ይህ ከአዲስ አበባ 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሙከ ጡሪ ውጫሌ ወረዳ ሰሜን ሸዋ ዞን ነው። ሸኔ አማራን ለማፅዳት በአብይ አህመድ የተመሰረተ ጦር

ይህ ከአዲስ አበባ 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው #ሙከ_ጡሪ ውጫሌ ወረዳ ሰሜን ሸዋ ዞን ነው። ሸኔ አማራን ለማፅዳት በአብይ አህመድ የተመሰረተ ጦር ነው የምንለው ያለ ምክንያት አይደለም።

ፈለገ ግዮን

 

“የአማራ ህዝብ በክንዱ፣ በትግሉ ሰብዓዊ ክብሩን እንደሚያስመልስ ቅንጣት ያህል አልጠራጠርም” – መስከረም አበራ

አካሌ ከእስር ሲፈታ አእምሮዬ የሚያስበውን የምፅፍባቸው “Devices” (ስልኬ፣ Lap topዬ ) ከእስር አልተፈቱም። አካውንቶቼ ሁሉ ይበጃል ብዬ ባደረግኩት “Two step verification adjustment” ምክንያት ስልኬ እጄ ላይ ሳይኖር አካውንቶቼን መክፈት አልቻልኩም። ስለሆነም ታስሬ በነበረበት ወቅት እኔንም፣ የጨቅላ አራስ ልጄንም፣የቤተሰቤንም ጩኸት ለጮሃችሁልኝ ውዶቼ ምስጋና ማቅረብ እንኳን አልቻልኩም። ዛሬ ግን የባሰው ስለመጣ በባለቤቴ አካውንት መጣሁ
ከቅርብ አመታት ወዲህ እየተባባሰ የመጣው የአማራ ህዝብ የሰቆቃ ኑሮና የውርደት ሞት አእምሮዬን ሰቅዞ ስለያዘኝ የገባሁበት የትግል መስመር በዛሬይቱ ኢትዮጵያ እጅግ አደገኛው መስመር እንደሆነ ጠንቅቄ እረዳለሁና እስሩ ብዙ አላስገረመኝም፤ የዚህ ህዝብ አሰቃቂ ሞት እስኪያበቃ ድረስ ልሄድበት ለራሴ ከማልኩት ጉዞም የሚያስተጓጉለኝ አይሆንም – እንደውም ይበልጥ ያበረታኝ ይሆናል እንጅ!
ገና ከእስር ከመፈታቴ የጠበቀኝ በአሰቃቂነቱ ዓለምን ሁሉ ያነጋገረ የመከረኛው የአማራ ህዝብ ሞት ነው። ይህ የአማራ ህዝብ እልቂት ዛሬ የተጀመረ ይመስል ዓለምን ሁሉ ገና ዛሬ ማነጋገሩ ልክ ባይሆንም አውቆ የተኛ በተነሳ ሰዓትም ቢሆን የህዝባችንን መከራ ተረድቼ አዘንኩ ማለቱ የዓማራን ህዝብ የህልውና ትግል ያግዛል እንጅ ክፋት የለውም።ሆኖምየአማራ ህዝብ ለድፍን አራት አመት በር ተዘግቶበት ሲጨፈጨፍ አውቆ የተኛው ዓለም ዛሬ ለደረሰው ጭፍጨፋ አስተዋፅኦ እንዳለው መረሳት የለበትም።
የአማራ ህዝብ በትግሉ ሰብዓዊ ክብሩን ሲያስከብር ዓለም በሞቱ ላይ ጆሮውን ደፍኖ የኖረውን ዓለም ሁሉ በሩዋንዳው የዘር ፍጅት እንዳደረጉት ይቅርታ የሚጠይቁበት ዘመን ይመጣል።
እነዚህ ዘግይተው የነቁ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፣ ኢምበሲዎች፣ ታዋቂ ዲፕሎማቶች እንኳን ጭፍጨፋው በአማራ ህዝብ ላይ በማንነቱ ምክንያት የተደረገ ጭፍጨፋ እንደሆነ አስረግጠው ሲናገሩ በማከብረው ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የሚመራው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና ኢሰመጉ “የንፁሃን ዜጎች ሞት” ሲሉ ወንጀሉን ያድበሰበሱበት ምን ለማግኘት እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም! እንዲህ ያለው የ”Genocide”ን ወንጀል የማድበስበስ አደገኛ አካሄድ ዘር ማጥፋቱን የሚያግዝ ብሎም የሚያባብስ እንደሆነ ጠንቅቄ ስለማውቅ በእነዚህ ሁለት ተቋማት አካሄድ እጅግ ማዘኔን መግለፅ እወዳለሁ!!!! ኢዜማ፣ኦፌኮ ፣ኦህዴድ፣ኦነግ ስላወጡት መግለጫ ምንም ማለት አያስፈልገኝም!!!!!
ከገዳይ በላይ፣ ከጭፍጨፋው ሰቆቃ በበለጠ ለሞቱ የሚሰጠው ስም እና ትርጉም እንደሚያሳዝነኝ ግን ሳልገልፅ አላልፍም። ሃዘኔን የሚያበረታው እንዲህ ያሉ አስመሳይ አካሄዶች ወደፊትም ይህን መሰል ጭፍጨፋ እንዳይከሰት የሚያግዙ ስላልሆኑ ነው! ሰው በስንቱ ያዝናል?
በእውነት ለመናገር አሁን ላይ የሚሰማኝን ስሜት ለመግለፅ ይቸግረኛል። ውስጤ ያለቅሳል፣ ጥቅመ ቢስነት አጥንቴን ዘልቆ ይሰማኛል፣ በሃገሬ ፖለቲካ ሁለመና ቂም ለመቋጠር ከሚዳዳው ልቤ ጋር ሙግት እገጥማለሁ፣ ነፍሴ “ምን ይሻላልን?” በማሰላሰል ትቃትታለች……የአማራ ህዝብ በክንዱ፣በትግሉ ሰብዓዊ ክብሩን እንደሚያስመልስ ግን ቅንጣት ያህል አልጠራጠርም! ለዚህ ህዝብ የሚወጣ ቀን አለ።
ተጨማሪ ያንብቡ:  ይድረስ ለእነ "ብለን ነበር" በሙሉ! - ጥላሁን ፅጌ

4 Comments

  1. BEWARE ADDIS ABABANS,

    The massacre by the fascists is coming to your door. If you are not organized, be capable of denfending yourself and get ready today, not tomorrow, you will die, not in thousands as the case is in the land of the DEVIL-Wollo-ga, but in tens and hundereds of thousands.

    This massacre can be stopped by you, not be abiy amed or by Europeans or the USA.

  2. እንኳን ለቤትሽ አበቃሽ ምን ይባላል ቃላትም አእምሮ ሲሰባሰብ ነው ይህ አማራ የተባለ ህዝብ እውን ኢትዮጵያን በድሎ ነው ዝም ማለቱ በደሉን አምኖ የተቀበለ መስሏቸው ነው? አሳሪዎቹስ ይህ ሁሉ ነብስ በግፍ ሲጨፈጨፍ ቢያንስ ፈረንጅ የሰጣቸው ሃይማኖት ሰውን ለመስዋእት አቅርቡልኝ ብሎ ያዘዘበት አላየሁም፡፡ የኢሬቻና ዋቆ ፈታ በሰው ልጅ ደም ሃሴት ያድርጉ አያድርጉ የነገረን የለም፡፡ ስብሃት ነጋን ፈትቶ አንችንና አቶ ታዲዮስ ታንቱን ማሰር ምን ይሉታል? እግዚአብሄር ፍርዱን ይስጥ ምን አይነት እንቅልፍ ይተኙ ይሆን? በይ አምላክ ካንች ዘንድ ይሁን፡፡ በድኖች ውርደቱ አንገሺግሿቸው ከህዝባቸው ጎን ይቆማሉ ማለት ዘበት ነው ሺመልስ ሲገላምጣቸው የሚሆኑት ነው የሚጠፋቸው ኦፍ ሪኮርድም በጥፊ ሳይመታቸው አይቀርም፡፡ አበበባው፤ከፍያለው፤ደመቀ፤አገኘሁ አብይ ጭንቅላታቸውን እንደ ለማዳ ከብት ካሻሸላቸው ከዚያ በላይ ብዙም አይፈልጉም፡፡ የንጹሃን ደም ይፍረድ ኢትዮጵያን ላቆዩበት ዉለታቸው ይሄ ነው? ዛሬ አማራ በየድምበሩ አጥንቱን ባይከሰክስ ሃጎስም አልቤርቶ፤ቀጀላም ቢስማርክ፤ሌላውም ስሚዝ አብደላ ይሆን ነበር እራሱን ሁኖ እንዲኖር ያደረገው አማራው ነው በዚህ ብትለው በዚያ ሃቁ ከዚህ ፈቀቅ አይልም፡፡ ለሃገር አንድነት ብሎ እራሱን ባይበድል ሆዳሞቹን ከውስጡ ቢያጸዳ ዛሬ የኢትዮጵያ ፖሊቲካ ልዩ መልክ ይይዝ ነበር ዛሬም አልረፈደም፡፡

  3. My HEROINE, MESKI,
    I have no words to appreciate you enough. I simply say I WORSHIP you. Hopefully, soon, you will begin your NEKAT show and educate us on contemporary Ethiopian politics and how the Amhara people should save themselves from being SLAUGHTERED LIKE A CHICKEN at the land of the devil, WOLLO-ga, and elsewhere.

  4. ኦሮሞነትና ገዳይነት ልክ እንደ ወያኔ ባርነት ትግራይ በብልጽግና ድህነት እየተመራ ዘርና ቋንቋን ተገን አርጎ እልፎችን በመግደሉ የኦሮሞ ስም በአለም ዙሪያ በዘር ማጥፋት በየሚዲያው ሲናፈስ ይገኛል። ይህ ተግባር ሰፊውንና ጥሮ አዳሪውን የኦሮሞ ህዝብ ስም በጅምላ ጭቃ ቀብቶታል። ህጻናትና አዛውንቶችን እንደ አረም እየቆራረጠ የሚጥል ሰይጣናዊ ድርጅት እንዴት ባለ ሂሳብ የኦሮሞን ህዝብ ነጻ ሊያወጣ እንደሚችል እብድ ካልሆኑ በቀር መገመት አይቻልም። ግን እንደ መራራ ጉዲና፤ በቀለ ገርባ እና እድሜ ልክ በኦሮሞ ህዝብ ስም የሚነግድት አዛውንቶቹ የኦነግ መሪዎች አሁንም የዛሬ 60 ዓመት የቆሙበት እይታ ላይ ናቸው። የእልፍ አማራ ሞት ለእነርሱ ደንታቸው አይደለም። ለዚያ ነው የብልጽግና ድህነት ፓርቲው በተኛበት መሳሪያውን ግምጃ ቤት እንዲዘጋ ተደርጎ የሰሜን እዝ በትግራይ መሬት ደሙ የፈሰሰው። አልፎ ተርፎም ሽዋ ድረስ እንዲገባ ተፈቅዶለት እልፍ ሰቆቃና መከራ በአፋርና በአማራ ህዝብ ላይ ያደረሰውና በማድረስ ላይ ያለው። ፈቅዶ ሃገር እሆናለሁ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦል ድረስ እንገባለን እያሉ ከሚደነፉ ሃይሎች ጋር ለመደራደርና አልፎ ተርፎም እልፍ የጭነት መኪና በእርዳታ መልክ ወደ ትግራይ እንዲገባ ማድረጉ የወያኔን ሰራዊት እየመገበ እንደሆነ አይረዳውም። የትግራይ ህዝብ ይኸው 50 ዓመት ተጠጋው በእነዚህ አረሞዎች መከራውን ሲቆጥር።
    እነዚሁ ሃይሎችና የውጭ ደጋፊዎች ያስታጠቁት ኦነግ ሸኔ፤ ከወያኔ ጋር አብሮ በቤኒሻንጉል እንዲሁም በሃገሪቱ ልዪ ልዪ ስፍራዎች እሳት እያስጫሩና እያነደድ ሲያጋዪት መስማትና ማየት ምንኛ ሃገሪቱ መሪና ስርዓት አልባ እንደሆነች ይናገራል። በከተማ ሰው ይታፈናል፤ ክፈል ተብሎ ለማስለቀቅ ይከፍላል። የተከመረ የእህል ክምር ይጋያል፤ ድሃና መከታ የሌላቸው ምስኪኖች በጠራራ ጸሃይ ይዘረፋሉ፤ ይባረራሉ፤ ዳኛውም ፓሊሱም አብሮ ይዘርፋል ያዘርፋል። ሃገሪቱ ከወያኔ ዘመን ጀምሮ ሙት ብትሆንም የአሁን ግን ወደ መቀበር እያቀረባት ነው። የቤ/ክ ክምችት፤ የመስጊድ በየቦታው መቆም፤ የፕሮቴስታንት እምነት ቤ/ክ እንደ አሸን መፍላት የህዝባችን እይታና አብሮ ኗሪነትን አልሞሸረውም። ይባስ ብሎ አምጡ/ስጡ/እያለ በለለ ቤታቸው እጃቸው ላይ ያለችውን ትንሽ ነገር እንኳን ይነጥቃል እንጂ። አታድርስ ነው።
    የአማራ በየቦታው እየታደነ መገደል ሊገታው የሚችለው ተደራጅቶ ተናቦ ሰልጥኖ ታጥቆ እዚህም ቤት እሳት አለ ማለት ሲችል ብቻ ነው። መንግስት ይድረስልን፤ የአካባቢው ነዋሪዎች እርድን ማለቱ ሁሉ ዋጋ የለም። በወለጋ ተማሪዎች ሲጠለፉ እንዲጠለፉ ያደረጋቸው በእጅ ላይ ሞቫይል ስልክ የያዘውና ከኦነግ ጋር ግንኙነት ያለው የአውቶብሱ ትኬት ቆራጭ ነው። ሰው እንደ እንስሳ የሚያርድ የኦሮሞ ስብስብ ራሱንም እንኳን ነጥሎ ሃገር ልሁን ቢል እርስ በእራሱ መባላቱ አይቀሬ ነው። ግን ፓለቲከኛ ባይ ነን ለሚሉት ሃገር ለማየት፤ ሰው ጋ የተሰበሰበ ገንዘብን ለመዝረፍ፤ በዓረብ ሃገራትና በሌሎች እሳት አቀባይና መልሶ አልቃሽ ሃገሮች እየተደጎሙ ሳይሰሩ ይኖሩበታል። ለወለጋው እልቂት ማልቀስና ማንባት ያለበት የአማራ ህብረተሰብ ብቻ መሆን የለበትም። ሁሉ ነበረ እንጂ! ግን ማን ሞቷል የእነማን ዘር ነው ቋንቋው ምንድን ነው ተብሎ በሚለቀስባት የአፓርታይድ ኢትዮጵያ ሰው በሰውነቱ መመዘኑ ቀርቷል። እየመረጡ ማልቀስ፤ እየመረጡ መቅበር። አይ ሃገር የሙታን ጉባኤ የሰፈነባት። ሁሌ መግለጫ፤ ሁሌ ግርግር፤ ሁሌ ስብሰብ ፍሬ የለሽ የገለባ ክምር። ኦነግና ወያኔ ቀን መርጠውና አስልተውን ነው ግድያና ግርግር የሚፈጽሙት። ጠ/ሚሩ ፓርላማ ላይ ሲለፈልፍ እነርሱ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል እልፍ አማሮችን (ቀይ ቀዪችን ግደሉ) ተብሎ ዋና ከተማው ድረስ ዘልቀው አተራምሰውና ገድለው ተሰወሩ። አሁን እንደገና ጠ/ሚሩ ለችግኝ ተከላ ሲሮጥ ወለጋ ላይ ናዚያዊ የሆነ ጭፍጨፋ ተፈጸመ። ቀና ይቀጥላሉ። ሃገርን ለማፍረስ ሲኦል ድረስ እወርዳለሁ ከሚል ሙት ድርጅት ጋር የሰላም ድርድር ላርግ ከማለት ይልቅ ሃይልና ጉልበትን አደራጅቶ ወያኔን ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻ ጊዜ ከምድረ ገጽ ማጥፋት ሁሉንም እሳት ባያጠፋም ይበልጡን ያከስመዋል። አሁን ተይዞ ያለው ያዝ ለቀቅ ፓለቲካ ገና ብዙዎችን ያስበላል። የአማራም ሆነ የሌሎች ሰቆቃና መከራ የሚገታው ወያኔ ባርነት ትግራይ ሲከስም ብቻ ነው። ሰው አልነቃም። ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊያንን ከሃገሯ ያባረረቸው በግብጽና በወያኔ ተላላኪዎች ተገፍታ ነው። ዝም ብሎ የሆነ ነገር አይደለም። አንድ የሳውዲ ባለስልጣን ትግሬ ነህ አማራ ኦሮሞ ነህ ምን ብሎ ሲጠይቅ ምን ያህል ፓለቲካው እንደ ተወላገደ ያሳያል። ሳውዲ የደም መሬት ናት። በቱርክ አሜሪካ ውስጥ ተጠልሎ የሚኖረውን ጋዜጠኛ በመጋዝ የሰነጣጠኩት ገዳይ የሳውዲ ሃይሎች አሁን ዙረው ተመልሰው ከቱርክ ጋር ቂጥ ገጥመዋል። ለዛ ነበር የሳውዲው ትራንፕ አንካራ በቅርብ የተገኘው። የሚገርመው ግን የዓለም የፓለቲካ አስራር ይበልጡ ይመሳሰላል። ወያኔ ለጄ/ሃይሎም የሆለታ ጦር ት/ቤትን በስሙ የሰየመለት ካስገደለው በህዋላ ነበር። ይኸው እንሆ ሳውዲም በቢለዋ ለቆራረጡት ጋዜጠኛ በሃገራቸው በስሙ መንገድ ሰይመውለታል። አታድርስ ነው። በማይካድራ የሰው አንገት የቆረጡት በሱዳንና በግብጽ ሰልጥነው ተመልሰው ውጊያ ገብተው ሁሉም ባይሆኑ ይበልጡ አልቀዋል። ይህ ነው የመገዳደል ዥዋዥዌ፤ ገድዬ እኖራለሁ ስትል ሌላው ይቀነጥስሃል። ባጭሩ ዋይታና ለቅሶህን ትተህ በህቡዕም ሆነ በይፋ ተደራጅ። ጄ/ አሳምነው ጽጌ ተናግሮ ነበር። ” አማራ ተከቧል” ጭንቅ ውስጥ ነው። አሁን ማን ይሙት ወያኔ ተመልሶ ወረራ አያረግም ሽዋ ድረስ አይገባም ብሎ ማመን ይቻላል? አይቻልም። ግን እንደ በግ እየተጎተቱ ከመሞት ተከላክሎ መሞት ተገቢ ነው። ወያኔ የነዳጅ እጥረት የሚለው ለውጊያው ዝግጅት እንጂ ለትግራይ ህዝብ አስቦ አይደለም። የቀበረው መሳሪያም ሆነ ነዳጅ አልቆበታል። የሰሜን እዝ ዳግም ተደራጅቶ መቀሌ ከገባ በህዋላ በወያኔ እየተላኩ በርበሬና ሚጥሚጣ ከዚያም ወታደሩን መንገድ ልምራችሁ እያሉ ያስጨረሷቸው የትግራይ ልጆች አሁን ምን ይሉ ይሆን በወያኔ መከራና ሰቆቃ? የኢትዮጵያ ችግር ወያኔ ነው። ሌላው ሁሉ እንዘጥ እንዘጥ ባይ የወያኔ ተላላኪ እንጂ በራሱ የቆመ ሃይል አይደለም። የሃገሪቱ መከራ የሚመነጨው ከትግራይ ምድር ነው። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share