April 17, 2022
2 mins read

ከርሞን ማየት (በላቸው ገላሁን)

Poemዛሬስ ምነው በዛ
እንጀራ፤ ዳቦ ድስቴ ጠነዛ
ልጆቼም ገልቱ ሆኑ ተረገሙ
ልሳን ድምጼንም አይሰሙ
ተጠላልተው፤ተገፋፍተው፤ ተናንቀው___እየተማሙ
በግብር በሃሳብ ገለሙ።

ገና ከማህጸን ሲወጡ ባርኬ
ቀለም ልቀሙ ብዬ አስኩዋላ ልኬ
ይገባቸው እንደሁ ጠልቆ
ያረቅቃቸው እንደሁ አምጥቆ
ያኖራቸው እንደሁ አስታርቆ
ከረሃብ፣ ከመከራ፣ ከድንቁርና፣ከእርዛት፣ ከስደት አላቆ፤

ግና!
ማን በረዘብኝ ቀለሙን
የጥበብ፣ የማስተዋል ጅረቱን
የሚያሳየውን ገላልጦ
ከጠዋት ጠሃይ ቱግታ አብልጦ፤
የአንድነት የፍቅር ብርታቱን
የታሪክ የባሀል ጥልቀቱን
የሃሳብ የምናብ ምጥቀቱን
የመኖርና ሰው የመሆን ር_ቀቱን።

ዋ!
ከንቱዎቼ ቀልባቸው ሆኖ ሆ! ና ዋ! ላይ
ሌላ ሆሄያትን የማይለይ የማያይ
የለቀሙት ተአስኩዋላው ተመላልስው
ገረጣ፣ ከሰረና መከነ እውቀታቸው
ሆነ ከንቱ አልባሌ
ለእኩይ ምግባር ገባ ሎሌ
እያወጀ እኔ ለእኔ
እያሰኘ
“አትቅረበኝ” ራቅ ከጎኔ፤
ተፈርጆ አጥርን ሰራ
ባጀ ተባ፣
ለጦርነት ለአተካራ
ዋ!
ባይገባው ነው በአንክሮ
ከጥንት አንስቶ ከድሮ
ቀለምን ሲያውቁ መርምሮ
ህይወት ሲገፉ ተባብሮ
ነው መድህኒቱ ለህይወት
ነግ ተነግ ወድያ ከርሞን ለማየት።

በላቸው ገላሁን
ሚያዝያ ፰ ፳፻፲፬ ዓ. ም.
U.S.A

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Abiy 3
Previous Story

የፅንፈኛ ኦሮሞዎች ማንነትንና ውሽት – አቻምየለህ ታምሩ

Mekonen
Next Story

መሥቀልኛ መንገድ ላይ ነን፡፡ ” የቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ ፡፡” – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop