የኢትዮጵያ አማሮች የዘመኑ አይሁዶች – ለምለም ፀጋው

እስኪ ልጠይቃት ኢትዮጵያን ምን ነካት፤?
አይኖቸ እያዩ እንደ እናት አልችልም ፍጹም ጸጥ ማለት።

በግብጽ ተጀምሮ እስከ ክርስቶስ ልደት፤
በጀርመን በሂትለር ድግሞም በሌላ አህጉራት፤

ተጨፍጭፈው ነበር የአይሁዶች አባላት።
እኔ አይደለሁም ይህን ያወራሁት፣
ተምዝግቦ አለ ክፍታችሁ አንብቡት።

“ግብፃውያንም የእስራኤልን ልጆች በመከራ ገዙአቸው።…
እናንተ የዕብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፥
ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፥
ወንድ ቢሆን ግደሉት ሴት ብትሆን ግን በሕይወት ትኑር።
… ፈረዖንም የሚወለደውን ወንድ ልጅ ሁሉ ወደ ወንዝ ጣሉት፥

ሴትን ልጅ ሁሉ ግን በሕይወት አድኑአት ብሎ ሕዝቡን ሁሉ አዘዘ።

ሴቲቱም ፀነሰች፥ ወንድ ልጅም ወለደች፤ … ሦስት ወር ሸሸገችው። ደግሞም ልትሸሽገው ባልቻለች ጊዜ፥

የደንገል ሣጥን ለእርሱ ወስዳ ዝፍትና ቅጥራን ለቀለቀችው፤
ሕፃኑንም አኖረችበት፥ በወንዝም ዳር ባለ በቄጠማ ውስጥ አስቀመጠችው።…” (ዘጸአት 1፡13-20 እና 2:2-10)

የአይሁድ ልጅ የሱስም ሲወለድ የሆነው ተነጽፏል፤

ሄሮድስ ንጉሱም ፈረዖን እንዳደረገው ሕፃናትን አርዷል።

የአይሁድ እናቶችም እጅግ አንብተዋል፣
ዛሬም የኢትዮጵያ አማሮች የዘመኑ አይሁዶች
ሊጽናኑ አልቻሉም በእንባቸው ታጥበዋል።

“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በራማ ተሰማ፤
ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤
የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን እንቢ አለች።” (ኤርምያስ 31:15)

እላንት የሰው ልጆች እስኪ ያንን ታሪክ ንገሯት፤

ያጽናናት እንደሆን ያችን የአማራ እናት።

ያአይሁድን ጭፍጨፋስ ታሪክ መዝግቦታል፤

በዋሽንግተን ዲሲ ትራምፕ በነገሰበት፣
ድርጊቱ እንዳይደጋገም ሃውልት ተሰርቷል፤
እዩ ተመልከቱ የዘመኑ አማሮች አይሁዶች ሆነዋል።

እስኪ ልጠይቃት እነሡ ራሳቸው አገሪ የሚሏትን፤

በጣሊያን ወረራም በዱር በገድሉ የተሰውላትን።

ኢትዮጵያን ምን ነካት፤?

አማሮች እንደ ከፍት ሲታረዱ እያየሁ፣
እንደ እናት አልችልም እንዲያው ጸጥ ማለት፤
ደግሚም ልጠይቃት አገሪን ኢትዮጵያን ከቶ ምኑ ነካት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሦስቱ የሰው ዓይነቶች በጥንታዊ የግሪክ ፈላስፋዎች አገላለፅ  (ትርጉም:ዘ-ጌርሣም)

ተው አትከልክሉኝ እኔ ላልቅስላት፤

“አይጥ በበላ ያው ዳዋ ተመታ” እንዲሉ፣

ስደቱ ፍንቀላው ግድያው በዝቶባት፣
በዚአያች በአማራ እናት፤
በአይኖቸ እያየሁ በጀሮም ሰምቸ፣

እናት በመሆኔ አልችልም ጸጥ ማለት።
ተው አትከልክሉኝ
ሌላ ማድረግ ባልችል እኔ ላልቅስላት።
አገሪ ኢትዮጵያ ምኑን መርዝ ጠጣሸው፣

እርሃቡስ ቢበዛ ምኑን ምርዝ በላሽው፤

ለቀብር ዳርጎሻል ከሆድሽ ያደገው።
ተው አትከልክሉኝ ለዚያች ለአማራ እናት፤

ሌላ ማድረግ ባልችል እኔ ላልቅስላት፤

በጎጧ ባሐገሯ ልጆቿን እያየሁ ሲያርዱባት።

 

© Lemlem Tsegaw, October 25, 2020

Tsegawlemlem853@gmail.com

 

 

1 Comment

  1. ወገኑን እንደ ቅርጫ ስጋ ቆራርጦና መኖሪያ ቤቱን አቃጥሎ የሚጨፍር የእንስሳ መንጋ በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙት በደል ጣራ ከደረሰ ቆየን። ያው ከአንድ የሞት ዘመን ወደ ሌላው እየተላለፈ የአማራ ህዝብ ከደርግ ዘመን ጀመሮ በደርግ ውስጥ በተሰገሰጉ የወያኔ፤ የሻቢይ፤ በሌሎች ተለጣፊ ቡድኖች ሲመነጠር የኖረ ህዝብ ነው። ይህ አሰራራቸው በሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ በስደት ላይ ያሉትንም ያካትታል። አማራው ሃገር ሃገር ኢትዮጵያ ገለ መሌ ሲል እነርሱ ከሥር ከሥር ኢትዮጵያን ሲያጠለሹ፤ አጋር አፍራሽ ሃይሎችን ሲደግፉና ድጋፍ ሲጠይቁ ኖረው ሻቢያ በአስመራ ወያኔ በአዲስ አበባ አለቆች ከሆኑ በህዋላ ደግሞ ይህ ነው የማይባል ግፍ በምድሪቱ ላይ ተፈጽሟል። አሁን መቀሌ ላይ መሽጎ ኡኡታ የሚያሰማው የወያኔ የሙታን ቡድን በስውርና በግልጽ የፈጃቸው አማሮች ቁጥር ከክዋክብት ቁጥር ይበልጣል። ዛሬ በትግራይ ከምድር በታችና ከምድር በላይ የግልጽና የድብቅ እስር ቤቶች እልፍ እስረኞች ሰቆቃ ውስጥ ናቸው። ከ 60 አመት በህዋላ ዛሬም ግን ወያኔ መግለጫን በመግለጫ እያማታ ኑ እና ግጠሙኝ ማለቱ ምን ያህል የፓለቲካ ወስላታ እንደሆነ ያሳያል። የራሱን የሥልጣን ጥም ለማርካት የትግራይን ህዝብ እሳት ውስጥ መክተት የተካነበት ብልሃቱ ነው። የአማራ ህዝብን ጥላቻ መሪ አቋም አርጎ ይራመድ የነበረው ሻቢያ ወያኔንም ጋተው እና ወያኔ ጭራሽ በአማራ ጥላቻ ሰክሮ በሚሊዪን የሚቆጠሩ ዜጎችን እንደ ጨፈጨፈ በጊዜው ለፓርላማ በቀረበው የህዝብ ቆጠራ ውጤት ተገልጧል። ወያኔ ማፊያ ነው። ድርቡሽ ነው። ሂትለር ነው ስንል ዝም ብሎ ያልሆነ ስም ለመለጠፍ አይደለም። ሥራቸው ይመሰክራል። በጉግል ሰርች ” ሞቶ መነሳት” የሚለውን የካፒቴን ተሾመ ተንኮሉን እውነተኛ ታሪክ በማንበብ ብቻ ወያኔ አራዊት መሆኑን መረዳት ይቻላል።
    አሁን እንሆ ወያኔን በዚህም በዚያም ገሸሽ ያረገው የኦሮሞ የፓለቲካ ብልሃት ዞሮ ተመልሶ ወያኔን እየመሰለ መሄድ ከአንድ ኮሮጆ የወጡ እባቦች መሆናቸውን ያሳያል። ድሮም አማራ፤ ዛሬም አማራ፤ ወደፊትም አማራ ነው የሻቢያ፤ የወያኔና የኦሮሞ ጠላት። የጠባብ ብሄርተኞች በሽታ። ሰው በሰውነቱ ሰው ሆኖ የመኖሩ ተስፋ በምድሪቱ አክትሟል፡ የክልልና የቋንቋ ፓለቲካ አንድን ከሌላው ጋር እያላተመ ሁሉም ሃገር ለመሆን እየሞከረ ነው። ዘሩና ሃይማኖቱ ተጠይቆና ተጠንቶ ግድያና ዝርፊያ በሚፈጸምባት ከቁርስራሽ ተራፊ ሃገር ገና አያሌ ገመና ይጠብቃታል። ግን ችግሩን የምናመነጨው እኛው ነን። ገዳይን የማይገድል መንግስት ህግን ሊያስከብር አይችልም። የኦሮሞ የፓለቲካ እብደት ልክ የለውም። ኦሮምኛ ካልተናገረ አትገበያዪ የሚሉ ሙት ፓለቲከኞች ባሉበት ሃገር መማርም ማስተማርም ጭራሽ አይቻልም። ተው ስትለው የሚብስበት የሰው የአንበጣ መንጋ የሚንጋጋባት ምድር ናት። ግድያው ዝርፊያው ማሳደድ በአማራ ተወላጆች ላይ ዛሬ ይሁን እንጂ ነገ ኦሮሞው እርስ በእርሱ እንደሚገሻለጥ የታወቀ ነው። የሰውን ደም አፍሶ በሰላም ማንቀላፋት አይኖርም። የአማራ ህዝብ ጅልነቱን ይተው። ጠላትና ወዳጁን ይለይ። ውጊያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያንን ለማጥፋት ያቀደ ነው። ፍልሚያው የተጠናና የተነደፈ ነው። እንዲሁ እንደሚነገረን በሁለት ሰዎች ጥል የተነሳ አይደለም። የክልል ፓሊሱ፤ የልዪ ሃይሉ፤ የአስተዳደር መዋቅሩ ሁሉ በግልጽና በስውር የተሳተፈበትና የሚሳተፍበት ነው። የኦሮሞን የፓለቲካ አክራሪዎች በውጭም በውስጥም የሚፈጽሙትን በደል ዶኮሜንታሪ ሰርቶ በአለም ላይ መርጨት ነው። ጉዳቸውን አለም ይየው። የአማራ ህዝብ ተባብሮ ራሱን መከላከል አለበት። ይህ የክልል ፓለቲካ አፓርታይድ በመሆኑ ገና እልፍ ሰው ሲናኮር እናያለን። የቋንቋው ጦርነት ገና አልተፋፋመም። ይቀጥላል። አሮጊትና ህጻናትን ነፍሰ ጡር ሴትን የሚገል የጎሳ ስብስብ ቋንቋ ባፍንጫዬ ይውጣ። ልማረው አልፈልግም። በቃኝ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share