀል አዲስ ተነሳሽነት ያመጣል ብለን በፅኑ እናምናለን:: መሆን ያለበትም ይኸው ነው:: አገዛዙ ቀይ መስመር ያለፈ በመሆኑ መላው የአማራ ህዝብ ለህልውናው እምቢ ብሎ በመነሳት የሚደረገውን ኢፍትሃዊነትና እብሪት አሁኑኑ በቃህ ሊል ይገባል:: አማራውን ብሎም መላው ኢትዮጵያን ከትርምስ ለመታደግ ዓለም አቀፍ የአማራ ሕብረት የሚከተሉትን ጥያቄዎች ያቀርባል:

ለመንግስት አካላት፦

1ኛ/ አርበኛ እና ፋኖ ዘመነ ካሴ ያለምንም መዘግየት በአስቸኳይ እንዲፈታ፣

2ኛ/ ህግ ማስከበር በሚል ሽፋን ባለፉት አምስት ወራት ለእስር የተዳረጉ ፋኖዎች፣ የልዩ ኃይል አባላት: ሚሊሻዎች፣ የመከላከያ አባላትና የፓለቲካ ድርጅት እባላት ከእስር እንዲፈቱ፣

3ኛ/ እንደ ታዲዮስ ታንቱ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ፣ ጎበዜ ሲሳይ፣ አባይ ዘውዱ፣ ደራሲ አሳየ ደርቤ የመሳሰሉት አላግባብ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና ማህበራዊ አንቂዎች እንዲፈቱ፣

4ኛ/ በኦሮሚያ ክልል በተለይም በወለጋ የሚደረገውን የአማራው ጭፍጨፋ ለማስቆም ትርጉም ያለው ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲጀመር፣ 5ኛ/ በትህነግ የተወረሩ የአማራና አፋር አካባቢዎችን ነፃ ለማውጣት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን፡፡

ለአማራ ህዝብ፦

1ኛ/ የወጣትነት ዘመኑን በሙሉ ለአማራ ህልውና፣ ለኢትዮጵያ አንድነት የሰዋውን ጀግናህን በፍጥነት ከእስር እንዲወጣ የማድረግ ግዴታ ያለብህ መሆኑን ተገንዝበህ እንደ አባቶችህ ትግልህን በጥበብ እንድታካሂድ ለማሳሰብ እንወዳለን::

2ኛ/ ለፍትህ የቆማችሁና የአማራውን የህልውና ትግል ለምትገነዘቡ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ግፊት በማድረግ ያለ አግባብ የታሰረውን አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ ሁሉም አገርን ከወረራ እና ከመፍረስ የታደጉ ፋኖወች፣ ጋዜጠኞች እና ማህበራዊ አንቂዎች እንዲፈቱ ከፍተኛ ጥረት እንድታደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን::

አማራ የጀመረውን የህልውና ትግል በአሸናፊነት ይወጣል! ኢትዮጵያ በቆራጥ ልጆቿ ትግል ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop