“እናንየን ድው አደረጋት” በእናቱና አባቱ አስከሬን መካከል በደም ተጨማልቆ የተገኘው የሁለት አመት ህጻን

/

240761225 2072947932856544 3515864049048125032 n

የሽብር ተግባሩ ወደር ያልተገኘለት አሸባሪው ህወሓት በአንድ ቀን እናትና አባቱን ገድለው በወላጆቹ አስከሬን መካከል ጥለውት የሄዱት የነፋስ መውጫው ህጻን በነፋስ መውጫ ተገኝቷል።

ነዋሪነታቸው በጋይንት ወረዳ ነፋስ መውጫ ከተማ የሆኑና ባልና ሚስት የነበሩት አቶ ደሴ ጌታቸውና ወይዘሮ ገነት አለብኝ የሦስት ልጆች ወላጆች ናቸው። የእንስሳትም የሰውም ህይወት ሳይመርጥ ባገኘው ቦታ በጦር መሳሪያ እየጨፈጨፈ ያለው አሸባሪው ህወሓት ለእነ አቶ ደሴና ባለቤታቸውም አልራራም፤ መንገድ ላይ በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል።
ሟች አቶ ደሴ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ገነት የሁለት አመት ልጃቸውን ይዘው መንገድ ላይ በነበሩበት አጋጣሚ ነው ከአሸባሪው ታጣቂዎች ጋር የተገናኙት። አረመኔዎቹ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች ህጻኑ ፊት እናቱንና አባቱን በጥይት ደብድበው ልጁን በወላጆቹ ሬሳ መሀል ጥለው ሄደዋል።
240802190 2072947982856539 6717742798187647366 n
240802190 2072947982856539 6717742798187647366 n
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች የሟች ቤተሰቦች ቤት ድረስ በመሄድ ምን እነደተፈጠረ ለመረዳት ጥረት አድርጓል።
ከታጣቂዎቹ ግፍ በህይወት የተረፈውን ህጻን ከሁለቱ ሟቾች ሬሳ መሀል በደም ተለውሶ እንዳገኙት የሟች እናት ወይዘሮ አባይ አንዳርጌ ተናግረዋል፡፡
የሁለት ዓመቱ ህጻን አማን ደሴ እናቱን እነ አባቱን በታጣቂዎቹ ስለመነጠቁ ያወቀ አይመስልም፤ አሁንም ድረስ ናናዬ እያለ እናቱን እየጠበቀ በር በሩን እየተመለከተ እነደሆነ አያቱ ነግረውናል፤ እኛም ያንኑ ተመልክተን አረጋግጠናል።
በግቢው ያለው ለቅሶ የወላጆቹ ሞት መሆኑን ያልተረዳው ህጻን በየመሀሉ ደግሞ በኮልታፋው አንደበቱ “እናናዬን ድው አደረጋት” እያለ የተመለከተውንና ውስጡ የቀረውን የታጣቂዎች ግፍ ይናገራል።
በአዲሱ ገረመው (ነፋስ መውጫ)
(ኢ ፕ ድ)
ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰበር ዜና | ምሬ ወዳጆ በርካታ መከላከያ ማረከ | Ethiopian News May 1 2023 |

2 Comments

  1. It is the right thing to blame and condemn TPLF as one of the main causes of the very tragic situation we are witnessing in our country! But I am sorry to say but I have to say that it is politically stupid and morally clumsy not to be courageous enough to talk about the other very deadly faction or junta of EPRDF (Prosperity) in the Arat Kilo palace! Yes, these kinds of tragic situations are very common in the region of Oromuma for three years and beyond. Now OLF and TPLF and all other criminal bodies are making alliances of bigger and more deadly forces on the one, and those in the palace are trying to survive their own deadly political system of EPRDF in which they grew up and served with great deal of loyalty. Believe or not, the very enemy of millions of kids like the above very heart-breaking kid are not only TPLF and its allies but also those who are in the palace who keep playing the very deadly political game of ethnocentrism they have been playing for so many years. That is why I strongly argue that the politics of blaming and condemning TPLF +OLF+. .. but not having the courage to talk about those in the palace with their very cancerous political behaviors and actions is a total stupidity of politics and decay of morality! If we want to see all these types of tragic situations like the one in the above information to end, we must talk and act to end the political system of EPRDF, not simply talk and complain about the very known bad behavior and act of this or that grouping!

  2. This kid strong in his face will defintely bring something
    in future as he is generously given to this mess world.
    For all these sabotage in one way or the other those tricky tricky
    People, selfish officials and greedy govt bodies will be liab
    le not be liable on court even if not functional but akso liable on other world, heaven of God!! GOVT of Ethiopia
    still has to
    investigate its internal parts and has to make quick
    decision because the mess of all these senarious attri
    buted to weak and reluctant govt actions. Please Abiy Admn
    has to take humble reaction as most are doing fake, just for public relations.
    Pragmatic actions crucial.
    Long luve to Ethiopia.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share