July 31, 2022
1 min read

አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ!

Poem

እንደ ዋላ ውሀ እደጠማት
እንደራባት ጥም እንደያዛት

የሚያሳብቀው ገላዋ
ጎስቋላ ነው ስጋዋ

ይህቺ እማማ…..

አዲስ አቁማዳ ተሸክማ
አየኋት ማህሌት ቆማ

አዳዲስ ዜማ ስታዜም
ስትደረድር ስትገጥም

አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅልኝ
የወይን አረግ ጥመቅልኝ

እባክህ ውዴ ….

እንጀራዬን ልጋግረው ላስፋ
ፍለቅ እባክህ የኔ ተስፋ

ዳኘው ገበታየን
ጎብኘው ቃል ኪዳኔን

ብይኔን ክፈት ደጁን
የማይ መቅጃየን የምንጩን

ላጠጣ አብራኬን ላርካ
ልዘምርልህ እጄን እንካ

የምስጋና ነዶ ይዤ
እቅፍ ሙሉ አበባ አስይዤ

ከከፍታው ተራራ ላይ አወጣለሁ
ስእለቴን እከፍላለሁ

እያለች ማህሌት ይዛለችና
ክፈትላት እባክህ ራራና

አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅላት
ቆማለችና ተለመናት
እባክህን ፍለቅላት
ተገለጥማ እሺ በላት

እባክህን እባክህን
እባክህን እባክህን
እባክህን ብዬ ስልህ?

ሀምሌ፣ 2014

Geletaw Zeleke

Leave a Reply

Your email address will not be published.

296391382 3256164031292720 9019281170708453046 n
Previous Story

የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በየሰብአዊ እርዳታ በጫኑ ተሽከርካሪዎች ያልተፈቀደ ጥሬ ገንዘብ እና ቁሳቁሶችን የማስተላለፍ ተግባርን በጽኑ አወገዘ

Alshebab
Next Story

የአልሸባብ የጥቃት ሙከራ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን  ለቀጠናውና ለምእራቡ አለምም የማስጠንቀቂያ ደወልነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop