ከሕዝብ ጉያ ሳታወጣ- ሰለባህን አትቅጣ – አሳዬ ደርቤ

የትኛውም የብአዴን አመራር ከሥልጣን ሊነሳ የሚችለው አንድም የመንግሥትን አካሄድ ሲቃወም፣ አንድም የሕዝብን በደል ተጋርቶ ሲያልጎመጉም የተገኘ ቀን ነው፡፡ አለቀ፡፡

በተረፈ ለሥርዓቱ ታማኝ መሆኑን እስካረጋገጠና የሕዝብን ጉዳይ ‹‹ምን አገባኝ›› በሚል ስሜት ማለፍ እስከቻለ ድረስ በስነ ምግባር ጉድለትም ሆነ በኪራይ ሰብሳቢነት ጎዳና ውስጥ ተዘፍቆ ቢገኝ የሚያባርረው ቀርቶ የሚገመግመው አይኖርም፡፡ እንደውም የተሻለ ሥልጣን ሊሰጠው ይችላል፡፡

ከዚህ አንጻር ከዓመታት በፊት አቶ ዘርዓይ አሰገዶምን እና አባይ ወልዱን ተጋፍጠው የህውሓት ውድቀት ላይ ጉልህ ሚና የተጫወቱት አቶ ገዱና አቶ ንጉሡ ጥላሁን ዛሬ ከሥልጣን የተገፉት በሆነ መድረክ ላይ የሕዝብን ሕመም የሚጋራ ንግግር አድርገው ካልሆነ በቀር ‹‹የአማራን ሕዝብ ባግባቡ እያገለገላችሁ አይደለም›› ተብለው አይመስለኝም፡፡

ያመኑበትን እውነታ ያለምንም ማቅማማት በመናገር እና ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል የሚታወቁት አቶ ጸጋ አራጌና አቶ ዮሐንስም ተመሳሳይ እጣ ያጋጠማቸው ‹‹ለዙፋኔ እስከታመኑ ድረስ ቢሞስኑ ምን አገባችሁ›› ተብለው ካልሆነ በቀር በሥልጣናቸው ሲባልጉ ተገኝተው አይመስለኝም፡፡

ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን… በብልሹ ሥርዓት ውስጥ የሹመት እድገት የሚያገኙ አመራሮች መባረር ቀርቶ መታሰር የሚገባቸው ሲሆኑ የሚባረሩት ደግሞ የተሻሉት መሆናቸው እርግጥ ነው፡፡ በዚህም መሠረት አቶ ዮሐንስ ቧያለውን፣ አቶ ጸጋ አራጌን እና አቶ ንጉሡን ከሥልጣናቸው ያነሳው አካል በቅርቡ ደግሞ ጠባቂዎቻቸውን ማንሳቱን እየሰማን ነው፡፡

ከሕዝብ የሚነጥል ጥፋት ቢያገኝባቸው ኖሮ ዶክመንታሪ ሠርቶ ከማሰራጨት ወደኋላ የማይለው መንግሥት የፈጸሙት ጥፋት ከሕዝብ የሚቀላቅል መስሎ ስለታየው ከወንበርም አልፎ ወደ መቃብር ሊያወርዳቸው ድምጹን አጥፍቶ እየተሳበ ነው፡፡

ሆኖም ግን የማካቬሌ አስተምህሮ ‹‹ከሕዝብ ጉያ ሳታወጣ- ተቀናቃኝህን አትቅጣ›› የሚል ምክር የሚሰጥ በመሆኑ… ይሄን ተልዕኮ የወሰዱ ተላላኪዎችም እኒህ አመራሮች ከመንግሥት ጥርስ ውስጥ ባስገባቸው ጥፋት ፈንታ በሥልጣን ዘመናቸው የፈጸሙትንና በሕዝብ የሚታወቀውን ስህተት መንቀስ ጀምረዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቡነ ማቲያስና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓባይ ወንዝ ዙሪያ ትልቅ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋል

እኔ ግን እልኻለሁ…

እንዲህ ያለው መንቻካ ክስ በትናንት ጥፋት ተጸጽተው ወደ ትክክለኛ ጎዳና ለመግባት የሚያስቡ ባለሥልጣናትን የሚያከስም መሆኑን አውቀህ እኒህን አመራሮች ከሥልጣናቸው ባለፈ ጠባቂዎቻቸውን እስከማንሳት ያደረሰውን ምክንያት ወይም ጥፋት እስክታውቅ ድረስ ጠባቂያቸው ሁን፡፡

3 Comments

  1. አይ መከራ አገኘሁ ተሻገር ፈሪና ስልጣን ወዳድ ዘራፊም በመሆኑ ከቦታው ላለመነሳት ብዙ ደባ ስለሚሰራ ነቃ ብሎ መጠበቅ ነው ሰውየው የመምቻ ዱላ ነው ቅጥነቱን ማለቴ አይደለም።

  2. They all are not only politically idiot but also morally bankrupt cadres of the same criminal political system. They have no and will never have a real sense and interest of seeing the emergence and prevalence democracy . They just play a very cheap and deceptive political game just to keep surviving and robing the country’s resources . They know very well that if a true democratic change becomes. a reality, their livelihood will be in danger . That is why the armies or cadres of the so called Prosperity are. very busy with not only suppressing innocent voices but also busy with killing the truth Any killing innocent people who hold it firmly !

  3. Who do they need the protection from? If the PP government is their enemy, the government can use the very same guards to arrest or kill them (like General Seare) without needing to lift the security detail. They cannot be afraid of the people as their past political activity could only offend the Amhara; and the Amhara are not known to assassinate. Bereket Simon used to walk around Bahr Dar with no bodyguards till the very last year of the protest. They assign Amahra PP just so they feel alienated from the public, not because they are in any real danger from assassinations. There just does no exist any such history.

    Now that Abin and Amhara PP have been shunned by the people, is PP grooming a new group to contain the fervent Amhara nationalism? Is the Amhara majority still gullible, falling for speeches instead of demanding concrete actions? Looking for easy fixes instead of a struggle that would require work and sacrifice?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share