ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ስልጣናቸውን ማስረከብ አለባቸው!! የዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ የአቋም መግለጫ

/

 

 አገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ ብዙ ፈተናዎችን አልፋለች። አሁን ያለችበት ፈተና ግን እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው። በፊቷ የተደቀኑ በርካታ አደጋዎች በቶሎ እንዲቀረፉ ካልተሰራ ምን አልባትም በቅርብ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ላትኖርም ትችላለች።

ከአራት አመታት በፊት መደመር በሚል ፣ ለውጥ የተባለው በመጣ ጊዜ፣ ከምድር ጫፍ እስከ ምድር ጫፍ ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ተስፋ ሰንቀው ነበር። የኢትዮጵያ ትንሳኤ እየመጣ ነው በሚል የደስታ ድባብ ሰፍኖ ነበር። ሆኖም ግን በአራት አመት ውስጥ መደመርን ሳይሆን መፈናቀልን፣ ጄኖሳይዶችን፣ ጭፍጨፋዎችንና የሚሊዮኖች መቀነስን ነው ያየነው። ሰላምን ሳይሆን ደም መፋሰስንና ጦርነትን፣ ብልጽግናን ሳይሆን ድህነትና ረሃብን ነው ያየነው።

አገራችን አሁን ባለችበት ቀውስ ውስጥ መግባቷ አንዱ ምክንያት የሕወሃትና የኦነግ አሽባሪ ቡድኖች ተግባራት መሆናቸው የሚካድ አይደለም። ነገር ግን ሕዝብን ከነዚህ አሽባሪዎች ሆነ ከሌሎች አገራዊ አደጋዎች የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት የብልጽግና መንግስትን እንደ መንግስት መስራት ያለበት መስራት ባለመቻሉ፣ ከኦነግና ከሕወሃት ባልተናነሰ ተጠያቂ ነው።

በቅርቡ ሕወሃትና ኦነግ በአገራችን ክፍል በከፈቱት ጦርነት ብዙ ጥፋት አይተናል። በሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጥቃት ፣ ፈጽመዋል። ዜጎችን በጅምላ ጨፍጭፈዋል። እናቶቻችንና እህቶቻችን የጾታ ጥቃቶች ደርሶባቸዋል። የብዙ ኢትዮጵያዊያንን ሕልፈት ምክንያት ሆነዋል።

መንግስት ሃላፊነቱን መወጣት ባለመቻሉም፣ “ከአቅሜ በላይ ነው። በመደበኛ የወታደራዊ አደረጃጃት የኦነግና የሕወሃት ጥቃት መመከት አይቻልም” በሚል፣ ለሕዝብ ባደረገው ጥሪ መሰረት፣ ሕዝብ፣ የአማራና የአፋር ልዩ ኃይሎችና ሚሊሺያዎች፣ የአፋር አርብቶ አደሮች፣ የራሳ ገበሬዎች፣ ፋኖዎች ከመከላከያ ጋር በመሆን፣ ሕወሃትን በበርካታ የአማራና የአፋር ክልል ወረዳዎች ነጻ ማውጣት ችለዋል። በዚህ ሂደት ቀላል የማይባሉ ወገኖች ውድ ሕይወታቸውን ገበረዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከድልድይ ላይ ራሷን በመወርወር ለመግደል ስትሞክር የነበረችው ወጣት ማን ትሆን?

ሆኖም መጀመሪያዉኑ አገር እዚህ ደረጃ እንዳትደርስ ስራዉን መስራት ያልቻለው፣ በዶር አብይ አህመድ የሚመራው፣ የብልጽግና መንግስት፣ በሕዝብ የተገኘን ድል መልሶ በመቀልበስ፣ ሕወሃቶች ትግራይን ብቻ ሳይሆን ራያንና ጠለምትን እንደያዙ እንዲቀጥሉ፣ መከላከያ እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ እንዲቆም ወስኗል። ያ ብቻ አይደለም፣ በጦርነቱ የታሰሩ፣ አቶ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች የሕወሃት የጦር እስረኞች ለቀዋል።

የብልጽግና መንግስት ወደዚህ ውሳኔ እንዴት ሊመጣ እንደቻለ በዝርዝር የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ ህወሃቶች አሁንም በአማራና በአፋር ክልል ውጊያዎች እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ፣ ጦርነቱ ገና ሳያልቅ፣ ህዝቡን አሁን አደጋ ላይ እያለ፣ የሕወሃት ሰዎችን መልቀቅ ተገቢ ነው የሚል እምነት የለንም። በተለይም በአፋርና በአማራ ክልል የተከፈለውን መስዋትነት ያረከሰ፣ በአማራና በአፋር ክልል ላይ የተፈጸመ ትልቅ ክህደት ነው እንላለን።

ይህ ክህደት በቀላሉ መወሰደ አለበት ብለን አናምን። የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የአማራና የአፋር ክልል መጠየቅ አለበት፣ ዝም ማለት የለበትም ብለን እናምናለን። የዶር አብይ አህመድ መንግስት በዚህ መልኩ፣ ለሕዝብ ንቀት በማሳየት፣ በተናጥል፣ የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥል ውሳኔ እንዲወስን ሊፈቀድለት አይገባም።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ይሄን ውሳኔ የወሰኑ የብልጽግና አመራሮች በአስቸኳት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ መልቀቅ አለባቸው እንላለን ። ህዝብን ፣ ፓርላማውን፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ፣ ባለድርሻ አካላትን ሳይመክሩበት፣ አምባገነናዊ በሆነ ሁኔታ አሸባሪ የህወሃት መሪዎች እንዲለቀቁ በማድረግ አገርን የበለጠ አደጋ ውስጥ የከተቱ መሪዎች እንዲቀጥሉ መፍቀድ ማለት የአገርን ውድመት እንዲቀጥል መፍቀድ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ስልጣናቸውን ማስረከብ አለባቸው !!

 

Terms & Conditions

24 Comments

  1. አይ ዘሐበሻ፣
    ራስህን እንደዚህ ባታጋልጥ ይሻልህ ነበር። አጋጣሚ ትጠብቅ ኖሯል?
    ለመሆኑ ዶ/ር ዐቢይ ሥልጣን የሚያስረክቡት ለማነው? ለአምስት አመት በሚሊዮኖች ዜጎች ድምጽ መመረጣቸው ይሻራል ማለት ነው?
    ከወቀስኻቸው ጠ/ሚሩ ባስክ እኮ፣ አላወቅህም?あ

    • አለም የምትባል እን ከፍ ኮምፒተር የሰጠህ ማነው? ተሰርተህ ያላለቅህ መሀይም ነህ ተመርጠው ባደረሱት ጥፋትና በህዝብ ግፊት ስልጣን የለቀቁ መሪዎች መኖራቸውን እንኳን አታውቅም። እንዳንተ አይነት ላቅመ ማሰብ ያልደረሱትን ሰብስቦ ነው ካዋቂ በላይ አዋቂ መስሎ ለመታየት የሚጥረው።

  2. ዘሀበሻ ጥሩ ብለችሗል – ለዛም እናመሰግናለን::

    ለአስተያየት ሰጪ አለም: አለምዬ የኛ ምንጣፍ ጎታች, ለምን አቢቹ ተነካ ብለሽ አትገንፍይ, በደም የተጨማለቀን ሰው እየደገፍሽ ነውና ልብ ግዢ::

  3. I have to say that the statement is truly right both politically and morally ! The very decision by the very criminal ruling elites who continued the very criminal political system of EPRDF by purging out their creator and master (TPLF) and have brought the very essence of integrity of the country to the verge of collapse or disintegration are now clearly and straightforwardly telling us that the people of Ethiopia are nothing but simple subjects of a very dirty and criminal political game.
    Needless to say, , the inevitability of this horribly disturbing and dangerous political game was very clear when we terribly fooled ourselves or made ourselves terribly stupid not only by accepting but also endorsing the highly deceptive, dishonest, hypocritical, conspiratorial, and above all treasonous Abiy Ahmed as a leader of a true democratic change three years ago .Yes, we need to admit that it was when we and more particularly our intellectuals including those who believed to be the most senior ones both academically and experiences of services horribly failed to abandoned their realistic and critical thinking and became victims of a very deceptive and dangerous political rhetoric of a prime minister who used to be a very brainchild of an extremely backward and deadly political system of ethnocentrism .
    Now, the very message of this severely outrageous and consequently deadly political action is a message that does tell this generation that it is oaky, and it will be okay to play any dirty and deadly political game as long as it helps to keep and advance the very political power of ethnocentrism that is instrumental to keep the people divided to the extent of treating each other as if they have no common issues and values throughout their long history.
    This is what Abiy Ahmed, and his merchants of deadly political gambling did for the past three years and now reached their highest stage of treason.
    I strongly believe and argue that it is critically necessary not to run away from admitting our own horrible and repeated failures as individuals, as a group or groups and above all as a society. It is particularly essential not to ignore or avoid the very disgraceful if not devastating contribution of most of our intellectuals who horribly failed both politically and morally as far as what they were and are supposed to do as intellectuals was concerned!
    Will we be willing and able to reverse this very devastating political and moral bankruptcy? I know it won’t be easy because we terribly and repeatedly failed and became victims of a very deceptive, dishonest, hypocritical, conspiratorial, and extremely narcissist prime minister and his ruling circle. But there is no and there will never be any other better way than making what went wrong right and moving forward accordingly!

  4. የቸኮለ አፍሶ ለቀመ እንዲሁም ፍየል ከመድረሷ ቅጠል መበጠሷ እንደሚባለው ዘሐበሻ ይህንን የመሰለ የቋም መግለጫ ከማውጣት እና እራስን ከመጋለጡ በፊት የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል እንደሚባለው ረጋ ብሎ አመዛዝኖ ታስቦበት የአቋም መግለጫ ማውጣቱ አይቀልም ነበርን? እንዲሁም በመንግሥት በኩል ለዚህ ውሳኔ እንዴት እንደተደረሰ የተገለጸ የለም ካልከው፤ዝርዝር ሁኔታዎችን ባለማገናዘብ ይህ ይጻፋልን? በተጨማሪ ጉበቱ በውስኪ ብጥስጥሱ ወጥቶ ያለቀ በጉበት እና በስኳር ህመም የደቀቀ፤በሰው ኃይል መጽዳጃ ቤት የሚመላለስ፤በነርሶች የሚጠበቅ፤ ከነቤተሰቡ እጁን የሰጠ ከ80 እስከ 84 አመት የደረሰ አስከሪን ስብሀት ነጋ ተፈታ ተብሎ ስልጣን ይልቀቅ ተብሎ ይጽፋልን? እንዲሁም ህዝብ ሳይመክርበት በተባለው መንግሥት በህዝብ የተመረጠው 115 ሚሊዮን ህዝብን በመወከል ሀገርን በተመለከተ ውሳኔ እንዲወስን እንጂ 115 ሚሊዮንን ህዝብ ስብሰባ ጠርቶ አወያይቶ ለማሰር እና ለምፍታት አለመሆኑን መረዳት ተገቢ ሲሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለተባለውም በምርጫ ተወዳድረው በፓርላማውም በመንግሥት መሥሪያ ቤቶችም እየተሳተፉ መሆኑን መዘንጋቱ ዘሐባሻ የድህረ ገጽ የመግለጫ አቋምን ከማርከሱ ባሻገር እስረኛ ለመፍታት እና ለማሰር የፓርላማው ሥራ አልመሰለኝ እና ዘሐበሻ ራሥን መርምሮ የአቋም መግለጫ ማውጣት ተገቢ ይመስለኛል።

    • እንባው በቀለ, በስበሀት ነጋም ሆነ በአብይ ተቆጥሮ የማያልቅ ግፍ እና ወንጀል እንባህ ያልበቀለ ስለሆንክ ልብህ ድፍን ነው, እራስህን መርምር::

    • እሄ ህዝብ አልጋ ሲሉት መሬት ነው ወዳጄ
      ኢየሱስን በ30 ዲናር የሸጠው ሰው ነው እናም ከአብይ አህመድ ማር መጠበቅ ከባድ ነው ። ዝም ብለክ ብቻ ወደፊት የፈለገ ያይሃል ያልፈለገ ይተወው ይመችህ በርታልኝ

    • Ambaw Bekle

      Egziabhere Yiyileh as you joke on the hundreds of thousands of people massacred since your liar and criminal pastor took power!

      My Gash! what kinds of cruel people exist in this world.

    • አምባው ወይስ አለም ከተማሩ አይቀር እንደ እናንተ ነው አይ ትንተና አይ የሀሳብ ጥራት
      ባጠቃላይ ጃፓን ለሙከራ የሰራችሁ ጽራት የጎደላችሁ ሮቦቶች ናችሁ እትምጡ ።ፕሮፌሰር መስፍን በናንተ ልክ እንዲገባችሁ ቢጽፍም ልትረዱ ባለመቻላችሁ አዝኖ ትቷችሗል። ኢትዮ ላቭ የሚባል ለናንተ የሚመጥን ክፍል ስላለ ብታረጁም ሂዳችሁ እራሳችሁን ሸንግሉ።

    • አቶ አምባ እዉን አብይ አህመድና ድርጅቱ በነፃ ምርጫ አሸንፏል ብለዉ ያምናሉ። በ97 ዓ ም 99 በመቶ ተቃዋሚዎች ያሸነፉበት የምርጫ ክልሎ አደስ አበ ባ እንኳ አንድ ተቀዋሚ አልተመረጠም። የምርጫ ሂደቱ የተበላሸም ነበር። በእኔ እምነት የዘሀበሻ የአቋም መግለጫ ትክክል እና እ’ንዲያዉም የዘገየ ነው።

  5. Morally and professionally the right move. Journalist are supposed to protect the people from immoral and deceitful rulers. Those journalists who serve the treasonous rulers as slaves are worse than the rulers.

    Thank you, the Habesha!

  6. ዘ-ሐበሻ ቀላል ያልሆነ መልዕክት ነው ያለህ፤ በርታ፣ ቁስል ያለበት ነው የሚተችህ፣ ትችትን ደግሞ በገንቢነቱ ተጠቅመህ መልዕክትህን አስተላልፍ ፣አድናቂህ ነኝ፣ ዕደግ።

  7. በነገራችን ላይ በጎሳ ስም የሚካሄደው ፖለቲካ አብዛኛውን የአንድን ብሄረሰብ ተወላጅ በፍጹም አይጠቅመውም። ለምሳሌ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ይካሄድ የነበረው የጎሳ ፖለቲካ በመሰረቱ ሰፊውን የትግሬ ብሄረሰብ በፍጹም አልጠቀመውም። ተጠቃሚ የነበረው በጣም ጥቂቱ የፖለቲካ፣ የሚሊታሪና የኢኮኖሚ ኤሊት ነበር። ይህም ቢሆን በቤተሰብ መልክ በተያያዘ አወቃቀር አብዛኛውን ህዝብ ከማንኛውም ዐይነት እንቅስቃሴ ያገለለ ነው። የጎሳ ፌዴራሊዝም የሚባለውም በየብሄረሰብ ውስጥ የዎር-ሎርድ አስተሳሰብ እኒዳብዳር ያደረገና፣ ጥቂቶች ተጠቃሚ በመሆን የየብሄረሰቡ ሰፊ ህዝብ ደግሞ ወደ አበባ፣ ሸንኮራ አገዳና ቡና ተካይነት ነው የተወረወረው። የየክልሉ አስተዳዳሪዎች ራሳቸውን ከማደለብ በስተቀር በየክልሉ ሚዛናዊነት ያለው በስራ-ክፍፍል ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚ ዕድገት ማዳበር አልቻሉም። ለምሳሌ የኦሮምያን ክልል ስንመለከት አነ አባዱላና የኋላ ኋላ ደግሞ እነ ለማ ስልጣን ላይ ወጥተው የወያኔ አገልጋይ ከመሆን በስተቀር ለህዝባቸው ይህ ነው የሚባል ስራ አልሰሩም። ጨወታው በብሄር ስም ጥቂቶችን ማደለብና አብዛኛውን ህዝብ ከማንኛውም ዐይነት ተሳትፎ ውጭ ማድረግ ነው። ለምሳሌ የኢኮኖሚ ዕድገትንና የህብረ-ብሄርን አገነባብ ታሪክ ስንመለከት ማንኛውም አገር ቢሆን በአንድ ወጥ ብሄረሰብ አገዛዝ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤት የሆነበት አገር በፍጹም የለም። ለምሳሌ አሜሪካን በቴክኖሎጂ፣ በሳይንስ፣ በሙዚቃና በሌሎች ነገሮች መንጥቃ ለመሄድ የቻለችው ከተለያየ ጎሳ የተውጣጡ ሰዎች ባደረጉት አስተዋጽዖ ነው። አንድ አገር እንደ ማህበረሰብና እንደ ህብረተሰብ ለማደግ ከተፈለገ የግዴታ በህብረተሰቡ ዘንድ መቀላቀልና በአንድ አገር ውስጥም ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት እንዲኖር ያስፈጋል። በአንድ አገር ውስጥና በአንድ አካባቢ ከአንድ ብሄረሰብ የተውጣጣ ሁሉኑም ነገር በሚቆጣጠርበት አገር ውስጥ ሁለ-ገብ የሆነ የኢኮኒሚና የባህል ዕድገት በፍጹም ሊኖር አይችልም። ይህንን የማይረዱ ተማርን የሚሉ ሰዎች የሚያደርጉት እንደርነት ከህብረተሰብና ከተፈጥሮ ህግ ጋር ነው። ተፈጥሮን ተፈጥሮ የሚያደርጋት የልዩ ልዩ ነገሮች ውጤት በመሆኗ ነው። እንደዚሁም ህብረተሰብን ህብረተሰብን የሚያደርገው በስራ-ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ሁለ-ገብ ዕድገት ሲኖር ብቻ ነው። እንደሚታወቀው እያንዳንዱ ግለሰብ የተለያዩ ተስጥዖ ስላለው ባለው ዝንባሌና በሚሰራው ስራ አማካይነት የንግድ ልውውጥ ይካሄዳል። በዚህም አማካይነት ፈጠራ ይዳብራል።
    በአገራችን ያለው ትልቁ ችግር የትግሬና የአኦሮሞ ኤሊቶች ከተሳሳተ ትረካ በመነሳት የሚያካሂዱት ከሳይንስ ውጭ የሆነ ፖለቲካ የአገራችንና የህዝባችንን ህልውና እየተፈታተነ በመምጥት ላይ ነው። ለምሳሌ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አማራው ብቻውን የገዛበት ዘመን አልነበረም። በአፄ ምንሊክና በአፄ ኃይለስላሴ የአገዛዝ ዘመን በአገዛዙ ውስጥና በመንግስት መኪና ውስጥ በተለይም ከትግሬና ከኦሮሞ የተውጣጡ ኤሊቶች ተሳትፈውበታል። የአገዛዙ አንድ አካል ነበሩ ማለት ይቻላል። አፄ ምንሊክም ሆነ አፄ ኃይለስላሴ አማራውን ብቻ የሚጠቅም የኢኮኖሚና የማህበራዊ ፖለቲካ አላካሄዱም። በእነሱ ዘመን አብዛኛው ህዝብ ገበሬ ስለነበረና ፊዩዳላዊ ስርዓትም ስለነበር ፖለቲካቸውም በፊዩዳሊዝም መነጽር መታየት ያለበት ነገር ነው። በሌላ አነጋገር፣ በጊዜው የነበረው በሁሉም ብሄረሰብ ውስጥ ይታይ የነበረው ኋላ-ቀርነት ከነበረው ስርዓት ጋር የሚያያዝና፣ የፊዩዳሊዝምን ውስጣዊ-ኃይል ማነስ የሚያንፀባርቅ ነበር። በጊዜው የተገለጸለት ምሁራዊ ኃይልና ዲይናሚክ የሆነ ኃይል ባለመኖሩ አፄ ምኒልክም ሆነ አፄ ኃይለስላሴ ከዚያ አልፈው መሄድ አልቻሉም።
    ስለሆነም ደሮ ወያኔዎች፣ ዛሬ ደግሞ የኦሮሞ ኤሊቶች የማይረዱት ይህንን ሀቅ ነው። የሰዎቹ አስተሳሰብ በተሳሳተ ትረካ ስከተቀረጸ ወይም ፕሮግራምድ ስለሆነ ጠቅላላውን የአማራ ብሄረሰብ እንደ ጠላት አድርገው ያዩታል። የአቢይም ችግር ይህ ነው። በጣም በተሳሳተ ፖለቲካ ለኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለጠቅላላው የአፍሪካ ህዝብም ከፍተኛ አደጋ እየፈጠረ ነው። ሰውየው ነገሮችን እየገለበጠ ነው የሚያየው። ተበዳዩን ትቶ በዳዮችን ለመጥቀም ነው የሚሯሯጥ። ገዳዩን እንደተገደለ የሚቆጥር፣ አገርን ያወደመና ታሪክ ያበላሸ ትክክል ነገር እንደሰራ አድርጎ የሚያይ ነው። ይህም የሚያረጋግጠው በወያኔ አገዛዝ ዘመን ወያኔዎች ይከተሉ የነበረውን የተበላሸ ፖለቲካ መመርመር አልቻለም። ወይም ምን እንደተሰራ የሚያውቀ ነገር የለም። በአጭሩ ፖለቲካ ማለት ምን ማለት እንደሆነ በፍጹም አልገባውም። ፖለቲካ ጥበብን የሚጠይቅ ነው። በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ያሉ ቅራኔዎችን በስነ-ስርዓት ማንበብና እንደ የሁኔታው ጥበባዊ መልስ መስጠት ያስፈልጋል። ከዚህ ስንነሳ አቢይ ሰሞኑን የወሰደው እርምጃ በራሱ ላይም ከፍትኛ አደጋ የሚያመጣ ነው። ሰውየው በአንድ ጊዜ በህዝብ ዘንድ የነበረውን ድጋፍ እያጣ ነው። ሁሉንም ነገር እኔ አውቃለሁ በማለት ብቻውን ነው ለመወሰን የሚፈልገው። ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በአገራችን ምድር ዲሶፖታዊ አገዛዝ ተፈጥሯል ማለት ይቻላል። ከዚህ ዐይነቱ አስተሳሰቡም ፍቅቅ የሚል አይደለም። ወሳኙ እኔ ስለሆነኩ ምንም ይሁን ምን ዝም ብላችሁ ተቀበሉ ነው የሚለው። ይህ ዐይነቱ አስተሳሰብና ፖለቲካ ደግሞ በ21ኛው ክፍለ-ዘመን የሚያስኬድ አይደለም።
    ፈቃዱ በቀለ
    www. fekadubekele.com

  8. አለም የምትባይው ወይንም የምትባለው አስተያየት ሰጪና እንደዚሁም አምባው በቀለ የተባልከው አስተያየት ሰጪ ሁለታችሁም አብይ አህመድ በድረ ገቶች ላይ ያሰማራችሁ ውታፍ ነአዮች ናችሁ፡፤ አብይ አህመድን በመደገፍ ስራ ላይ ተቀጥራችሁ ይህንን መሰል አስትያየቶችን እየጻፋችሁ የምትኖሩ ሆዳሞች፡፤ በሚገባ የታወቃችሁበት ስራችሁና የአብይ አህመድ ተከፋይ ለመሆናችሁም ብዙ ማሳየወች አሉ፡፡ አሁንም ይሄውና ዘሀበሻ በወጣው የድረ ገጽ አቋሙ ላይም ዘመታችሁበት፡፡
    በዘሀበሻ ድረ ገጽ ላይ ትንሽም ሆነ ከበድ ያለ አብይ አህመድን የሚጎሽም ጽሁፍ ሲወጣ ከማንም በፊት ብቅ ብላችሁ የጥላቻ መርዛችሁን የምታቀረሹ ከንቱ ሆዳሞች፡፡ በዘሀበሻ ድረ ገጽ ላይ የሚጽፉ ብዙ ጽሀፊወች የጽሁፎቹ ግርጌወች ላይ አስተያየቶቻችሁ ተለቅመው በሰነጠረዥ ቢቀርቡ ሁልጊዜ የያዟቸው ሀሳቦች አብይ አህመድን ደግፎ ጸሀፊወችን መቃወም ነው፡፤ ይህ መቸና በየትኛው ጽሁፍ ላይ ምን አይነት አስተያየት እንደሰጣችሁ (በተለይ አለም በሚለው ስም) መረጃውን በቀን፣ በርእስና በስድባችሁ/ባለጌነታችሁ ልክ ሰንጠረዡን ሰርተን ይዘነዋል፡፤
    ሰው ለሆዱ ሀቅን ተቃርኖ ምን ያህል ይኖራል??
    አብይ አህመድ በኢትዮጵያ የመሪነት ቦታ ላይ ተክፍሶ በውስጡ የደረተው የኦሮሙማ ድሪቶ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ጉዳት እንጅ ጠቀሜታን የማያመጣ ችሎታ፣ አተያይና ወኔ የጎደለው ሰው በመሆኑ ይህ በጎደሎ ቀን የመጣብን ደነዝም ሴረኛም ሰው ስለሆነ ከዚህ የከፋ እልቂት ሳያመጣብን በፊት ከስልጣኑ በአስቸኳይ መወገድ አለበት፡፡

  9. ዘ ሀበሻ እውነትም ለህዝብ የምትታገል መሆንህን በዚህ አቋም ማረጋገጥ ስለቻልን ከልብ እናመሰግ ናለ!! ከፖለቲከኞች እና ከመሪዎች ጋር ሳይሆን ከህዝብ ጋር የሚቆም ሁል ግዜም ስለ እውነት የሚቆም አሸናፊ ነው፡፡

  10. የኦነግ መንግሥት ስለሆነ ወያኔ ጨርሶ ከሚጠፋ አማራን እያዳከመ busy እንዲያደርግ ይፈለጋል። ሕዝቢ ትግራይ ወያኔ የጋተውን የጥላቻ መርዝ ካላስወገደ፥ ሁለቱን ሕዝቦች አናክሰው ሥልጣናቸውንና አጀንዳቸውን ያደላድላሉ። ፕሮቴስታንት ነን ብለው የምዕራቡን፥ እስላም መስለው የዐረቡን የቱርኩን እርዳታ ይቀበላሉ ።
    ኦርቶዶክስ ሆይ ንቃ፣ ተጋሩ ሆይ የዘረኝነቱን መርዝ ትፋ፣ አማራ ሆይ ተደራጅ፥ የወገንህ እልቂት ይሰማህ። ስለ ድንግል ብሎ እግዚአብሔር ይቅር ይበለን።
    ለዐቢይ ብልግና የምታሽቃብጡ አማሮች ሁሉ፥ እባካችሁ የወገናችሁ ሕመም ይሰማችሁ፣ ሰው ሁኑ።
    ጊዜው የኛ ነው ብላችሁ ግፍ የምትሠሩ የምታሠሩ ሁሉ፥ እግዚአብሔርን ፍሩ። እናንተ እንኳ ከፍርድ ብታመልጡ፥ ለልጆቻችሁ ለዘራችሁ ግፍ አታኑሩ።

  11. እግዜር የሰጣት ዕድል ሆኖ ኢትዮጵያ በብዙ ሐግሮች ደርጅተው የሚኖሩ ልጆች አሏት እነዚህ ልጆች ኢትዮጵያ ተብላ ከምትጠራው ሐገራቸውና ወገኖቻቸው በምንም መልኩ አይለዩም የግዜና የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ የአብይ መንግስት ከመጣ ጀምሮ በኢትዮጵያ ባለማወቅ የፋሺስት አስተሳሰብ እየዳበረ ነው ላይ ላዩ ደህና ይመስላል ውስጡ ግን መርዝ አለ – መርዙን እያየነው ነው::

  12. ዘ ሐበሻ ልክ እንደ ሞቱት ነን አገራችን የበሻሻ ዱርየ መቀለጃ ሆነች ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ይላሉ አበው!
    ህዝብን ማታለል እስክመቼ ?
    የስማዕታት ነፍስ ይፋረድ !!!!!!!

  13. አብይ አህመድ የራሱ የሆነ በለእዉነት እና በመረጃ ላይ የተመረኮዘ ዉሳኔ መስጠት የማይችል ያልሰከነ ሰዉ ነው። ሁሉንም ዜጎች በእኩል የማያይ። ለኦረሞ የበላይነት የቆመ ገዢ ነው።

  14. ዶሮው ለ3ኛ ጊዜ ጮኽ! – ከወንድሙ መኰንን፣ እንግላንድ

    “እውነት፡ እልኻለኹ፥ በዚች፡ ሌሊት፡ ዶሮ፡ ሳይጮኽ፡ ሦስት፡ ጊዜ፡ ትክደኛለኽ።”
    ማቴዎስ 26 ቁጥር 34
    ከወንድሙ መኰንን፣ እንግላንድ 11 January 2022

    https://amharic.zehabesha.com/archives/125808

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share