July 17, 2022
3 mins read

ታምራት ቶላ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮንሺፕ የወንዶች ማራቶን ክብረ-ወሰንን ሰበረ

01460000 0aff 0242 6889 08da681808ff w1023 r1 s
01460000 0aff 0242 6889 08da681808ff w1023 r1 s
በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮንሺፕ የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያዊው ታምራት ቶላ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሲሆን ። የሀገሩ ልጅ ሞስነት ገረመው የብር ፣ ቤልጂየምን የወከለው ባሺር አብዲ ደግሞ የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት ሆነዋል።

በዩናይትድ ስቴትስ ኦሪገን ኢዩጂን እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮንሺፕ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ በታምራት ቶላ አማካኝነት አግኝታለች ።

አመሻሹን በተደረገው የወንዶች ማራቶን ውድድር ባለ ድል የሆነው ታምራት ከበርሊኑ ቻምፒዮንሺፕ ወዲህ በኬንያዊው አቤል ኪሩይ ለ13 ዓመታት ያህል ተይዞ የቆየውን የርቀቱን የቻምፒዮንሺፕ ክብረወሰን አሻሽሏል።

ውድድሩ ሊጠናቀቅ 10 ኪሎሜትሮች ገደማ ሲቀረው ጀምሮ ከተፎካካሪዎች ተነጥሎ ወደፊት የገሰገሰው ታምራት ቶላ ውድድሩን በ2 ሰዓት ከ 5 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ በድል አጠናቋል።ይህ ሰዓት አቤል ኪሩይ ከገባበት ሰዓት ከ ደቂቃ በላይ የፈጠነ ነው።አቤል በቲዊተር ገጹ በኩል ” ከ13 ዓመታት በኃላ ክብረወሰኔ በዛሬው ዕለት ተሰብሯል !” በማለት ለታምራት የእንኳን ደስ ያለህ መልዕክቱን አስተላልፏል ።ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሞስነት ገረመው በአንድ ደቂቃ ከስምንት ሰከንድ ዘግይቶ በመግባት የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ሆኗል። ቤልጂየምን የወከለው ትውልደ-ሶማሊያዊው በሺር አብዲ በበኩሉ 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ49 ሰከንድ በሆነ ሰዓት 42 ኪሎ ሜትር ማካለል የሚጠይቀውን ውድድር በማጠናቀቅ የነሃስ ሜዳሊያ ተሸላሚ መሆኗኑን አረጋግጧል።

ከዛሬው የወንዶች ማራቶን ድል በፊት ፣ በትናንትናው ዕለት በተደረገው የሴቶች 10ሺ ሜትሮች ውድድር በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች እልህ አስጨራሽ ፉክክር ያደረገችው ለተሰንበት ግደይ የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስመዝግባለች ።

VOA

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Ethiopia 1
Previous Story

ኦርማኒያ እስከ ኦሮሚያ፣ ደረጀ ተፈራ (የግል ምልከታ)

175235
Next Story

የአዲሳባ ዙሪያ ጉዳይ የደህንነቱ ሹም ማስጠንቀቂያ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop