October 24, 2022
5 mins read

የአማራ እጣ ፈንታ በራሱ ወኪሎች እንጂ በሌሎች አይወሰንም!! – የአማራ ኅብረት በሙኒክ (ጀርመን)

German Amhara Association

German Amhara Associationየአማራ ኅብረት በሙኒክ (ጀርመን)
Amhara Union in München (Deutschland)
የአቋም መግለጫ

የሕወኃት ዘረኛ ቡድን በኦነግ አጃቢነት መንበረ ሥልጣኑን ከተቆጣጠረብት ጊዜ አንስቶ የአማራ ሕብረተሰብ በጠላትነት ተፈርጆ እንደ ዜጋም ሆነ እንደ ብሔር እውቅናን አጥቶ ራሱን የማስተዳደር መብት ተነፍጎ በሞግዚት አስተዳደር የሚገዛ ሕዝብ ነው ።

አማራ በማንኛውም ነገር ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች አነስተኛ ሆኖ ሳይሆን በ30 ዓመቱ የዘር ፖለቲካ እንደ ማንኛውም ራሱን ያደራጀና ውክልና ያለው ሆኖ አለመገኘቱ ጥቅሙን ብቻ ሳይሆን ህልውናውን ጭምር ለአደጋ ዳርጎታል ። በመሆኑም በሰሜን በትግራይ ወራሪ ኃይልና በደቡብ በመንግሥታዊ መዋቅር የሚታገዘው የኦነግ ሰራዊት ማንነትንና ዘርን መሠረት አድርጎ የሚፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል የአማራ ህዝብ ወኪል ነኝ የሚለው ብአዴን/ብልጽግና አማራውን ከዘር ፍጅቱ ሊከላከለው ይቅርና መቃወም አልቻለም።

በተደጋጋሚ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ሲፈፀም በአማራ ክልል ም/ቤትም ሆነ በፌደራል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ወንጀሉን በሥሙ ጠርተው የዘር ማጥፋት (Genocide) ወንጀል መፈፀሙን ተቀብለው አቋም ሊወስዱ ይቅርና ብሔራዊ የሀዘን ቀን እንኳን ማወጅ አልቻሉም። በአጭሩ የአማራ ብልጽግና እመራዋለሁ ለሚለው ህዝብ ፍላጎት ፣ ጥቅምና ደህንነት መቆም አልቻለም። በመሆኑም አሁንም እንደዚህ ቀደሙ በኦነጋዊና ህዋሃታዊ ሴራ ድርድሩ የሚያመጣው “ሰላም” የአማራን ሽንፈትና ቀጣይ መካራ የሚያመጣ እንዳይሆን ስጋት ስላለን የአማራ ህብረት ሙኒክ ጀርመን:-

1ኛ. በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት እየተካሄደ ያለውን የሰላም ውይይት በስልጣን ሽኩቻ ጦርነት ከፍተው የአማራንና የአፋርን ክልል የጦር ሜዳ ያደረጉት ትህነግና የኦሮሞ ብልጽግና አማራን ወክለው ጥቅሙን ያስጠብቁለታል የሚል እምነት ስለሌለን አማራ በራሱ ወኪሎች ቢደራደር ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንድሚያመጡ እርግጠኞች ነን ።

2ኛ. የጦርነቱ መንስኤዎች ሥልጣን የጨበጠው የኦህዴድ ብልጽግናና ሥልጣኑን የተቀማው ትህነግ እንጂ የሶስቱ ክልል ወዳጅ ሕዝቦች ባለመሆናቸው ተወያይተው ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት የሚችሉት ገለልተኛ ተወካዮቻቸውን በማሳተፍ መሆኑን የምናምንበትና የአማራ ማህበር በአሜሪካ ለአወያዮች ያቀረበውን የመወክል ጥያቄና ያቀረባቸውን አራት ተወካዮች የሚያምናቸውና የሚቀበላቸው መሆኑን የአማራ ሕብረት በሙኒክ (ጀርመን) ያረጋግጣል ፤

3ኛ. የአማራን ሕዝብ ለማዳከምና ረፍት ለመንሳት ሆን ብለው ያለ ወንጀላቸው ወንጀል እየፈበረኩ ያሰሩትን ዘመነ ካሴን ፣ የአማራ ፋኖዎችን እና የህሊና እስረኞችን በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፤

4ኛ. በኦሮሚያ ክልል በአማራው ላይ የሚካሄደውን የዘር ማጥፋት ወንጀል መንግሥት ኃላፊነቱን ወስዶ እንዲያስቆምና ወንጀለኞችን ለፍርድ እንዲያቀርብ ጥሪ እናቀርባለን ፤

አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ

የአማራ ማህበር ሙኒክ (ጀርመን)

23.10.2022

Stadtsparkasse München IBAN:DE ____________________________BIC: SSKMDEMM ______

Leave a Reply

Your email address will not be published.

311278404 422940713362723 2315275887077441253 n
Previous Story

“ምነው ባልተወለድን እያልን በሞተ ሰው እየቀናን ኖረናል” የራያ አላማጣ ነዋሪዎች

bayisa wak woya `
Next Story

የታቀደው የመንግሥትና የሕወሃት ንግግር፣ መሰናክሎቹና የሚጭረው ተስፋ – ባይሳ ዋቅ-ወያ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop