“ ሞት አይቀርም ፤ ሥም አይቀበርም ። “ እና  ለሥማችሁ ሥትሉ ፤ ተመሥገን ደሣልኝን እና ታዲዎስ ታንቱን ፍቷቸው

ሲና  ሙሴ

የመንግሥት ህግ አሥከባሪ ወይም ወንጀልን ተከላካዩ ፤ የአቃቢ ህግ መሥሪያ ቤት ወይም ተቋም  ፣ ንፁሐን የአለአንዳች ተጨባጭ  የሆነ  የህግ መተላለፍ ፤ ያለማሥረጃ ፤ በፖሊስ እየታፈኑ ሲታሰሩ እያየ ፣ “ ይኽ አካሄድ ህግን የጣሰ ነው ።

“ ብሎ ለመሞገት አልቻለም ።  የፍትህ ሚኒስትሯም ይኽንን ህገ ወጥ ተግባር በግልፅ ለማውገዝ የሚያሥችል ወኔ አጥተዋል  ። ጭራሽ ድምፃቸው ጠፍቷል ። ምናልባትም የአፋኞቹ እጅ ረጅም በመሆኑ ለደህንነታቸው ሰግተው ይሆናል ። ድምፃቸውን ያጠፉት ። ለሠላም ሚኒሥቴር ድኤታው ያልተመለሱ በመንግሥት ውሥጥ መንግሥት የሆኑ ፤ ከህግ በላይ የሆኑ  ኃይሎች ፤  ለፍትህ ሚኒሥትሯ እንዴት ሊተኙ ይችላሉ ?

ፖሊሱንም ሆነ አቃቢ ህጉን በቁጥጥራቸው ሥር በማዋል  ዳኞችንም በብልፅግና ፓርቲ ሥም በመጠርነፍ ልዩ ጥቅም እንዲያገኙ በማድረግ ፣  ለህሊናቸው ሳይሆን ለጥቅማቸው እንዲዳኙ በውዴታ ለጥቅም  ሟች በማድረግ ፣በአገሪቱ ህግ ላይ እንዳሻቸው እየፈነጩበት እንዳለ በአይናችን እያየን አይደለም እንዴ ?! ( የኢትዮጵያ መከላከያ ያላለውን ብሏል ብለው ዋሥትና በማሥፈራርቿ የሚያሥከለክሉ   አይደሉም እንዴ ? የተከበረውን መከላከያ መነገጃ ሲያደርጉ ማን ጠየቃቸው ? ) እንዳሻቸው  ፍርድን ሲያጣምሙ ። በነፍሰ ግድያ ያልተጠረጠረን ፣ ከኢትዮጵያ ጠላት ጋር ያልተባበረን ፣ የሽብር ፀር የሆነን ጋዜጠኛ እንደ አሸባሪ እና እንደ ሚሥጥር ሰራተኛ ወይም ሰላይ ሲከሱ  እያሥተዋልን አይደለም እንዴ ? በጋዜጠኛ ተመሥገን ደሣለኝ እና በጎምቱው ጋዜጠኛ በአቶ ታዲዎሥ ታንቱ ላይ ፣ ግፍ ና እንግልትን በደመ ቀዝቃዛነት እየፈፀሙ ያሉትሥ “ እኛ ፈላጭ ቆራጭ ነን ። ከህግም በላይ ነን ። “ የሚሉ አምባገነኖች አይደሉም እንዴ ?

ዐቃቤ ሕግ ጋዜጠኛ ተመስገን ” ወታደራዊ ምስጢሮችን ለሕዝብ ይፋ በማድረግ፣ ሐሰተኛ የሆኑ ወታደራዊ መረጃዎችን በማውጣት፣ ለአመጽ ሕዝብን ማነሳሳት ። ” የሚሉ ክሶችን አቅርቦበታል ። ሲጀመር ተመሥገን ደሣለኝ ጋዜጠኛ አንጂ የመከላከያ አባል አይደለም ። የመከላከያ   ዓባል አለመሆኑ እየታወቀ ለምን ይኽ ክሥ እንደቀረበበት በራሱ ግራ ያጋባል ። ቅጥረኛ ሰላይ ሆኖ በወታደራዊ አታሼነት ከውጪ አገር ካልተላከ በሥተቀር የአገሩን ወታደራዊ ምሥጢር ለመሠለል እንዴት ይተጋል  ? ወይም ለማወቅ ከተጋ ምሥጢሩን በረብጣ ብር ይሸጣል እንጂ እንዴት በይፋ መፅሔት ላይ በማውጣት ለአገሩ ዜጎች በሙሉ ያሣውቃል  ? ያም ሆነ ይኽ ፣ ተመሥገን ከቶም ወታደራዊ ምሥጢሮችን   የሚያውቅበት መንገድ የለም ። በመፅሔቱ ያወጣቸው ወታደራዊ ጉዳዮችም ፣ የሠራዊቱን ህይወት የሚመለከቱ ፣ በሠራዊቱ ውሥጥ ያለው አንድነት እንዲጠናከር ቀድሞ ከነበረው የወያኔ ወታደራዊ አደረጃጀት ልንወጣ እና በሚሊተሪ ህግ ብቻ ልንመራ ይገባናል የሚሉ ናቸው ። መከላከያውን በብሐር ተዋፆ ሳይሆን በፍላጎታቸው በሚቀጠሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ልንገነባ ይገባናል ። ኮታ አያሥፈልገንም ።  የለኮታ በወጣው የቅጥር መሥፈርት ሁሉም  ወጣት በወታደራዊ አካዳሚ ውሥጥ በበቂ ሥልጠና አልፎ ለታላላቅ ማዕረግ መብቃት አለበት ። በጠንካራ ዲሲፕሊን የታነፀ መከላከያ ሠራዊት ሊኖረን ይገባል ። ዛሬ የሚሥተዋለው ግን  በመርህ ላይ የተመሠረተ አሠራር አይደለም ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቢይና ሽመልስ ኦሮሞን በቁም እየገደሉት ናቸው!! - ይነጋል በላቸው

የተረኝነት  አሠራር ነው ፤ በጉልህ በመከላከያ ከፍተኛ አመራር ውሥጥ የሚታየው  ። እንደ ወያኔ  ቁልፍ አመራሮችን ከአንድ ቋንቋ ተናጋሪ የማድረግ ነገር ይታያል ። ይኸው መረጃ ። 123..።  በፊደራል ፖሊሥም ሆነ በማረሚያ ቤት ውሥጥ ቁልፍ አመራሮችን ከአንድ ቋንቋ በማድረግ ተመሳሳይ ድርጊት ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ፈፅሟል ። መረጃ 123  ። …

ለእውነት  የቆመው ጋዜጠኛ ትላንት ወያኔ አሥሮኛል ። ብልፅግና ደግሞ ፀረ _ወያኔ በመሆኑ በጭፍን ላጨብጭብለት አላለም ። የብልፅግናንን ህፀፅ ለማሳየት በፍትህ መፅሔት ረጅም መንገድ ተጉዟል ። ሰው የሆኑትን ሹማምት ግብራቸውን ከሥማቸው ጋር አመሣክሮ ተችቷል ። ሂሰ አቅርቦባቸዋል ። ህዝቡ ከሚያውቀው እውነት ጨልፎ ላላወቀው ህዝብ አሣውቋል ። ይኽቺ አገር የጥቂት ግለሰቦች ሣትሆን የ115 ሚሊዮን ህዝብ እንደሆነች እንዲያውቁ አድርጓል ።

መንግሥት ይመጣል ። መንግሥት ይሄዳል ። አገዛዙ ወይም አሥተዳደሩ ፣ ደግም ይሁን ክፉ ፣ ማለፉ አይቀርም ። ሁሉም ኃላፊ ነው ። በሚያልፈው ህይወታቸው የማያልፍ አኩሪ ታሪክ የሚፅፉ የታደሉ ናቸው ።

ሞት አይቀርም ዛሬ በፖለቲከኞቻችን ድንቁርና አማራ ነኝ ። ትግሬ ነኝ ። ኦሮሞ ነኘ ። ወዘተ ። እያለ የሚገዳደለው ሰው  እጅግ አሣዛኝ ነው።   አሣፋሪም ነው ።   ሰውነትንም የረሳ ነው ።  ለጥቅም ባደሩ ፖለቲከኞች  ህሊናው ታውኮ  በጥድፊያ ለሞት ቢዳረግም ፣ ቢዘገይም  ሞት አይቀርለትም ። ህይወት እንደሆነች ለማንም አጭር ሆና ሣለ  ፤ በዚች አጭር ህይወት የኢትዮጵያ ሰው እንዳይደሰት፣ ህይወቱን በተቻለ መጠን አጣፍጦ ፣ ህይወትን አጣጥሞ እንዳያልፍ ፣ ዛሬ ወይ ነገ መሞታቸው የተረጋገጠ ፖለቲከኞች ፣ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ በንቃተ ህሊናው እና በሆዱ አየታገዙ በአጭሩ ይቀጩታል።  ይኽንን እውነት ተመሥገን ደሣለኝ በፍትህ መፅሔት በተለያየ ጊዜ ደጋግሞ ገልፆታል ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአራት ኪሎው አድባር - ተመስገን ደሳለኝ!

ዛሬ ፣ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም የተገለፀለት አንድ እውነት አለ ። ይኽም እውነት ሞት በህይወት ላለ ሰው ሁሉ በተራ መድረሱ ነው ። ኦሮሞ ሥለሆነ ፣ ትግሬ ሥለሆነ ፣አማራ ሥለሆነ ፤ ወይም ዶክተር ሥለሆነ ፤ ጠ/ሚ ሥለሆነ ፤ ፕሬዘዳንት ሥለሆነ ፤ ፓትርያርክ ሥለሆነ ወዘተ ። አይፈራውም ። ሞት ለማንም የማይቀር የሰው ሁሉ ዕጣ ፈንታ  ነው ። ምት ሰው አይመርጥም ። ከገደለም በኋላ በብሔሩ አይጠራውም ። አማራ ሞተ ። ትግሬ ሞተ ። ኦሮሞ ሞተ ። ወዘተ። ሞተ  አይልም ። ለሞት ሁሉም ሟች ፤ “ሬሣ ” ነው ። ሁሉም ሟች ” አሥከሬን ” ነው ። ነገ ሟች መሆኑን የዘነጋ ሰው ሁላ ለቀብር ተሰባስቦ ከሆሥፒታል ወይም  ከቤተክርስቲያን የሚመጣውን አሥከሬን  ” አሥከሬኑ አልመጣም እንዴ ? ” ብሎ ሲጠይቅ አልሰማህም እንዴ ? ከሞትክ የምትጠራው በአሥከሬን ነው ። ይኽም የወል ሥምህ ነው ። አዳሜ  !! ከወዲሁ ይኽንን ተረዳ ። ከመሞትህ በፊትም ከመቃብር በላይ ለሚውለው ሥምህ ተጨነቅ ።

5 Comments

  1. ጎበዝ ምን እየተደረገ ነው በዚች አገር ማንነው የሚመራን? ቱባ ቱባ የሚያህሉ የትግሬ ነብሰ ገዳዮችን ገድሎ እንዚህን ንጹህ ዜጎች አስሮ ማሰቃየት ምን ይሉታል? አሁን ስብሃት ነጋንና የህወአትን አመራሮች የፈታ በሰሜን ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮችን ያረዱ ነብሰ ገዳዮችን የፈታ ማንኛውንም ወንጀለኛ ለማሰር የሞራልና የህግ ስልጣንና ብቃት የለውም። ለነገሩ ትግሬዎችም ወዳችሁ ሳይሆን ፈርታችሁን ነው ያሉት እውነታቸውን ነው ይህ መንግስት በእጅጉ ተንቋል።
    ፖሊቲክኞች ጁዋር መሃመድ ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፤ስዩም ተሾም፤የኔ ሰው ምናምን፤ አቶ በቀለ ገርባ፤ አቶ መራራ ጉዲና

    ባለስልጣኖች ታከለ ኡማ፤ሺመልስ አብዲሳ፤አዳነች አቤቤ፤ቀጀላ መርዳሳ፤ አረጋዊ በርሄ፤ሽፈራው ሽጉጤ፤ሱሌማን ደደፎ፤ወርቅነህ ገበየሁ
    ቀጀላ መርዳሳ፤ሌንጮዎች፤አርከበ እቁባይ፤

    የፖሊቲካ ተንታኞች አንዳርጋቸው ጽጌ፤አረጋዊ በርሄ፤ስዩም ተሾመ
    እንዲህ እየተመረጡ ረብ የሌላቸው ሰዎች በስልጣን መቀመጣቸው ባጋጣሚ ሳይሆን ታስቦበት መሰለኝ።
    ፓስተር ታምራት ላይኔና፤ ያሬድ ጥበቡ፤ቴዎድሮስ ጸጋዬን እንኳን ስለነሱ እብደት ቃል ፍለጋ መቸገር አይገባም

  2. ስፍር፣ ቁጥር ፣ወደርና አቻ የማይኝላቸው የጭካኔና የአርመኔነት ስራወች እንዳሉ ሆነው አሁን በዚህች ሰአትና ደቂቃ ታላቁን የሀቅና የእውነት ተሟጋች አቶ ታዲዮስ ታቱንና ደፋሩን የእውነት ዘጋቢ ጋዜጠኛ ትመስገን ደሳለኝን አስራ የምታሰቃይ አገር በውስጧ ምክክር ተደረገ አልተደረገ ለቀሪወቹ ሚሊዮኖች ኢትዮጵያዊያን ቅንጣት ትርጉም አይሰጠንም፡፡ ሲጀመር በኦሮሙማ አውሬወችና በቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ መካከል የሰላም ምክክር ብሎ ነገር አይኖርም፡፡
    ወያኔ አንደሆነ አንዴዉኑ ለይቶለታል፡፤ ምን ጊዜም የማያገኛቸውን የአማራ ለም መሬቶችን ወልቃይትንና ራያን ከመመኘት ውጭ መንገዱን ጨርቅ ያድግለት ብለናል፡፤ ባቄላ ቀረ ቢሉ ፈስ ቀለለ ነው ነገሩ፡፡ ኖረውስ ምን ጠቀሙ??
    አብይ ከወያኔ ጋር እያደረገው ያለው ለህዝብ ይፋ ያልተደረገና ሁሉንም ያላካተተ ተንኮል የሞላበት ድርድር ሰላምን አያመጣም፡፡
    ሞት ለግብዞቹ ተረኞች ኦሮሙማወችና የእነርሱ ኮንድሞች ለሆኑት ለአማራ ሆዳም አሽከሮቻቸው፡፡
    ፍትህ ለታድዮስ ታቱ!! ፍትህ ለተመስገን ደሳለኝ!! ድል በኦሮሙማ መራሹ መንግስት የዘር እልቂት ታወጆበት በማለቅ ላይ ለሚገኘው የአማራ ህዝብ አለኝታ ለሆነው ለፋኖ!! እኔም ፋኖ ነኝ!!!

  3. ድንቁ እናመሰናለን እነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያን በጎሳ ሸንሽነው ይህ ግብዝ ህዝብ ሲነታረክ አገራቸውን የግላቸው ካምፓኒ አድርገው ህዝቡን ረሰተዋል ማን በዚህ መልኩ ነገርና አገርን አበለሻሹ ብሎ ዉክልና ሰጣቸው? ሽመልስ አብዲሳ፤ ያረጁ ያፈጁ የኦነግ ፖለቲከኞች፤አብይ አህመድ፤ታከለ ኡማ፤አዳነች አቤቤ፤ስራ ሰርቶ የማያውቀውን አረጋዊ በርሄና ብርሃኑ ነጋን እዚህ ታላቅ አገር ላይ የስራ ልምድ አድርጉ ብሎ በማይገባቸው ስልጣን ላይ አስቀምጦ ስራን ማበለሻሸት ምን ይባላል? የዚህ ተመሳሳዩ እነ አዳነች አቤቤን ኦፕሬሺን ትያትር ላይ በሽተኛን አስቀምጦ ቀዶ ጥገና አድርጉ ማለት ነው አገሪቱ ላይ የሆነውም ይኸው ነው፡፡ ለትግሬዎች 100 ቢሊዮን ብር ተልኮ እሱን አማራውን ወግተው ሲጨርሱ እንደገና በጀትና ድጎማ ተሰጣቸው አሁን ደግሞ ያወደሙትን መሰረት ልማት ከ ኢትዮጵያ እየተሰረቅ ሊሰጣቸው ነው ኧረ ጥጋብ በዛ ኢትዮጵያ ተወካይ አጣች? በትግሬዎች ዘመን ትግሬዎች ጥጋባቸው ሰማይ ነክቶ አሰብን ለኤርትራ ሲሰጡ ዛሬ ቀን አልፎ የኤርትራ ተደራዳሪዎች ደነገጥን ነበር ያሉት ስዩም መስፍን መቀሌ ድረስ ለሻቢያ ሰጥቶ በቴሌቭዥን ቀርቦ ደስ ይበለን ከጠበቅነው በላይ ተሰጠን ብሎ ሲያላግጥ ነበር፡፡ መቺ ነው የሚቆመው እንዲህ ያለ ትያትር ህዝቡስ እድሜ ልኩን ከሚቀለድበት ላንዴና ለመጨረሻ እንደ ሱዳን ህዝብ ወጥቶ በቃችሁ የማይለው?

  4. የእውነት አርበኞች አይዟችሁ ይህ ትውልድ እናንተን አሳስሮ ጫት የሚቅም ነው እንዲህ ሁኖ እንዲያስብ ትግሬዎች ሂፕኖታይዝድ አድርገውት ሂደዋል የውነት ቀን ግ ን እመጣል፡፡

  5. የእውነት አርበኞች አይዟችሁ ይህ ትውልድ እናንተን አሳስሮ ጫት የሚቅም ነው እንዲህ ሁኖ እንዲያስብ ትግሬዎች ሂፕኖታይዝድ አድርገውት ሂደዋል የውነት ቀን ግn እመጣል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share