ጠላት ባርነት እና ድህንነት እንጂ ነፃነት እና ዕድገት አያስገኝም

የኢትዮጵያ ቋሚ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያዊነት እና ኢትዮጵያ የጥላቻ መነሻ እና መድረሻ ማድረጋቸዉ  የሚገርም ነዉ ፡፡

የሚያሳዝነዉ ግን የክፋታቸዉን ክርፋት እና ጥቃት ለብሄራዊ ዉድቀት እና ሞት  የደስታቸዉ  ምንጭ ሆኖ ቀጥሏል ፡፡

ትናንት ኤርትራ ከእናት አገር እንዳትለይ እና ሁለቱም ህዝቦች ከጥላቻ ይልቅ የፍቅር አቻ ፤ከመለያየት አንድነት ቢከተሉ መልካም መሆኑን ህዝብ ቢናገሩም ሰሚ አጥተዉ  የኤርትራን ኢትዮጵያዊነት የሚሻ መንገዱን ጨርቅ አሉን …አለን የኢትዮጵያ እና ህዝቦች ጠላት የነበሩ ፤ያሉ እና የነበር፡፡

ኢትዮጵያ የብዙኃን አገር  የባህር በር ማጣት የለባትም ቢያምስ አሰብ ሲባል ፉፁም ፀረ  ኢትዮጵያ እና ህዝቦች  አሰብን መርቆ  የግመል መፈንጫ ነዉ  በሚል የኢትዮጵያን ጉዳይ  ለሞኝ ያብቃችሁ ብሏል የእኛዉ  አሊባባ  መሪ የነበረዉ ፡፡

ቀጠለ እና በሴራ የበሬ ግንባር በማትኃል  አንድ አይዉል ባድሜ  ላይ የሴራ ፖለቲካ  ለማስቀጠል ሲባል በኢትዮጵያ ታሪክ ሆኖ ማይታወቅ  የዜጎች ሞት ይህም ከሰባ ሽ  አስከ መቶ ሽ በአንድ ዓመት የወንድማማቾች ሞት እና ዕልቂት ምክነያት ሆኗል ፡፡

ይህ በነበረበት  ሁነት ከአራ ዘጠኝ መቶ ሠባዎች ጀምሮ አስከ ዛሬ በጉልበት እና በማን አለበኝነት በዉስጥ እና ዉጭ ኢትዮጵያ ጠላቶች ለእነርሱ ትልቅ ለኢትዮጵያ እና ለዓማራ ህዝብ ምንም የሚሉትን የወልቃይት ፣ራዕያ እና መተከል  ምንም ያልሆነ እንዲያዉም የብቀላ መሳሪያ በማድረግ ቀጥለዉበታል፡፡

የሀምሌ ፭ ቀን ሁለት ሽ ስምንት ዓመተ ምህረት የማንነት እና የህልዉና ንቅናቄ  ግለት ለማዳፈን ጥልቅ ተሀድሶ በሚል ሰበብ  በሁለት ሽ ዘጠኝ  ክረምት ወራት መጨረሻ ጥልቅ ተሀድሶ ስም የማዕከላዊ  እና አዲስ አበባ ቅጥር ሠራተኞች ጋር ከፍተኛ ግብግብ የነበረበት የሁለት ሳምንት ስብሰባ ሲካሄድ የማንነት እና የድንበር ወሰን ጥያቄ  ቅወቧል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የባህልና የእምነት ጣራ ሲያፈስ ክህደት፣ ቅጥፈንትና ሌብነት እንደ ዶፍ ሳያቋርጥ ይወርዳል!

ትናንት የነበሩት እና ዛሬም ኢትዮጵያ ጠል ፖለቲከኞች  እንደዛሬዉ ያኔ  ጎንደር ሲባል  ጎንደር ለሀረር ምኑ ነዉ ሲሉ ፤ ወልቃይት ፣ራያ እና መተከል የሞት ቀጠና የመሆናቸዉ የፍትህ እና የህልዉና ጉፋይ ሲባሉ  የሚሰጡት መልስ ኢትዮጵያዊነት እና ህዝባዊነት የጎደለዉ የምን አገባኝ እና ምን አለብኝ የድፈረት እና የንቀት ምላሽ ነበር ፡፡

ይህ አልበቃ ብሎ ዛሬም በታሪክ በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የደረሰዉን ዉርደት ፣ ጥቃት ፣ስደት እና ሞት ለኢትዮጵያ ጠሎች የስልጣን ጊዜ ማራዘሚያ የሚደረግ ገፀ በረከት የሆነ አስከሚመስላቸዉ በኢትዮጵያ ህዝብ መቃብር ላይ ይፏልላሉ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ በማንነቱ(ኢትዮጵያዊነት)  ከሶስት አስርተ ዓመታት በላይ የደረሰበትን እና እየደረሰበት ያለዉን ሁለንተናዊ ጀምላ መገለል እና መገደል እያሳነሱ  በህዝብ ቁስል  መርዝ የሚነሰንሱ ትናንት በጎጃም ጉዳይ ጎንደር ፤ በኢትዮጵያ ጉዳይ ኢትዮጵያዊ አያገባዉም ባዮች ዛሬ በህዝብ ነፃነት እና ማንነት ተጋድሎ ቢያላግጡ ምን ይገርማል፡፡

የሚገርመዉስ ትናንት አገር እና ህዝብ ክደናል ፤ በጥቅም እና በከንቱ ዉዳሴ የአገራችንን ጥቅም አሳልፈን ሰጥተናል ብለዉ ተፀፅተዉ ይቅር ብለዉ ካሳ ለመክፈል ከህዝብ ፊት ሲንበረከከኩ ነበር ፡፡

በዓማራ እና የኢትዮጵያ የዘመናት የማንነት እና ሉዓላዊነት ጥያቄ ላይ ትናንት ኤርትራን፣ የባህር በር፣ የኢትዮ-ሱዳን ድንበርን፣ የዓማራ ህዝብ የህዝብ ጠላት በማለት ኢትዮጵያዊ መሰርት ለማናጋት ከዚያ አስከ ዛሬ ተግተዉ ከሚሰሩት በጥላቻ እና በከንቱ አቻ በሽታ ከሚሰቃዩት  ፍትህ መጠየቅ ታሪክን እና የኋላ ማንነትን አለማወቅ ነዉ ፡፡

የሚያሳዝነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ዓማራ የህልዉና ፣ የማንነት ፣ የግዛት አንድነት እና የግለሰብ ነፃነት አስቀድሞ ከታሪክ እና ከህግ ማዕቀፍ ዉጭ ጥላቻ እና የበታችነት ትብታብ በወረሰዉ ዱለታ/ሴራ በቁሙ ገድለዉ ከቀሙት ዛሬም ነፃነት ማለቱ ነዉ ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ልማታዊ ፓትርያርክ (ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ)

ነፃነት በዉሳኔ ለዚያዉም ከጠላት ሳይሆን በህብረት እና በፅኑ ዓላማ ማስተዋል ባለበት ኃይል እና ኃይል ነዉ ፡፡

ለዚህም ነዉ አንድነት ኃይል ነዉ ኃይልም የጠላት መንበርከኪያ አለት ነዉ ፡፡ የኃይል ሚዛን ሲያጋድል ጠላት ቀርቶ ወዳጂ ጠላት ሊሆን ይንሸራተታል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በህይወት ቤዛ፣ በአጥንት ክስካሽ ፤ በደም ፍሳሽ  በጎንደር እና ወሎ የተገኘዉን  የነፃነት ጭላንጭል ዕዉቀና፣ የስራ ማስኪያጃ ገንዘብ…….ብሎ ርምጃን መግታት ወደፊት የሚደረገዉን የህልዉና እና ዕድገት ጉዞ ለአፍታም ሊያዘናጋ አይገባም ፡፡

የማንኛዉም ሀብት ምንጭ ህዝብ ነዉ በመደበኛ ሆነ በሌላ መንገድ ከግብር ፣ቀረጥ…የሚገኝ የአንድ አገር ወይም አካባቢ ገንዘብ ምንጭ ህዝብ አስከ ሆነ በተለይም እንደ ወልቃይት እና ራያ አካባቢ ያሉትን  ለማልማት ከሌላ አካል መጠበቅ የተገኘዉን ነፃነት መፋቅ ነዉ ፡፡

እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ በቀን አምስት ብር ለዕድገት ቢመድብ ኢትዮጵያን አይደለም አፍሪካን መለወጥ ይቻላል፡፡

እኮ እንዴት ነዉ ጎመን ከዉጭ የምታስገባ ኢትዮጵያ ሁመራ ፣ራያ፣ መተከል…..የመሳሰሉ ጠፍ መሬት በበጀት መኖር ፤አለመኖር እየተባለ ጦም ማደር ለማን ይበጂ ይሆን ፡፡

አገር የሚለማዉ በሰዉ ለዚያዉም በራሱ ዜጎች እንጂ በጠላትም ሆነ ጠላትነቱ በማይነገር ወዳጂ ፤ጎረቤት አለመሆኑን አዉቀን ለረሳችን ህልዉና እና ዕድገት እንደ ሰንሰል ተጋምደን ለእኛ እና እኛ ዘብ እንቁም፡፡

ኢትዮጵያን መስርተዉ ሰርተዉ ያቆዩን ኢትዮጵያዉያን እንጂ ጠላትም ሆነ መንግስታት አልነበሩም ፤አይደሉም ፡፡

እናም እኛ እንደ ህዝብ ከባርነት እና ድህነት ቀንበር ጫንቃችን የሚላቀቀዉ በህብረት እና አንድነት መስራት እንጂ ለህልዉና ጠንቅ ከሆኑ ጠላቶች ነፃነት መጠበቅ የጥልቅ ድንቁርና ቁራኛነት ነዉ ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ አንድ - ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

የየትኛዉም አገር እና ህዝብ የዕድገት እና ስልጣኔ ምንጭ ህዝብ ብቻ ነዉ ፡፡ 

አንድነት ኃይል ነዉ

ማላጂ

 

3 Comments

  1. እንኳን አሁን የዓለም የኢኮኖሚና የፍልሰት ስሪት ባጠላለፈን ጊዜ ድሮም ቢሆን አንዲት ሃገር ለብቻዋ ቆማ አታውቅም። እህሉ ቀርቶ ጥይት እየተሰፈረ በሚሸጥባት ሃገራችን ጠላቶችም ወዳጅ መሳዪችም ያኔም ነበሩ አሁንም አሉ። ሆን ተብሎ ኢትዮጵያ ለዘንተ ዓለም እንድትተራመስ ነበር ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ ያለ ውዴታ እንድትጠቃለል የተደረገው። የእኛ ለ 30 ዓመት በተውሶ መሳሪያ መገዳደል ለነጩ እና ለዓረቡ ዓለም እፎይታ ነበር። ነጩ አለም ለጥቁሩ ዓለም ክፋትና ተንኮል ከማሰብ ተኝቶ አያውቅም። የዚህ ከፋታቸው ከፍታ ጎልቶ የሚታየው በወያኔ (ባርነት) ትግራይ ነው። ያሰለጠኑት፤ ያስታጠቁት፤ በአለም መድረክ ቆመው የሚሟገቱለት ወያኔ ለህዝብ መብት ስለቆመ አይደለም። የእነርሱ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ስለሆነ እንጂ። ባመዛኙ የኤርትራውን የእድሜ ልክ መሪ ሳጥናኤል አድርገው የሚስሉት በራሱ እይታና አስተሳሰብ ስለሚራመድ ነው። በመሰረቱ በክፋት ወያኔና ሻቢያ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ናቸው።
    ወያኔ የእብደት ጦርነት በሰሜን እዝ ላይ ፈጽሞ እልፍ ሰዎች ካለቁ በህዋላ አሁን በትግራይ ውስጥ የሚፈጽመው በደል በየቀኑ በመባባስ ላይ ይገኛል። ከወያኔ ፍርፋሪ ለቃሚዎቹን የትግራይ ልጆች እንተዋቸውና ለእውነት ለትግራይ ህዝብ ቆመናል የሚሉ ድምጻቸውን የሚያሰሙበት ጊዜው አሁን ነው። ቁጥራቸው የበዛ የእርዳታ ድርጅቶች ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ። ጥቂቶች ለትግራይ ህዝብ የሚቆረቆሩ ሲሆኑ የሚበልጡት በስለላ፤ በወደፊት እድል ፈንታ (የተመለከቱትና ያዪትን) በመጽሃፍ መልክ፤ በፊልም፤ በልዪ ልዪ ሁኔታ ያወጡትና ይከፈላቸዋል። ለእነርሱ የመዝናኛ ጊዜ ነው። እንደ ሰፊው ህዝብ አይራቡ። አይታሰሩ። የሚያሳዝነው ግን ሁሌም በደል ተሰራ፤ ይህን አየን፤ ያን ሰማን በማለት የሚያስታውቁን ጊዜው ካለፈበትና እልፎች አፈር ከለበሱ በህዋላ በመሆኑ ዋጋ ቢስ ነው።
    እግሩና እጅ የተቆረጠ፤ ዓይኑ የጠፋ፤ በክራንቻ ያደለው ደግሞ በዊልቸር የሚሄድ ወጣቶችን በትግራይ ማየት የተለመደ ሆኗል። የሞተውን ማን ይቁጠረው? ጥያቄው መሆን ያለበት ይህ ሁሉ የዘመናት ሞትና እልቂት ለምንና ለማን ብለው የሚጠይቁ የትግራይ ልጆች ተለቅመው ይታሰራሉ፤ ይሰወራሉ። ልብ ያለው የትግራይ ልጅ የያዘውን መሳሪያ መሪህ ነን በሚሉት ላይ ማንሳት ይገባዋል። እንዴት ሃገር በጥቂት የፓለቲካ ወስላቶች ትጠፋለች? አውሮፓና አሜሪካ ተቀምጠው የትግራይ ወጣቶች በጦርነት እንዲማገድ በሃሳብም ሆነ በቁሳቁስ የሚረድ ሁሉ ጉልበትና ያላቸውን አስተባብረው በተለያዪ መጠለያዎች ከትግራይ ውጭ ያሉ የትግራይ ተወላጆችን ቢረድ በእጅጉ ይመረጣል። ወያኔ የተላከ መድሃኒት አዲስ ፋርማሲ ከፍቶ መቀሌ ላይ በመሸጥ ይገኛል። በእርዳታ የተላከ እህል ሰው አዋጡ እያሉ ህዝቡን በማዋከብ 15 ኪ.ግ እህል ይሰጡና ይህን ያህል እንጀራ ለሰራዊቱ ጋግራችሁ አምጡ ይባላል። እየሰጡ መቀማት ይሉሃል ይሄ ነው። እነርሱ በውስኪ ይራጫሉ። አሁን ጌታቸው ረዳን ያየ ትግራይ ውስጥ ሰው ይራባል ብሎ ያምናል። ያለ ልክ ወፍሯል። እንዲህ ነው ለራስ ሲቆርሱ። ባጭሩ ገና ከጅምሩ ጀምሮ ወያኔ ለትግራይ ህዝብ የቆመ ድርጅት አይደለም። ለራሱና በዙሪያው ላሉት እንጂ። ይኸው እንሆ ከዘመናት በህዋላ ዛሬም ያው ሴራቸውና ክፋታቸው አለቀቃቸውም። የትግራይ ህዝብ ሆ ብሎ ቢነሳ እነርሱ እንኳን ትግራይ ላይ ቀርቶ በዓለም ላይ መኖሪያ አይኖራቸውም። ግን እየፈሩ ነጻነትን መሻት አያቻልም። የአዲስ አበባው መንግስት ገብቶ ነገሮችን እንዲያስተካክል የሚጠይቁ ሁሉ ጅሎች ናቸው። ነውጥ ከውስጥ እንጂ ከውጭ አይመጣም። ወያኔን ከትግራይ ህዝብ ጀርባ ላይ የሚያሽቀነጥረው የትግራይ ልጆች ብቻ ናቸው። ሌላው ደጋፊና ዘብ ቋሚ ሊሆን ይችላል። እርግጥ ነው ወያኔ ኢትዮጵያዊነትን ይጠላል። ለዚያም ነው የአፓርታይድ ክልል አሰራርን የመሰረተው። ግን ይህ ሁሉ የልጆች ጫዋታ፤ የአደረ እንጀራ ቁርስርስ የሚሆንበት ጊዜ ቀርቧል። ወያኔ የሰሜንን ጦር አጥቅቶ፤ ቆይቶም በብልጽግና የፓለቲካ ሻጥር ሽዋ ድረስ ዘርፎና ገድሎ መቀሌ ተመልሶ ሲቀረቀር ያተረፈው ማን ነው? መልሱ ማንም ነው። የደንቆሮ ለቅሶ መልሶ መላልሶ ይሉሃል እንዲህ አይነቱን የፓለቲካ ውስልትና ነው። ዳግመኛ ለመዝመት ወያኔ ሰዎች እየመለመለ፤ እያስታጠቀ እንደሆነ የአይን እማኖች ነገረውኛል። በባህሪው ወያኔ ያለ መገዳደልና መግደል መኖር ስለማይችል ገና እልፍ የትግራይ ልጆችን ያስጨርሳል፤ ምድሪቱንም ባዶ ያደርጋል። ወያኔ ማለት አረመኔ፤ የሰው ባህሪ የሌለው፤ ከራሱ ውጭ የሌላው ሞትና ቁስል የማይሰማው የፓለቲካ ውሾች ስብስብ ነው። በየስርቻው ሆነህ በስመ ትግራይ ወያኔን የምትደግፍ ሁሉ ሂድና ተመልከቱ። እግዚኦ አታድርስ በማለት መፈጠራችሁን ጠልታችሁ ትመለሳላችሁ። በቃኝ!

  2. ተስፋ የትግሬ ነገር አጥንትህን ዘልቆ ገብቷል ትግሬ ሌሎች ላይ ያደረሰው ባንተ ምዘና ብዙም ክብደት ያገኘ አይመስልም በጽሁፍህ የችግሩ ምንጭ ህወአት እንደሆነ ገልጸሀል በዚህ ብዙዎች አይስማሙም ህወአት ማለት ትግሬ ነው ትግሬ ማለት ወያኔ ነው። በእርግጠኝነት ፲ ኢትዮጵያዊ የሆነ ትግሬ አትጠራም ህወአታዊ እንጅ ። የአካባቢው ተወላጅ ትመስላለህ አንድ እግርህ እዛው ነው አንደኛው ደግሞ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት የሚሰጠውን ጥቅም የተረዳህ ይመስላል እንግዲህ ለትግሬዎች ልብ ይስጥልን ማለት ነው እንጅ ምን ይባላል? ከሀገር ቤት ርቆ በውጭ የሚገኘው ትግሬ የኢትዮጵያ ወታደር እሱን ሊጠብቀው የሄደ በትግሬዎች ሲታረድ ማውገዝ እንዴት ከበደው? አሁንማ የሀገሪቱም መሪ ሳይረሳቸው አልቀረም። እንግዲህ አንተም ጫር እኛም እንመረምራለን።

    • ወገኔ ከመስመሩ እንደ ወጣ ባቡር እይታየን ስተህ ትግሬ ትግሬ በማለት ገደል በመግባት ላይ ትገኛለህ። የትግሬ፤ የኦሮሞ፤ የአማራ የሌሎችም ወገኖቻችን የጅምላ ጥላቻ ለአንተም ለሃገራችንም የወደፊት እርምጃ አይጠቅምም። የችግራችን ሁሉ ጦስ እኔም አንተም ሁላችንም ነን። ወያኔና መሰሎቹ የፈጸሙትንና በመፈጸም ላይ ያሉትን በይፋ ስለሚያደርጉት ለአይናችን የተሰወረ አይደለም። ግን እንደ አንተና እንደመሰሎችህ ወደ 3.5 ሚሊዪን የሚጠጋ የትግራይን ህዝብ አንድ ሙቀጫ ውስጥ ከትቼ አልወቅጥም። የትግራይ ህዝብ ፈጸመ የምትለውን ግፍ ተገዶ እንደሚያደርገው ይገባሃል? ምርጫ ባልተሰጠው ህዝብ ላይ መደንፋት በእውነት ላይ ማቀርሸት ነው። ችግራችን ፓለቲካችን ሁሉ የዘርና የቋንቋ ፓለቲካ መሆኑ ነው። የአንተም ሰልፍ በዚሁ የተሰመረ በመሆኑ የጋራ የሆኑ እሴቶችን አይቶ፤ እኔ ማን ነኝ ብሎ አይጠይቅም። ሌላውን በደፈና ይኮንናል እንጂ። አርፈህ ተቀመጥ። እሳት የሚያቀጣጥል መቼ በምድሪቱ ላይ አጣን፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share