ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

/

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሕዝቡ እንደ አንድ ሠራዊት ሆኖ ለሀገሩ ህልውና በመቆም፣ የመከላከያ ሠራዊቱን በሁሉም ነገር በመደገፍ፣ የውጪውን ጫና እና የውስጡን ትንኮሳ እንዲመክትና እንዲቀለብስ ጥሪ አቀረቡ
*************************

ለትግራይ ሕዝብ ያለንን ሐሳብ፤ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያለንን ቦታ ለመጨረሻ ጊዜ አሳይተናል። ግጭት ላለማባባስ፣ ለሕዝቡ የእርሻ ወቅት ፋታ ለመስጠት እንዲሁም የርዳታ አቅርቦቱ ያለ ሰበብ እንዲከናወን ስንል በሰብአዊነት ላይ የተመሠረተ የተናጠል የተኩስ አቁም አድርገናል። ሰላም የተወሰነ ዋጋ እንደሚያስከፍለን ብናውቅም ይህ ግን የመጨረሻ ሰላማዊ ዕድል ነው።

ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ እንደሚባለው ጁንታው የሰላም መንገድ ሊዋጥለት አልቻለም። አሁን ባለው ቁመናው ያለ ግጭት ውሎ ማደር አይችልም። ሕጻናትና ወጣቶችን በአደንዛዥ ዕጽ እያሳበደ ወደ ጦርነት እየማገደ ይገኛለ። የመከላከያ ሠራዊቱ እነዚህን ሕጻናት ወታደሮች የመታደግ ሞራላዊ ግዴታ ወድቆበታል።
ለሕዝባችን ስንል የከፈልነው ዋጋ ባልገባቸው ደካሞች ምክንያት ውጤት አላመጣም። ጁንታው የኢትዮጵያ ህልውና ቀንደኛ ጠላት መሆኑን ደግሞ እያስመሰከረ ነው። ይሄንንም መላ ሕዝባችንን አስተባብረን እንቀለብሰዋለን። በአንድ በኩል ሰብአዊ ርዳታ እንዲቀላጠፍ እየሠራን በሌላ በኩል የውጭና የውስጥ ጠላቶች ተናበው የከፈቱብንን ጥቃት መክተን እንቀለብሰዋለን።
ጁንታው ዋሻ ውስጥ ገብቶ ሕዝቡ በረሐብ ሊያልቅ ነው እያለ ሲያላዝን ነበር። ለሕዝቡ ሲባል ሰብአዊ የተኩስ አቁም ሲደረግ ደግሞ የረሐቡን አጀንዳ ትቶ የጦርነት ነጋሪት መጎሰም ጀመረ።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ስለ ርዳታና ስለ ረሐብ ሲናገር መቆየቱን ዘንግቶ ጁንታው ሕጻናትን ሲያሰልፍ እንኳን ዝምታን መርጧል። የርዳታ መግቢያ ኮሪደሮችን የግጭት ቦታዎች ሲያደርጋቸው የርዳታ ድርጅቶች አሁንም መንግሥትን ለመውቀስ ይቃጣቸዋል። እነዚህን ሁሉ ከግምት በማስገባት መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ ነገር በተገቢው መንገድ ያደርጋል።
ሕዝባችን ከሐሰተኛ መረጃዎች እና ከጠላት ፕሮፓጋንዳ ራሱን እንዲጠብቅ አሁንም ለማሳሰብ እንወዳለን። ጁንታውና አጋሮቹ ያላቸው ዐቅም ውሸትን መፈብረክ ብቻ ነውና። የውስጥና የውጭ ኃይሎች ፕሮፓጋንዳቸውን አቀናጅተው ሕዝብን ለመከፋፈል እየሠሩ ነው። ለዚህ ደግሞ ሕዝባችን እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ እንደ አንድ ሠራዊት ሆኖ ለሀገሩ ህልውና በመቆም፣ የመከላከያ ሠራዊቱን በሁሉም ነገር በመደገፍ፣ የውጪውን ጫና እና የውስጡን ትንኮሳ እንዲመክትና እንዲቀለብስ ጥሪ እናቀርባለን።

EBC

ተጨማሪ ያንብቡ:  ታግደው የነበሩት መምህር ግርማ ወንድሙ ከፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል

4 Comments

  1. It is very embarrassing or disgusting to Ethiopia to remain under these types of stupid or nonsense and ruthless ruling elites whose hands are terribly full of the very blood of innocent Ethiopians for 27 years as the very tools of TPLF and now as ruling forces in the palace for more than three years !
    It is absolutely outrageous to hear this guy (the so casket pm) saying the same big and dangerous rhetoric of lie over and over and over again ! He is one of the most mischievous and dangerous political figure particularly to the people of Ethiopia who continued to face untold sufferings partly because they terribly lack basic level of literacy and access to credible information .
    I really wonder how theses types of politicians like the pm who have their own children and family can sleep a good sleep with all their nonsensical , mischievous and ruthless political mentality and behavior !

  2. Why didn’t want to communicate his message right through electronic media instead of on his Facebook or social media ? Is us not a political jock if not an insult to the people of Ethiopia who have no the literacy . access and affordability to the use social media ? These guys of political gambling have no any sense of what is good or bad as long as they feel that their power is protected by any means! Sad!

  3. የሰውየው ዲስኩር ሰልችቶኛል። ሙያ በልብ ነው። እልፍ ጊዜ የሰላም ጥሪ ማድረግ ደንቆሮን ከተኛበት እንደማስነሳት ይሞከራል። በእኔ እምነት እነ አቦይ ስብሃትም እዚያው ገደሉ ውስጥ መቅረት የነበረባቸው ሰዎች ናቸው። ወያኔን መለማመጥ ለመሸወድ ብቻ ነው። ወያኔ ሰው ገድሎ ቀብር የሚውል፤ እዝን ላይ አብሮ የሚቀመጥ በዘሩ የሰከረ የፓለቲካ ድርጅት ነው። በቅርቡ ዶ/ር ተብዬው ደ/ጽዪን ሮይተርስ ላይ ቀርቦ በቪዲዪ በሰጠው አጭር የቃል ምልልስ እንዲህ ይለናል። ” አላማችን ወራሪዎችን ጠራርገን ማስወጣት ነው። ከዚያም አልፎ አይቀጡ ቅጣት ለመስጠትና ለመደቆስ ነው” ያው በእንግሊዘኛ ስለሆነ ቃለ መጠየቁን የሰጠው እንደ ተረዳኝ ነው የተረጎምኩት። እብድ ለመሆን በሃበሻ ምድር ልብስ ማውለቅ አያስፈልግም። ሴቶች ወንዶች እናቶች አባቶችን ቪዲዪ ላይ አማራን ለመቅጣት ነው የምንዘምተው በማለት ለሮይተርስ ሲናገሩ መስማት እብደታችን ጣራ ላይ መውጣቱ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። በአንጻሩ የአማራው ክልል ተወረሃል ውጣ ድረስ ተብሎ አዋጅ መነገሩ ሃገሪቱ ወዴት እያመራች እንደሆነ አስረግጦ ያመላክታል። ይህ ሁሉ ግን የዶ/ር አብይ መንግስት ጥፋት ነው። ትግራይን መልቀቁ እንዳለ ሆኖ አላስፈላጊ የሰላም ጥሪ ሌት ተቀን ለእነዚህ ደም አፍሳሽ ሙታኖች ማቅረቡ የመንግስትን ደካማነትና ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ነገር እንደሆነ እናያለን።
    እውቁ ጣሊያናዊ ፈላስፋና የዚያ ዘመን የፓለቲካ ስሌት አዋቂ Niccolò Machiavelli እንዲህ ይለናል። “መንግስት ማለት እምብዛም የማይጨክን፤ እምብዛም ለዘብተኛ ያለሆነ፤ በማህል ላይ ሆኖ ለሃገር ደህንነትና ለህዝቦች አንድነት የሚቻለውን ሁሉ በድብቅም ሆነ በይፋ የሚፈጽም ነው” ይለናል። እንዴት ለዶ/ር አብይ የወያኔ ሴራና አልሞት ባይነት ይጠፋዋል? ራሱ ከዚያ የክፋት ጆኒያ አይደል እንዴ ሾልኮ የወጣው? የምን መለማመጥ ነው። ሊገልህ የመጣን የዘር ፓለቲከኛ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው እንታረቅ፤ የዓለም ህበረተሰብን ሰምተን፤ ለእፎይታ ጊዜ፤ ለእርሻ ጊዜ እያሉ ሰውን ማማታት። አይበቃም? ድመት መንኩሳ አመለዋን አትረሳ ጥሩ አባባል ነው። ግን ድመቷ ደጋግማ መመንኮሷ ለምድሩም ሆነ ለሰማይ ቤት ቢላሽ ነው። ስለሆነም መልኩስናው እንዲቀርባት ማድረግ ነው።
    ጠ/ሚሩ ዲስኩራቸውን አሳጥረው ወያኔና የወያኔ አመራሮችን አይቀጡ ቅጣት ካልሰጧቸው ሂሳቡ የሚወራረደው በአማራና በኤርትራ ህዝብ ላይ ብቻ ሳይሆን በጠ/ሚሩና ከእርሳቸው ጋር አብረው በሚደሰኩሩት ሁሉ ነው። ወያኔ የሆነ ሰው ምንም ጊዜ ቢታጠብ ከወያኔነቱና ከዘረኛነቱ በጭራሽ አይጠራም። መስሎአቸው ስንቶች ምግባቸው ላይ መርዝ እየጨመሩ በወያኔ ሴራ ተሰናብተዋል። የጦርነቱ አራማጆችና የትግራይን ህዝብ ከሌላው ጋር የሚያላትሙት ሃይሎች በህቡዕም ሆነ በይፋ በተገኙበት በቁጥጥር ስር እስካልዋሉ የትግራይ ህዝብ ጦር ከመምዘዝ አይቦዝንም። ትላንት በየስፍራው የኢትዮጵያ ጦር ይህን ሰርቶ የኤርትራ ወታደር ሰው ገድሎ ይሉን የነበሩ የወያኔ አለቅላቂ ሚዲያዎች ዛሬ ድምጻቸው አይሰማም። ቆም በማለት ለምን ብሎ መጠየቅ አስፈላጊ ነው። እነዚህ ያለና የሌለ ወሬ አነፍናፊ ስመ ነጻ ፕሬስ የመንግስታት የፓለቲካ ሴራና ትንኮሳ አስፈጻሚ በመሆናቸው ነው እንጂ ሰራዊቱ ትግራይን ለቆ ከወጣ በህዋላ ወያኔ በትግራይ ህዝብ የፈጸመውና በመፈጸም ላይ ያለው በደል አራዊቶች እንኳን የማያረጉትን ነው። ግን ማን ይዘግበው? በኤርትራ ስደተኞች ላይ የተፈጸመውንስ ማን ይጻፍ? የወያኔ ብቀላ በሞተ አስከሬን ላይ ሁሉ ነው። ከሰውነት ደረጃ የወጡ እንስሳዎች ናቸው የምንለው ለዚያ ነው።
    የትግራይ ህዝብ ወያኔን አፍቅሮ የሰሜን እዝን የወራሪ ሃይል በማለት ባደረሰበት ጫና ጥሎላቸው ወቷል። እሺ እስቲ አሁን ምን ይፈጠር ተብሎ ነው ሂሳብ ለማወራረድ ሰው የሚያልቀው? በዚህ ተግባርስ አትራፊዎቹ እነማን ናቸው? ትላንትም ዛሬም ወደ እሳት የሚገፉህ የወያኔ ሃርነት አመራሮችና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ያተርፋሉ። የትግራይ ህዝብ ግን ከመከራ ወደ መከራ እንደሚሸጋገር ግልጽ ነው። ኢትዮጵያ ፈራርሳ ትግራይ ሃገር ሆና በሰላም እኖራለሁ ብሎ ማሰብ ተንጋሎ መትፋት ነው። አይሆንም። እዚህም እሳት እዚያም እሳት ይኖራልና። ሁሌ ሲገዳደሉ መኖር። አይሰለችም?
    በመጨረሻም ጠ/ሚሩና ሌሎችም ባለስልጣኖች እባካችሁ መግለጫ አታውጡ። አደነቆራችሁን። ሙያችሁን በስውር ስሩ። ቀረርቶው፤ ሽለላው፤ ዘፈንና ታንቡር መምታቱ፤ ደመሰስናቸው ማለቱ ሁሉ ይቅር። የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የኢኮኖሚ እቀባ እንዲያደርግ መጠየቁ ከአሜሪካ በተነገረው መሰረት ነው። ተናበው ነው የሚሰሩት። እንግዲህ እናንተ ፍረድ ማን ላይ ነው ቁጣው ማተኮር የነበረበት? ወያኔ ላይ ወይስ ትግራይን ለቆ በወጣው መንግስት ላይ? ፍትህ በምድር ላይ እንደሌለ እናውቃለን። የምዕራባዊያን ሴራ ጥልቅ ነው። መሪዎችን እስከማስገደል የሚደርስ፤ ዞረው ተመልሰው ደግሞ ስለ ነጻነትና ዲሞክራሲ ሊነግሩን ይቃጣቸዋል። ዓለምን የሚገዛው ረጅም ድላ በእጅ ሲገባ ብቻ ነው። ሰሜን ኮሪያን ያልሞከሩት ለዚያ ነው። እልፍ ጊዜ የሚደነፉባት ኢራን እኔም ጋ እሳት አለ ሌላም እሳት እያዘጋጀሁ ነው በማለቷ ነው እስካሁን ያልተነካችው። ደካማ ብትሆን ኖሮ እስካሁን የኢራቅ፤ የሊቢያ፤ የየመን፤ የሶሪያ እድል በገጠማት ነበር። ጠ/ሚሩ የውጭውን ጫና ባፍንጫዬ ይውጣ በማለት የሃገሪቱን ዳር ድንበር ከወንበዴዎችና ከወራሪዎች መታደግ እስካልቻለ ድረስ የታሪክ ተወቃሽና ቀዳሚ ሟች ከመሆን አይድንም። ቀን እያለ ይታሰብበት። በቃኝ!

  4. Ethiopia need a very dynamic and experienced leader not a motivational speaker. Abye don’t have experience and capability to lead the country , even if the magnitude of the crises was savior when he took over, rather than fixing it he is making it worst . The economy is getting deteriorated , Managing The a very complicated social dynamics and a country a center of the geopolitics , can’t be managed by wish full thinking .As he says he loves Ethiopia ,The best thing he can do t organize a platform for the Ethiopian to come up with a road map and let them decide the way moving forward , He should hand over the leadership to a matured and experienced leaders

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share