የአቶ መለስ ልጅ መንግስትን በጣልቃ ገብነት ተቃወመች፤ የመለስን ፎቶ ካለ ፈቃድ መጠቀም ሊከለከል ነው

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የቀድሞ የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የበኩር ልጅ ወጣት ሰምሀል መለስ ባለፈው ቅዳሜ በተቋቋመው “የመለስ ፋውንዴሽን” ውስጥ መንግስት ጣልቃ መግባቱን ተቃወመች።
ቅዳሜ መጋቢት 28 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተካሄደው የፋውንዴሽኑ የማቋቋሚያ መስራች ጉባኤ ላይ ወጣት ሰምሀል ፋውንዴሽኑ የመለስ አስተሳሰብ ምንጭ መሆን ሲገባው መንግስት በፋውንዴሽኑ ላይ ሚናው መጉላቱ ተገቢ አለመሆኑን ተናግራለች።
ወጣት ሰምሀል በፋውንዴሽኑ ምስረታ ወቅት “አሰራሩ እኔ አልገባኝም። ከዚህ በፊትም ቤተሰብ አንስቶ ነበር። በአዋጁ ላይ የመንግስት ሚና መጉላቱ ስህተት ነው ብለናል” ስትል ተቃውሞዋን አሰምታለች።
ሰምሀል የመንግስትን በፋውንዴሽኑ ጣልቃ መግባትን ብትቃወም ከፋውንዴሽኑ 13 የቦርድ አባላት አራቱ ከቤተሰባቸው ዘጠኝ ደግሞ የመንግስት አካላት ሆነው የተመረጡ ሲሆን ወደፊት አዋጁን በማሻሻል ሌሎች አካላትን ለማሳተፍ ከመታሰቡ ባለፈ በዕለቱ የሰማህል ሃሳብ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።
በተያያዘ ዜና የቀድሞ የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ምስል ያለቤተሰቦቻቸውም ወይም በስማቸው ከተቋቋመው ፋውንዴሽን ፈቃድ ውጪ በማንኛውም ቦታ መለጠፍም ሆነ ምስላቸውን ቀርፆ መጠቀም ሊከለከል ነው።
የአቶ መለስን ምስል ያለፈቃድ መጠቀምን የሚከለክለው ረቂቅ መመሪያ የተዘጋጀው በአዋጅ ቁጥር 781/2005 አንቀፅ ዘጠኝ ንዑስ አንቀፅ 2(ሰ) መሰረት ነው።
ረቂቅ መመሪያው ባለፈው ቅዳሜ የመለስ ፋውንዴሽን ይፋ በተደረገበት ወቅት ለውይይት ተበትኗል። በረቂቅ መመሪያው ስለ ምስላቸው አጠቃቀም በሚያወሳው አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ (1) ላይ ማንኛውም ሰው ለክቡር አቶ መለስ ዜናዊ ያለውን ፍቅርና ክብር ለመግለፅ ምስሉን በመኖሪያ ቤቱ ግድግዳ ላይ ሊሰቅል፣ በአልበም ውስጥ፣ በቦርሳው፣ በኪሱ፣ በተሽከርካሪው ወይም በሌላ የግል መጠቀሚያው ሊይዘው ከሚችለው በስተቀር ምስላቸውን ገንዘብ ለማሰባሰብ ፣ ለሽያጭ፣ ለባዛር፣ ለጨረታ ወይም ለማንኛውም የንግድ ድርጅት ወይም ሌላ ተቋም ማስታወቂያ፣ የንግድ ምልክት፣ ለመታሰቢያነት ወይም ለማንኛውም ጥቅም ማስገኛነት ሊሰቅል ወይም ሊቀርፅ ወይም በማንኛውም ሁኔታ ሊያስቀምጥ እንደማይችል አስቀምጧል። Semahal Meles, Azeb Mesfin and Marda Meles weeping over Meles Zenawi’s death
ከዚህ በተጨማሪ የአቶ መለስን ምስል በተለየ ሁኔታ ለህዝባዊ አላማና ጥቅም ለመጠቀም የፈለገ አካል ከቤተሰባቸው ወይም ከፋውንዴሽኑ ቦርድ ፈቃድ ማግኘት እንዳለበት መመሪያው ያስገድዳል።
በተያያዘም ከፋውንዴሽኑ ፈቃድ ውጪ በአቶ መለስ ዜናዊ ስም ማንኛውንም አይነት ግንባታ ለመገንባት በማሰብ የእሳቸውን ስም፣ ምስል ወይም ስራዎች በመጠቀም ገንዘብ ወይም ቁሳቁስ መሰብሰብን ረቂቅ መመሪያው ከልክሏል።¾
ምንጭ፡ በአዲስ አበባ ታትሞ ዛሬ ኤፕሪል 10 ቀን 2013 ለገበያ የዋለው ሰንደቅ ጋዜጣ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሀይሌ ገብረስላሴ ስልጣን ለቀቀ

8 Comments

  1. leave alone his photo, I do not like even whenever people talk a lot about him. As I said before, let the board members collect a lot of money to send him in the hell to bribe the manager of the hell to minimize his punishment and to prepare a guide line for his followers about the status of revolutionary democracy in the hell.

  2. She is a poor tigre and Eritrean Banda: She has to wait till we unearthed her father remain and will send it for her to Adwa and seraye:the land of the banda.

  3. what a law who wants to display meles’s picture in his or her wallet or in his home. you weyanes are the ones forced people to do it,no body cares about meles in any way shape or form. don’t blow your trumpet.

  4. WEGEGNA NACHEW ABO NEGE GIZEW SEEDERS YETENKOL , YEFIRHAT ENA YE CHIKANE MASTAWEKIA ENASERGEWALEN YE MELES CHIRAQUN PHOTO.

Comments are closed.

Share