በቦሌ አየር መንገድና በጎንደር የሚሰማው ወሬ ጥሩ አይደለም! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ (ma74085@gmail.com)

ሁለት መሠረታዊ ቁም ነገሮችን ላነሣ ነው ከግላዊ የወሸባ (ኳራንታይን) ሥፍራየ ብቅ ያልኩት – እንዲያውም ሦስት ይሁኑልኝ፡፡ እንደምን ሰነበታችሁ ወዳጆቼና ውድ አንባቢዎች፡፡

ከቦሌ አካባቢ ስለሰማሁት አስደንጋጭ መረጃ ልንገራችሁ፡፡ የሚመለከተው አካልም የእርምት እርምጃ እንዲወስድ በዚህ አጋጣሚ ላስታውስ፡፡ ማንኛውም ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር የሚገባ ሰው ለ14 ቀናት ተገልሎ በህክምና ክትትል እንደሚቆይ በመንግሥት ታውጇል፡፡ ይህ ህግ ደግሞ ማንኛውንም ዜጋ ይጨምራል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በጣም ግልጽ ነው፡፡ በሽታው ማንንም ከማንም እንዳለመለየቱና ሁሉንም እንደማጥቃቱ የመከላከል እርምጃውም ሁሉንም ማካተት ይኖርበታልና አንዱን ከአንዱ እየመረጥን አድልዖ ብናደርግ በአንገታችን ላይ ገመድ መጠምጠም ነው፡፡

የአየር መንገድ ሠራተኞች በረራ አድርገው ሲመለሱ በቀጥታ ወደ ቤታቸው እንደሚሄዱ ነው ከታማኝ የመረጃ ምንጭ የሰማሁት፡፡ ይህ ለምን ይደረጋል? እነዚህ ሰዎች በቫይረሱ ቢያዙ ቤተሰባቸውንና ጓደኞቻቸውን ይበክላሉ፤ ቤተሰባቸው ቢበከል አካባቢያቸውም ይበከላል፡፡ ሥሌቱ ቀላል ነው፡፡ ይህ ነገር ታጥቦ ጭቃ እንደማለት ነው፡፡ በአንዱ አቅጣጫ ለማገድ እየሞከሩ በሌላ አቅጣጫ እንዲዛመት የመፍቀድ ያህል ነው፤ጉዳዩ እጅግ አሳሳቢ ነው፡፡ ገንዘብ ተፈልጎ ጤንነትም ተፈልጎ አይሆንም፡፡ አንዱን መምረጥ ነው፡፡ “አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ” ነው ነገሩ፡፡ በእስካሁኑ ሁኔታ አንድ ሦስት ያህል ሆስተሶች በቫይረሱ እንደተያዙ ይነገራልና ይታሰብበት፡፡ ቅጥ  ያጣ የገንዘብ ፍቅር የሚያስከትለው ችግር ካልታሰበበት መዘዙ ለነተወልደም መትረፉ አይቀርም፡፡

ስለሆነም አየር መንገዱ ባለው ሆቴል ውስጥ ለበረራ የሚልካቸውን ሠራተኞች ለተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ማቆየት ይኖርበታል እንጂ ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ ማድረግ አይገባውም፡፡

ሌላው የአደባባይ ምሥጢር የዶ/ር አቢይ መንግሥት የዓለምና በተለይም የኢትዮጵያውያን የትኩረት አቅጣጫና ወቅታዊ ጭንቀት ኮሮና ላይ መሆኑን ከመገንዘብ አኳያ ይመስላል የአማራውን አካባቢ ለተጨማሪ ጭንቀት ዳርጎታል፡፡ ይህ ፋኖን ምክንያት በማድረግ ክልሉን የጦርነት ቀጣና የማድረግ ወቅትን ያልጠበቀ ድርጊት ዓላማው ምንም ይሁን ምን መጨረሻው ግን አያምርም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰውየው (የመጨረሻ ክፍል) ከይገርማል ታሪኩ

ዛሬ ወቅቱ የጸሎትና የምህላ ነው፡፡ ዓለማችን አይታው በማታውቀው ወረርሽኝ በአራቱም አቅጣጫ ተወጥራለች፡፡ ጭንቀታችን “ይህ ወረርሽኝ ይጨርሰናል ወይንስ በቀላሉ ጎሻሸሞ ይተወናል?” የሚል እንጂ ስለወደፊት ዕቅዶች በሃሳብም ይሁን በግብር የምንዋትትበት አይደለም፡፡ በዚህ ወረርሽኝ ሰበብም የፖለቲካና የግል ፍላጎቶቻችንን ለማሣካት መዳከር አይጠበቅብንም፡፡ አንዳንዴ አእምሯችንን በትክክል ብናሠራው ካላስፈላጊ ትዝብት እንድናለን፡፡ ሰው እንሁን፡፡

በክረምት ወቅት ዐይጥና እባብ ላይነካኩ በደመ ነፍስ ተስማምተው ክፉውን ጊዜ በሰላም ያሳልፋሉ ይባላል፡፡ ክፉ ዘመን ሲመጣ በነፍስ የሚፈላለጉ ባላንጣ ወገኖች ጊዜያዊ የተኩስ አቁም አድርገው የጭንቅ ቀንን ይዘልቃሉ፡፡ የአማራ ጠላቶች ግን ይህን አስከፊ ወቅት እንኳን ሊታገሱ የቻሉ አይመስሉም፡፡ የአማራ መኖሪያ ብለው የፈረጇቸውን ሥፍራዎች ለማተራመስ ይህን ወቅት መርጠዋል፡፡ ይህም የሚጠቁመው አማራው ዕንቅልፍ የማይወስዳቸው ጠላቶች ያሉት መሆኑን ነው፡፡ በዚህ ጊዜ እንኳን ካላዘኑለት መቼ እንደሚራሩለት መረዳት አስቸጋሪ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡

እርግጥ ነው – በፋኖ ስም የሚንቀሳቀሱ መጥፎ ሰዎች ይኖሩ ይሆናል፡፡ በፋኖ ስም ወንጀል የሚሠሩ ዋልጌዎች አይኖሩም አይባልም፡፡ ግን ግን ይህን መጥፎ ወቅት እንደ ጥሩ አጋጣሚ ተጠቅሞ “ሰሊጥ ውስጥ የተገኘሽ መጭ አብረሽ ተወቀጭ” እንዲሉ የአማራን ደጀን ፋኖን ለማጥፋት መሞከር የዞረ ድምሩ ከባድ ነው፡፡

ሦስተኛው ነገር አሁን በዚህ ወቅት ሳይቀር አዲስ አበባ አካባቢ አማራን ለማፈናቀል የሚደረገው የዕብድ አክራሪ ኦሮሞ ባለሥልጣናት ተግባር ነው፡፡ በአሥራት ቴሌቪዥን እንደተከታተልኩት እነኚህ ተረኛ ነን ባዮች አማሮችን እያሳደዱ ቤታቸውን በማፈርስና ንብረታቸውን በማቃጠል ለወረርሽኙ ይበልጥ ተጋላጭ እንዲሆኑ እያደረጓቸው ነው – ሊያውም በኦሮምኛ እየዘፈኑ “እዚህ አካባቢ አማራ መጥፋት አለበት!” በሚል መፈክር ታጅበው፡፡ ይህንን ድርጊት የአቢይ መንግሥት አያውቅም ማለት አንችልም፡፡ በሌላም ወገን የአቢይ ታዛዦች በሚያስተዳድሩት የአማራው አካባቢም በአሁኑ ወቅት ቤት እያፈረሱ አማሮችን ለጎዳና ሕይወት መዳረጋቸውንም  እየሰማን ነው – ማፈናቀሉና ቤት ፈረሳው በዚያው በአማራው ክልልም መከናወኑን ልብ ይሏል፡፡ ሰው የሆነ ሰው በዚህን ወቅት እንደዚህ ያለ ነገር አያደርግም፡፡ አማራን የማሳደድና የማጥፋት ዘመቻ በወያኔ ታቅዶ ላለፉት 30 ዓመታት ጫፍ በደረሰ መልኩ ተግባራዊ ቢደረግም አሁንም በባሰ ሁኔታ በአዲሶቹ ጌቶች አማራው ስቃዩን እየበላ ነው፡፡ ለበጎ ነው! መከራን ያላስቀደመ ድል የለም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ‹‹አድርባይነት›› የወያኔ/ኢህአዴግ መለያ ባህሪው ነው።‹‹አድርባይነት›› ምን ማለት ነው?

ስለአማራነት ትንሣኤና ተዛማጅ ጉዳዮች አሁን ጭንቅ ላይ ሆነን ምንም ማለት አልፈልግም፡፡ ግን በተስፋ ልለያቸሁ ወደድኩ፡- ይህ ወረርሽኝ ያደረገውን አድርጎ ያልፋል፤ ሁሉም ወገን ደግሞ የሥራውን ያገኛል፤ ተንጋለህ የተፋኸው ካንተው ውጪ ወደየትም አይሄድም፡፡ አማራው ጋር ጠብ ያላችሁ ወገኖች ግን ወደ ቀልባችሁ ተመለሱ፡፡ ገድላቸሁ የማትጨርሱትን ኃይል ለመግደል መሞከር ጣጣው ብዙ ነውና ለጊዜው ኮሮና ላይ አተኩሩ፤ እናተኩር፡፡ ደግሞም በአንድ ወገን ጸሎት በአንድ ወገን ጦርነት ትራጂ-ኮሜዲ ዓይነት ቧልታይ ድንቃይ የፋርስ ትያትር ነውና በመከራ ወቅት ልታስቁን አትዳዱ፡፡ ያዋጣል ካላችሁም መንገዳችሁን ጨርቅ ያድርጋላችሁ – የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም፡፡ እኔ ግን ተናግሬያለሁ – የተናገርኩትም ለማንኛውም አማራ ጠል አክራሪ እንጂ ለእገሌ ወይ ለእገሊት እንዳልሆነ ማሳሰብ እፈልጋለሁ፡፡ መልካም የhibernation ዘመን! ዘመነ aestivation ደግሞ መምጣቱ አይቀርም፡፡ ያኔ ግን ብዙ ግሳንግስ ተወግዶ … ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል… ለምንደርስ ብዙ መልካም ዜና ነበረኝ… ግዴለም … ብቻ ያድርሰንማ፡፡

የነጃዋርን ትዕቢት፣ የነበቀለ ገርባን ዕብሪት፣ የነዶ/ር ገመቹን ትምክህት፣ የነፕሮፌ. መረራን እስስታዊ ባሕርይ፣ የነዳውድ ኢብሣን ጎጠኝነት … የነእስራኤል ዳንሣን “ተዓምር ሠሪነት”፣ የነ “ንግሥተ ነገሥታት እህተ ማርያም” ስንዱንና መሰል ሥራ ፈት የሰይጣን ባርያዎችን አጋንንታዊ መተት አፈር ደቼ አብልቶ ሁሉንም በየጓዳው የወተፈና ዶሮ ጠባቂ ያደረገ አምላክ ክብሩ ይስፋ፡፡ እርሱ ጠፍጥፎ የሠራው ይመስል “ከክልሌ ውጡልኝ!” ይል የነበረን ጎጠኛ ሁሉ ደጁ ሳይቀር እንዲናፍቀው ያደረገ አምላክ ምሥጋና ይድረሰው – (ኮሮናዬም ልጅ ይውጣለት!)፡፡ ደግሞም ገና ምኑ ተነካና! ከዚህች 4 በመቶ እንኳን የመግደል አቅም ከሌላት ትንሽዬ ቁንጥጫ ወደ 80 እና ከዚያ በላይ የመግደል ኃይል ወዳለው መቅሰፍት እንሸጋገራለን – የላይቴ ላይ በል ያለኝን አልኩ፡፡ መትረፊያው አሁን ለኮሮና የሚነገረውና በተወሰነ ደረጃም እውነት መሆኑ ሊካድ የማይገባው ውኃና ሣሙና እና አካላዊና ማኅበራዊ መራራቅ ብቻ እንዳይመስልህ፡፡ ንስሃና ጸጸት ብቻ ነው፡፡ ያ ከሰው ልጅ ሥልጣኔ በላይ የሆነ ቀን ጅማሬው በጉልኅ እየታዬ ነው፡፡… ልብንና ኩላሊትን የሚቀይር የዘመናችን ሥልጣኔ በቤተ ሙከራ ራሱ የፈጠረውን ተራ ጉንፋን ማከም አልቻለም፡፡ ይህም ብቻ አይደለም –  ለሌሎች የፈጠረው ወረርሽኝ በራሱ ጓዳ ግዘፍ ነስቶ ሽዎችን በየቀኑ ሲያጭድ ፈዝዞ ከማየት ውጪ አንድም አልፈየደም – ቀን አይጥልም አንበል፤ ይጥላል፡፡ አዎ፣ የማይታመነው ትያትር መሰል የዓለም ፍጻሜ በሙሉ ግርማ ሞገሱ ጀምሯል!!

ተጨማሪ ያንብቡ:   መቻልህ ፣ ማለፍህ ፤ ካሥጠቃህ ፤ ምን ትጠብቃለህ ?! ( አባታጠቅ   ምንዳሁንኝ )

20 Comments

  1. “የአየር መንገድ ሠራተኞች በረራ አድርገው ሲመለሱ በቀጥታ ወደ ቤታቸው እንደሚሄዱ ነው ከታማኝ የመረጃ ምንጭ የሰማሁት፡፡” You are right, and I have also confirmed it from genuine sources. Your information sources are plausible. Keep it up!

  2. This devil-incarnate so called Abiy is surely digging the grave of Ethiopia. Following the suit of TPLF, OPDO and its servant ANDP (ብአዴን) are trying to eliminate the Amhara. It is wonderful to learn that every body is silent while these crooked satans are committing such gigantic genocide in the Amhara region.

  3. ጉዱ ካሳ ካንተ አዉቃለሁ ብዬ አይደለም መቼም ተወልደ የሚባል ወንጀለኛ ትግሬ አየር መንገዱን ሳይሆን አገሪቱን ይዞ ካልወረደ ነብሱ እረፍት አታገኝም። አየር መንገዱ ብዙ አስነዋሪ ስራዎችን ሲሰራ እንደነበረ በብዙ መረጃ ተመልክተናል። እነ አባይ ጸሀዬ በርታ እያሉት ገና ብዙ ነገር ታያለህ አንተ ግን መሪዎቹ ሰሙህም አልሰሙህም ወገንን የማዳን ሓላፊነት ስላለብህ ያየኸዉን የታዘብከዉን ወደ ህዝቡ አድርስ። ባለፈዉ ሸገር ላይ ቀርቦ ከስራ ብዛት ምግቡን ወደ ቢሮዉ ሲሄድ መኪና ዉስጥ እንደሚበላ ነበር ከመአዛ ጋር እየተቀባበሉ የነገሩን ። እንደሱ አይነት ወንጀለኛ ለጥያቄ ጋዜጠኛ ዘንድ ሲቀርብ አንጀቱ ላይ ቁሞ ለምን እነ እከሌን ከስራ አባረርክ? ለምን ዘርን ያተኮረ ጥቃት ወገን ላይ ትፈጽማለህ? ዉጭ አገር አለህ ሰለሚባለዉ ደርጅትና ንብረት አዎንታ ወይም ማስተባበያ ለኢትዮጵያ ህዝብ መስጠት ትችላለህ? እየተባለ መጠየቅ ሲገባዉ እሱ ግን ፐብሊክ ኢሜጂ ሰርቶበት አልፏል ኢትዮጵያ ካለች አንጀቱ ላይ ቁሞ የሚጠይቀዉ ጋዜጠኛ ይመጣል።፡ለነገሩ ዲማ ነገዎ፤አረጋዊ በርሄ፤ጁዋር መሀመድ…..ባልተጠየቁበት አገር ማን ይጠየቃል?
    ኢትዮጵያን አምላክ ይጠብቅ

    • ሰመረ የምትባለው ሰው አብዛኛዎቹ ኮሜንቶችህ በትግራይ ተወላጆች እና ባለስልጣናት ፍፅም ጥላቻ፤ ዘረኝነት የሚያንፀባርቁ ናቸው አሁን አቶ ተወልደ ከዶ/ር አብይ ትእዛዝ ይወጣል ብለህ ትገምታለህ በረራዎች ሁሉም ይዘጉ፤ ይቁሙ ቢባል ማን የሚወስነው የሚኒሰትሮች ምክር ቤት ነው ስለዚህ ሰው እንድ ሰውኛ እንጂ በብሄሩ መወቀስ የለበትም እዚም እዛም አጥፊዎች አሉ ስንፈርድ ሚዛናዊ ፍርድ ይሁን ነገሩ አትፍረድ ይፈረድባሀል ነው

  4. ዳግማዊ ጉዱ ካሣ ሆይ!
    ግላዊ ወሸባዋን አዲስ ቃል ተማርኩኝ። አመሰግናለሁ። እስቲ ባለፈውም እድሉን ያጣሁበትን ጉዳይ ከዚሁ ቶፒክ ሳልወጣ የመሰለኝን ከግርጌ እላለሁ። እዚህ ባነሳሀቸው ነጥቦች እስቲ እንዲህ ልበል በመጀመርያ።

    ፩) የአየር መንገድ ሰራተኞች ቀጥታ ቤት ስለመሄድ፣
    ሁሉን ነገር በክፋት ካላየነው በቀር ቤት ከሄዱ በሁዋላ ምን ክፍል እንደሚተኙ ያያቸው አለ? ለዚህ መከራ ጊዜ ተብሎ የተለየ ግቢ ውስጥ ሆኖ ራቅ ማለቱን ማን አየ ወንድሜ? መቼስ ቤተሰባቸውን አይናቸው እያየ አይጨርሱም ከሚል ነው። አየር መንገድ አስተዳደር እንኳ ቤታችሁ ሂዱና ተኙ ቢላቸው የሚያረጉት አይመስለኝም የለየላቸው ጽልመቶች ካልሆኑ በቀር። ቤት መሄዳቸው የልጆቻቸውን፣ ሚስቶች/ባሎቻቸውን ድምጽ ከርቀት መስማቱም ተስፋ ነው። በየግላቸው በየቅጥርግቢያቸው “ወሸባ” ከገቡ ብለህ አስበሀል? የነዚህንስ ሙያተኞች ኢንተሊጀንስ መስደብ አይሆንም ወንድም?

    ፪) የዶር አቢይ መንግስትና አማራዎች ወይም ፋኖዎች

    ይህ ጉዳይ ትንሽ ቅንነትን አልላበስ ስላለ እስቲ እኔም እንዲህ ልበል። ፈጣሪ በሚያውቀው ለህሊናዬ እንጅ የዘር ልክፍት ሲያልፍም አይነካኝ። ዶር አቢይ ባለፉት ብዙ ወራት ጦራቸውን ወለጋና ማንኛውም የሸኔ ሽፍታ በናኘበት ዖሮምያ ሲያዘምቱና ሲያጠሩ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ምነው ዝም አልክ? ይህ” በአማራው ህዝብ ላይ ዘመቻ” የምትለውን ሰውዬው እስካሁን ከሚሰሩት ስራ ሳየው ልረዳው ያልቻልኩት ነው ሚዛናዊ ሆኜ ካየሁት። መቼስ እንደምታውቀው ላለፉት ሰላሳ አመታት የ ህውሀት ሰዎች የአማራውን ክልል የራሳቸው “ፕሮቴክቶሬት” አድርገው እንደፈለጋቸው ሲያረጉት፣ በተለየ ሁኔታ ከዚያ ክልል የነሱን ፍርፋሪ የተላመዱ ብዙ ሎሌዎች ማፍራታቸው እሙን ነው። ዛሬ ዋንኞቹ በግዞት መቀሌ ሲከትሙ፣ የነሱ ብዛት ያላቸው አጫፋሪዎች የፋኖን ልብስ ተላብሰው በየአማራው ጋራና ሸለቆ ቢንሰራፉና እነዚህን ተንኮለኞች እያደነ መንግስት እርምጃ ከወሰደባቸው በመላው አማራ ላይ ተነሳ ሊባል ነው? ደግሞስ ይህን ኮሮና ከለላ በማድረግ የነዚህ ጽልመት ውላጆች ግድያውንና ተንኮሉን ቢያፋፍሙት አያይ” ኮሮና ስላለች ዝም ብለን ህዝቡን ሲያጫርሱ እንይ” ሊል ነው መንግስት? እንጅ ማን ይሙት አቢይ አህመድ ከአማራ ተዋልደው፣ ሳተና ጎንደሬ ባለቤት እቤት አስቀምጠው አማራን ለማጥፋት ልዩ ተልእክዎ እያካሄዱ ነው ለማለት በዚህ ምህላ ዘመን ለአይምሮዬ እጅግ ይከብደኛል። በምን ስሌት ይህ እውነታ ነው ብለህ በአደባባይ ልትግተን ትሞክራለህ ወንድም?

    ፫) በአዲሳባ ስለሚካሄደው የአክራሪዎች ሴራ ይሁን በማንኛውም ክልል ስለሚካሄደው የአክራሪዎች ክፉ ተግባር አገሪቱ ስለደረሰችበት የዘቀጠ ፖለቲካዊ እውነታ እንጅ ከ ዶር አቢይ ምልከታ ጋር እንዴት ይገናኛል? አቢይ ያሰማራቸው ሰራዊት አደሉም እኮ ወንድሜ ፣ ጊዜው የወለዳቸው ጠባቦች እንጅ ። ሁሉደግሞ በአንድ ጀንበር አይጸዳምና ቀስ እያለም ይሰክናል።

    በመጨረሻም እንዳልከው እነ አክራሪ ይሁኑ የጽልመት ውላጆች ኮሮና ልክ እስገብታ በየጉረኖው ወትፋቸዋለችና የአምላክን ስራ ባሁኑ ጊዜ አለማድነቅ ገልቱነት ነው። እኔ የሚታየኝ ከዚህ አስከፊ መቅሰፍት ከተረፍን አገራችን ጸድታ ወደፊት እመር ብላ እንደምትነሳ ነው። የዚህን ምርጫ መራዘም በዚች ኮሮና ምክንያት መሆኑ እጅጉን አስደስቶኛል በግሌ። ለምን? መጪው ሁለትና ሶስት አመታት የጎሳ ፖለቲካ በፈጣሪ ቸርነት ጉድጓድ የሚገባበት ዘመን በመሆኑ። ኮሮና ልብ ብለህ እንደሆነ የዜግነት ፖለቲካን እያስተማረች ነው። ሁለት ሶስት እመት በሁዋላ በተለይ ወጣቱ ትውልድ በደንብ ግራጁዌት ያደርግበታል። በምኞት ደረጃ ለአገር እንዲተርፉልን የምፈልገው ወጣቱን ትውልድ እንጅ የኔ ቢጤውን፣ አይደለም (ከተረፍን እሰየው። ልጆቻችንና የልጅ ልጆቻችን ይቅደሙ ብዬ ነው)። እናም ዳግማዊ ጉዱ ካሣ ሆይ ሚዛናዊ ሁን ዶር አቢይ ላይ። ሰው እንዴት ግማሽ አከላቱን ይጠላል ብለህ አስብ እንጅ ። አማራን ጠልቶ አገር ያስተዳድራል ብሎ ለመቀበል ይከብዳል በጣም። አክራሪዎቹ የሚሉትን ብትሰማ ደግሞ አጃኢብ ያሰኝሀል ። እስቲ ፈጣሪ ይታረቀን እንደ ቸርነት እንጅ የኛስ ነገር እያደር ያሳስባል። ሰላም ሁን ባለህበቱ።

    • አባዊርቱ ወንድሜ ግሩም ግሩም ሃሣቦችን ሰንዝረሃል፤ አስተማሪና አስታዋሽ ናቸው።
      ወሸባ የምትለዋን ቃል በተመለከተ እንዲያው በደፈናው “ጉሮ ወሸባየ፣ ጉሮ ወሸባ” በሚለው ባህላዊ ዘፈን ከምሰማው ውጭ ትርጉሙን አላውቀውም ነበር። በቅርቡ ነው ወዳጄ ፕሮ. ፍቅሬ ቶሎሣ በfb ገጹ ያስተማረኝ። ምኔ ሞኝ ወዲያው ተጠቀምኩባት።
      ወንድሜ አባዊርቱ ብዙ ነጥቦችን ነው ያነሣኸው። እኔ የምጽፈው አውቀዋለሁ ስለምለው ጉዳይ እንጂ ብሔረሰባዊ ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር አስቤው አላውቅም። እኔ የማውቀውን ከጻፍኩ፥ ሌላው ለምሣሌ አንተ የሚያውቀውን ከጻፈ ጉድለታችን ይሟላል። እኔ ለተበደለ የማይራራ ልብ የለኝም። ወለጋ ውሥጥ ስለታገቱት ልጆቻችን ጬሄያለሁ፤ ስለአክራሪ ኦነጎች ጬሄያለሁ። ምናልባት ሁሉንም መጣጥፎቼን አላየህ ይሆናል።
      ስለአቢይና ሥለአማራ ክልል ሆድ ይፍጀው ማለቱ ይቀላል። ጊዜና ፈጣሪ ይግቡበትና መፍትሔውን ይሥጡ እንጂ ሁኔታዎች ከወያኔው ዘመን ባልተናነሰ መልክ ክልሉና አመራሩ ለአቢይ ፍላጎት የሚያሸረግድ ነው። የዕይታ አቅጣጫ ጉዳይ ነው። ከሚያጥበረብሩ ነገሮች ራቅ ብለን በሃቅ ካየን የአማራው ክልል በብዙ መንገድ እየታፈነ ነው። ፋኖን ብናይ አጥፊን ለይቶ ለህግ ማቅረብ ሲቻል በደፈናው ልምታ ብሎ ሀገር በውጭ ኃይል የተወረረች ያህል ታንክና መድፍ መሀል ከተሞች ላይ ማርመስመስ ምን ያህል ትክክል እንደሆነ ራሥህ ፍረድ። ደግሞስ ይህ ወቅት ለምን ተመረጠ? ነገሩ መስቀል ከቀላጤ እንዲሉ ነው፤ በአንድ ዕጅ መስቀል በሌላ ዕጅ ሽጉጥ። እግዜርስ ጸሎትና ምህላችንን እንዴት ይስማ?
      ዛሬ እየተሠራጨ ያለ የነታከለ ኡማን እጅግ አሣፋሩ ገመና ደግሞ ልንገርህ። አማራን ከአዲስ አበባ እያፈሱ ወደጎንደርና ባህርዳር እያጋዙ ነው። በዚህ የጭንቅ ቀን እነዚህ የሁላችንም ናቸው የምንላቸው ወንድም እህቶቻችን እየሠሩት ያለው ሁሉ ዕብድ ሰው እንኳን አይሠራውም። ይህን መጥፎ ሥራቸውን ለጊዜው ጉልበታቸው ሊሸፍነው ይችል ይሆናል፤ የድሃንና የተበዳይን ዕንባ የሚያብሥ ፈጣሪ መኖሩን ግን መርሣት የለብንም።
      ብዙ አጫወትኩህ ወንድማለም። ከሚተርፉት መድቦን ከአድማሥ ወዲያ ማዶ በአዲስ መልክ በምትወለደዋ ኢትዮጵያ ተገናኝተን ብንጫወት ደሥ ይለኛል። ያኔ ይህ ሁሉ የቂልነት ሥራ አይኖርም።

  5. ጉዱ ካሳ ጌታቸው ረዳ ነው አለኝ ውስጥ አዋቂ ሰው ። ዘሃበሻ ይህንን ለሕዝብ ማጋለጥ አለበት። ሁሉም ላይ ድንጋይ መወረወር የወያኔ ጸባይ ነው።

  6. Kassa kejaala ደህና ነህ? እንዴነህ?
    የትኛው ጌታቸው ረዳ? የሕወሓቱ ወይንስ ወዳጄ የኢትዮሰማይ ብሎግ አዘጋጅ? ግን ካሥቾ፥ ማንስ ብሆን ዋናው የሃሣቤ ሚዛናዊነትና ትክክለኝነት እንጂ ማንነቴ ምን ይሠራ(ልሃ)ል? ውሸት ከተናገርኩ በመረጃ ሞግት። እውነት ከተናገርኩ አትሞትም በጨዋ ደምብ ለሚዲያው ምሥጋና አቅርብ። በጉልበት ማሰብ ለሚዳዳው ሰው የሰው ማንነትን ለማወቅ ይጓጓል፥ ሥምን እያነሣ ጭቃ ለመቀባት። ካሥዬ፥ ከጠቀሥኳቸው ጌታቸው ረዳዎች የትኛውንም አይደለሁም።

    • አንተ ንገረን እንጂ ማንነትህን? እንደምታውቀው ሁለቱም ትግሬ መሆናቸው እንጂ አቋማቸው የተለያየ ነው። ከቀደም ጀምሮ የምትጽፈውን አንብቤለሁ። እንዴት አቋምህ እንደሚለዋወጥ ለማሳየት ከባድ አይደለም። በዚህ ምክንያትና በውስጥ አዋቂ ጥቆማ ነው ጌታቸው ረዳ ወያኔውን ትሸታልህ የተባለው። አንባቢያን ጉዱ ካሳ የሚጽፈውን ወደ ኋላ ሄዳችሁ ለማንበብ ሞክሩ። መፍትሄ ሳይሆን የህዝብን አንድነት ለመናድ ሲታገል ታገኙታላችሁ።

      • አንተ ካሣ የተባልክ ሰውዬ በፈጠረህ ተስተካከል! ራሥህ ተንሽፈህ ሰውን ለማንሻፈፍ አትሞክር። አንድም መረጃ ሣትጠቅስ “የሕዝብን አንድነት ለመናድ ሲታገል” የሚል መልእክት መናገር ነገ በነፃነት ዘመን ያሥከስስሃል። የዘረኞችን ገመና ማውጣት አንድነትን ለመናድ መታገል ነው? ከጽሑፎቼ የትኛው በምትለው ደረጃ እንደሚገኝ በአድራሻየ ላክልኝ። ነገሬ ከእውነት እንጂ ከጥቅምና ከዘረኝነት ጋር ፈጽሞ ንክኪ የለውም። ተሣሥቼ ከሆነ ለመታረም ዝግጁ ነኝ። በከንቱ ሥም ለሚያጠፋ ግን አልመችም። ሰቀር ይቀራል እንጂ ሀሰትን የምለማመጥበትና አዝዬ የምዞርበት አንቀልባ የለኝም። “በዱ በዲ መሌ ሰሬኤጀኒ ቀኒ” ይላል ያገሬ ባላገር “ሲጠፋ ይጥፋ እንጅ የውሻን ዐይን አያጥቡም” ለማለት። ፈረንጅን ባያይ ነው ለነገሩ። እነደመቀ መኮንንንም ጭምር!
        ካሣ ለኦነግና ኦህዲድ ስስ ልብ ሊኖርህ ይችላል፤ መብትህ ነው፤ አይገርመኝምም። ግን ሥትደግፍ በቅጡ ደግፍ። ንጹሕን ሰው ጭዳ በማድረግ የምትደግፍ ከሆነና ሰው ከሆንክ ነገ በሥራህ ታፍራለህ። ዘርን ፖለቲካን ተወው፥ ወደ ብርሃን ውጣ ወንድሜ። የኔ ምክር ያጥፋህ፤ አሁኑኑ ወደቀናው መንገድ እመር በልና እኛንም ይድነቀን። እሥከመቼ ሃቅን በሚደፈጥጥ የግል ዓለም ጎጆ ውሥጥ ተወሽቀህ ትኖራለህ? ለየትኛው ዘመን? ለዚህ ለኮሮናም ዘመን ብለህ ከእውነት ጋር ትላተማለህ? ኧረ ይቅርብህ! ሰው ስትሆን ልታገኘኝ ብትሻና ኮርዬ ካልቀደመኝ ምድራዊ አድራሻየ ይሄውልህ፥ ma74085/gmail.com

        • ጉዱ ካሳ አንተ ነህ እንጂ ስምህን ቀይረህ ለውጡን ለማክሸፍ ፡ ህዝብን አርስ በርስ ለማጣላት እንቅልፍ አጥተህ የምትጥረው ። የሚሉሽን ብተሰሚ ገበያ ባልወጣሽ። ቃላት መደርደር እውቀት እይደልም እኮ። እስቲ ደፍረህ ጌታቸው ረዳ ወያኔው አደለሁም በል። በኦሮሞኛ ተረት መጥቀስ ከትግሬነትህ አይፍቅህም ። አሁንም ለአንባቢያን ወድ ኋላ ሄዳችሁ ጉዱ ካሳ ( ጌታቸው ረዳ ወያኔው) የጻፈውን አንብቡ። ማን እንደሆነ ታውቁታላቸሁ። ኢሜል ጻፍልኝ የምትለው ከቻይና በገዛችሁተ ሶፍት ዌር ልተሰልለኝ ነው። ስለአንተ ያለኝን መረጃ ጊዜ ሲፈቅድ አጋልጠዋለሁ። አሁን ምንጬ አደጋ ውስጥ ስለሆነ እተወዋለሁ።

  7. አቶ ጉዱ ካሳ ስል አብይና ኮርኖ ቫየረስ የሚመስልህን ተናገርህ ፡ መናገር ጥሩ ነው ግን አንድ ትልቅ ያልነገርከን
    ጉድ አለ በጎንደር ከተማ ውስጥ የሽፈተ እራሱን አርበኛ ብሎ የሚጠራን የከተማን ወሮበላ ምነው በነካ ብዕርህ
    ሳትነግረን አለፍከው ? አንተም እንደ..ፈራሃችው? አብይን መውቀስ መክሰስና መስደብማ ቀላል ነው

    6 ህጻናትን አፍነው ወስደው የገደሉ የጭት መኪና ሾፈሮችን አፍነው ዎስደው ገንዘብ የሚቀበሉትን በለሊት ከብት እየዘረፉ ለሱዳን አሻግረው የሚሸጡትን በዘረፉት ገንዘብ ጠጅና አረቂ አየጠጡ የጎንደርን ከተማ ከምችቱ 8᎘9 ሰ
    አት ጀምሮ እስኪነጋ በጥይት ሲያናውጡ የሚያድሩትን ምነው አለፍካችው ? ሽፍትነት ከተማ ውስጥ ሆነ አንዲ እቶ ጉዱ አውንት ለመናገር እውቀቱም አድሚህም አያሳጥህም ፡ ለዚች አጭር አድሚህ ብለህ እውነትን አትፍራ እኛ ጀንበር በዎጣና በገባ የምንኖረውን ኑሮ ለአንድ ቀን መጥተህ ብታየው ሩቅ ሆኖእሉባልታና ስንክሳር ከውዲያ ዎዲህ ከማምታታት ይሻል ነበር ፣ ሲፈልጉ መንግስትን ህግ አያስከብርም ህግ ለማስከበር ሲሰራ እርሶና መሰሎችዎ መሰሎችዎ ያረጀ ቁራ ጩህታቹ ለጆሮ ይቀፋል፡ አምላክ ል+ቦ+ና= ይስታችሁ

  8. አቶ ጉዱ ካሳ ስል አብይና ኮርኖ ቫየረስ የሚመስልህን ተናገርህ ፡ መናገር ጥሩ ነው ግን አንድ ትልቅ ያልነገርከን
    ጉድ አለ በጎንደር ከተማ ውስጥ የሽፈተ እራሱን አርበኛ ብሎ የሚጠራን የከተማን ወሮበላ ምነው በነካ ብዕርህ
    ሳትነግረን አለፍከው ? አንተም እንደ..ፈራሃችው? አብይን መውቀስ መክሰስና መስደብማ ቀላል ነው

    6 ህጻናትን አፍነው ወስደው የገደሉ የጭት መኪና ሾፈሮችን አፍነው ዎስደው ገንዘብ የሚቀበሉትን በለሊት ከብት እየዘረፉ ለሱዳን አሻግረው የሚሸጡትን በዘረፉት ገንዘብ ጠጅና አረቂ አየጠጡ የጎንደርን ከተማ ከምችቱ 8᎘9 ሰ
    አት ጀምሮ እስኪነጋ በጥይት ሲያናውጡ የሚያድሩትን ምነው አለፍካችው ? ሽፍትነት ከተማ ውስጥ ሆነ አንዲ እቶ ጉዱ አውንት ለመናገር እውቀቱም አድሚህም አያሳጥህም ፡ ለዚች አጭር አድሚህ ብለህ እውነትን አትፍራ እኛ ጀንበር በዎጣና በገባ የምንኖረውን ኑሮ ለአንድ ቀን መጥተህ ብታየው ሩቅ ሆኖእሉባልታና ስንክሳር ከውዲያ ዎዲህ ከማምታታት ይሻል ነበር ፣ ሲፈልጉ መንግስትን ህግ አያስከብርም ህግ ለማስከበር ሲሰራ እርሶና መሰሎችዎ መሰሎችዎ ያረጀ ቁራ ጩህታቹ ለጆሮ ይቀፋል፡ አምላክ ል+ቦ+ና= ይስታችሁ

  9. Sebile Borena እና Abel Adugna በሚል ሁለት የሚለያዩ ሥሞች ከዚህ በላይ የቀረበውን አንድ ዓይነት አስተያየት አነበብኩት፤ ጥሩ ነው። የሥሞች መለዋወጥ የሚሰጠውን ፍካሬያዊ (connotational) ፍቺ ለጊዜው ትተነው በቁም ነገሩ ላይ ትንሽ ማለትን ወደድኩ፤ ምክንያቱም ዋናው ነገር የተነሣው ጉዳይ እንጂ በሥሞች ውሥጥ ለማስተላለፍ የሚፈለገው የማንነት ወቅታዊ መገለጫ ብዙም ሊያውከን እንደማይገባ አምናለሁ። እንዲያ ባይሆን ግን በወደድኩ።
    ለአባዊርቱ ያልኩትን አንብብልኝ ውድ ወዳጄ ቦረና ወይም አዱኛ። የማውቀውን በምንም ምክንያት አልደብቅም። ግፈኝነትና ኢፍትሃዊነት በየትም ቦታ ቢፈጸም በወገንተኝነት ተሸፋፍኖ ሊቀር አይገባም። ይህን አጭር መጣጥፍ ያነበበ ጤናማ ሰው ጸሐፊው ጎንደር ውሥጥ በዚያን ሰሞን ማንነታቸው ባልታወቀ ዐረመኔ የሰው ሰይጣኖች ታፍነው ተወሥደው የታረዱ ሕጻናትን ድርጊት ይደግፋል ብሎ ማመን የጸሐፊውን ማንነት ሆን ብሎ ለማጠልሸት የሚደረግ ከንቱ ሙከራ እንጂ ሚዛን አያነሣም። በዚህ ጽሑፌም ቢሆን በፋኖ ሥም መጥፎ ሥራ የሚሠሩ እንደሚኖሩ እነዚህን ግን ለይቶ ለፍርድ ማቅረብ እንደሚገባ ጠቅሻለሁ፤ ይህን ማለቴ እንኳን አልታየልኝም።
    ወንጀለኛን ለምን እደግፋለሁ? እኔን ማጥቃት ከተፈለገና ከላይም ከተፈቀደ ከአስመሣዩ አቢይና ከዳፍንታሙ ማይም የጎንደር ሽፍታ የትኞቹ ለኔ ይቀርባሉ?
    ስለሆነም ሰውን በጭፍን አንፈርጅ። የጎንደርንም ሆነ የሌላውን አካባቢ ሕዝብ ሰላም የሚያውኩና ንጹሓንን የሚገድሉ የሚዘርፉም ወንበዴ ዜጎች ወደህግ ቀርበው የሥቅላት ሞት ቢፈረድባቸውና ከነሱ ውሥጥ አንዱ ወንድሜ ቢሆን የቆመበትን በርሜልም ይሁን በርጩማ ገፍትሬ እንዲንጠለጠል ለማድረግ ሰውን ላለመግደል ለራሤ የገባሁትን የሞራልና የሃይማኖት ህግ እጥሣለሁ።
    ይህን ሁሉ ያልኩት በተዛዋሪ ዘረኝነትና የጥቅም ትሥሥር እውነትን የሚጋርዱ፣ ክርን ወይ ማተብን የሚያሥበጥሱ መጥፎ አሽክላ መሆናቸውን በመጠቆም ወደ እውነት እንድንጠጋ ነው። በተለይ በዚህን ፈጣሪ ወንበር ዘርግቶ በግልጽ እያሥተማረን ባለበት ወቅት ስለትክክለኛና ፍትኃዊ ፍርድ ካልተማርን መቼ ልንማር ነው?… ልብ ይሥጠን፤ እርሱ ይርዳን፤ እሳቱንም ያብርድልን። እኛም ከተሰቀልንባቸው የየግል ዓለማት ወርደን እንቀራረብ፤ ከጥላቻና በቀልም እንውጣ። ለዚች ላለቀላት የምድር ሕይወት በረባ ባልረባው አንባላ። ከተፋቀርን ለሁሉ የሚበቃና ለሎችም የሚተርፍ አዱኛ አለን። ካልተፋቀርን ድህነቱና ሥደቱ መዘባበቻነቱም እንደሥካሁኑ ሁሉ በስፋት ይቀጥላል። ዘረኝነት በተለይ ከማይምነታችን ባልተናነስ ትልቁ ጠላታችን ነውና እንጠየፈው። ነገር አበዛሁ… የብሶት ነገር…

  10. The organization that goes with the brand name “Ethiopian Airlines” is still Woyane Airlines , the Oromos let Woyane do whatever Woyane wants with the organization , as long as Woyanes throw advantages that recognizes it is Oromos elites turn to shine at the expense of everyone else.

  11. አንዳንዴ ከጅሎች መጃጃል “ጊዜን በአግባቡ ከመጠቀም አኳያ” መልካም ነው። ታቃለህ አቢይ ማለቴ ቀጀላ ምን ይባላል መሠለህ በትግርኛ ማለትም ባማርኛ “እኔውም ዕብድ ነኝ ከወፍ የገበየሁ፤ መቀመጧን እንጂ መብረሯን የታየሁ።” ሰው መሥለኸኝ፣ አንድ ኦነግ እንኳን አሣምኜ ወደ ሕዝባዊው ባቡር ልመልሥ ከሚል ቅን ግን ፍሬአልባ እሣቤ በመነሣት ብዙ ደከምኩ። ለነገሩ ይህን ያህል ካንተ ጋር መከናታቴ(መጃጃሌ ላለማለት ነው) በኮሮና ምክንያት ገና ለጡረታ ባልደረሠ ዕድሜ ቤት ስለዋልኩ እንጂ ይህን ያህል ጊዜ የተትረፈረፈኝ “ጌቾ” ሆኜ አይደለም። አየህ የፓርቲ ስብሰባ አለ፤ እንቅልፍ የሚነሣን የራያና ወልቃይት ነገር አለ፤ ከጓደኞቼ ከነሥብሃትና ከጌታቸው አሰፋ ጋር የማታው ቀዘፋና ያን ተከትሎ ከነእንኮዬ ጋር ሌሊቱን ወደ ገነት የመለወጥ ነገር አለ… ብቻ ቢዚ ነን ለማለት ነው።
    መረር እያልኩ ልቀጥል ነው፤ አዝናለሁ። ደንቆሮን ልኩን ካልነገርከው ይበልጥ የሚጎዳው ራሱ ነው።
    ቀጀላ ግን እውነቴን ነው የተዋጣልህ መንቻካና አንድም መረጃ ወደ አእምሮህ እንዳይገባ በባልጩት ድንጋይ የዘጋህ ነህ። ያንተ ወንድሞች ናቸው እንግዲህ ይህን 100 ምናምን ሚሊዮን ህዝብ እያወላገዱ በመግዛት ላይ ያሉት። ደግሞም ከመወለዱ የከሸፈን ለውጥ ተብዬ ልታከሽፍ ትለኛለህ – ወግ የሚያምርህ ወገኛ! “ሲወልዱ አይታ ‘ካካዋን ካካች'” ይባላል። ጌታህ አቢይ ለውጥ ሲል ሰማህና አንተም በበላህበት ለውጥ አለመኖሩን ልቦናህ እያወቀው ለምትጥለው እዳሪና ለምትሸናው አሥካሪ መጠጥ ብለህ ትበጠረቃለህ። የዕውቀትህና የነቢይነትህ ልኬት ደግሞ ጌታቸው ረዳን ከአንድ ምሥኪን ኢትዮጵያዊ መለየት እንኳን እሥከማያሥችል የድንቁርና አዘቅት ይወርዳል። ጌታቸው ረዳ ማንን ፈርቶ ነው ጎጃም ድረሥ ሄዶ የሀዲሥ አለማየሁን የምናብ ፍጡር ጉዱ ካሣን በብዕር ሥምነት የሚጠቀም? በል ንገረኝ እንጁ የኔ ደነዝ? ጌታቸውን ሣታውቀው ነው ለካ የምትቀባዥረው። ሚዲያ አትከታተልም እንዴ ጌታህን እንዴት አድርጎ እሥከዶቃ ማሰሪያው እንደሚያሥታጥቀው?
    ጉረኛ መሆንም ይቃጣሃል። አንተ ስለኔ “ጌታቸው ረዳ” የምታውቀው መረጃ ኖሮ፣ ያንንም “መረጃ” ለማውጣት ከዚህ የኦነግ ዘመን የተሻለ ጊዜ አስፈልጎህ “ስለአንተ ያለኝን መረጃ ጊዜ ሲፈቅድ አጋልጠዋለሁ” ማለትህ የሚጠቁመው ድርጅትህ ኦነግ/ኦህዲድ ወይም ንጉሥህ አቢይ የካድሬና የዲጂታል ፕሮፓጋንዲስት ድርቅ የመታው መሆኑን ነው። ለነገሪ እኔን ጌታቸው ማለትህ ራሱ ለደደብነታችሁ በቂ ምሥክር ነው። ትግራይ ቲቪና ድምፂ ወያኔ ላይ በግልጽ ያሻውን የሚደነፋ ሰው ታየኝ ዳግማዊ ጉዱ ካሣ ብሎ በነዘሃበሻ ሲመጣ! ወላድ አትይህ ቀጀላዬ! አንተ ስትጸነስ በቤታችሁ ጣርያ ትክክል ሰማይ ላይ የነበረው ዞዲያካዊ ኮከብ ራሱ አሣዘነኝ። አንተን ጥሎበት።
    ውይ ውይ ለካንሥ ህማማት ነው። በድራቡም ፃም ጸሎትና ምህላ ታዟል- እንዳንተ ዓይነቱን ቢሉት ቢሉት የማይገባው ንክር ኮሮና ቫይረሥ አምላክ እንዲገላግለን ታሥቦ። በዚህን ወቅት አንተን እንዳሥከፋ ምክንያት ሆነሃልና ወደሚቀርብህ ‘ቢሾፍቱ’ ሂድና በል 250 እሬቻ … ቧይ ለየት መጣብኝ እሬቻና ቦረንትቻ ዶሞ … ሥግደት ስገድ። ጅል አይሙት እንዲያጫውት…(በቃኝ፣ አንተም ይብቃህና ወደሚቀርብህ ጠበል ሂድ ባባየ፣ ኦህዲድ ያጋባብህን እውነትን የመካድ ደዌ ከዚህም ሣይከፋብህ ታከምና ሰው ሰው ሽተት…)

    • ጉዱ ጌታቸው ስለጽንፈኝነት ምንአልባት ከሁለት አመት በፊት የጻፍከው ትዝ ይልሃል። ራስህን ብዚያ ጽሁፍ ተንትነው። ዛሬ ደግሞ አማራ ሆነህ ኦሮሞን ጠላህ። በዚያ ጽሁፍህ ደግሞ የትግሬ ጠላት ነበርክ ። ለዚህ ነው የአንድነት ጠላት ነህ የምልክ። እሬቻ የኦሮሞ በሃል ነው። አንተ ፈለከው አልፈለክው ይከበራል። አንተም የኦሮሞ ህዝብ ዛሬ ከሌሎች ጋር በመሆን የደረሰበት ደረጃ ያሳብድሃል እንጂ ወደ ስልጣን መመለስ የለም።

  12. አባ ዊርቱ አብይ ተነካ ብለዉ በሚያስቡበት ጊዜ አስተዋይነቶን የሚፈታተን ነገር ይታያል በብዙ ጽሁፎቾም ይህን አንጸባርቀዋል በአምላክ እንጂ በሰዉ ያን ያህል ሀይማኖታዊ እምነት ባይኖረን መልካም ነዉ። ከዉስጦ ያለዉ ነገር አመለካከቶን ስላንሸዋረረዉ የወለጋን ከፋኖ ጋር አገኛኝተዉታል።
    የወለጋዉ ኦነግ ከምንም በላይ ቁም ስቅል ያሳየዉ የወለጋን ህዝብና የአብይን ሹመኞች ነዉ የዘርን አወቃቀር አስመልክተን ስንጮህ አያገባችሁም እንባላለን እርሶ ደግሞ ወለጋ ኦነግ ላይ እርምጃ ሲወሰድ የት ነበራችሁ የሚል ምልከታ ይሰነዝሩብናል። ፍርዱን ለርሶ ልተወዉ ሶማሊያ ክልል አብዲ ኢሌ ላይ የተወሰደዉ እርምጃ አማራ ክልልን ለማፈራረስ የተወሰደዉን አፋጣኝ እርምጃ ከኦነግ ሸኔ ጋር ያስተያዩት። የእኛ ናቸዉ ጉዳያችን በር ዘግተን እነመክራለን አባ ገዳ ሰምበቶ ይጨርሱታል የኦሮሞ ደም በከንቱ መፍሰስ የለበትም እየተባለ እሹሩሩ ሲባል ነዉ የከረመዉ። 13 ባንክ ሲዘርፍ ምንም እርምጃ አልተወሰደም ያ ገንዘብ እኮ የመንግስት አይደለም የህዝብ ነዉ። ኦነግ እድሜ ለአብይ ምን ደረሰበት እነ አሳምነዉ እኮ በፈጠራ ተንኮልና ፍሬምድ ተደርገዉ እኮ ነዉ ባስቸኳይ የተደመሰሱት ምንም ጥፋት እኮ የለባቸዉም እንዴት ሁኖ ነዉ ባህርዳር ሁነዉ መፈንቅለ መንስት የሚያደርጉት በዚህ ላይ ስለ ወታደረዊ ነገር የሚያዉቁም ይመስለናል አረ ይተዉን ብዙ ነገር አለ ነገሩን ቀልድ አናድርገዉ።
    አብይ እነ አሳምነዉን ሲያስገድል እኮ መጀመሪያ ኤርትራ ከዛም አክሱም ደብረ ጽዮን ጋር መክሮ እኮ ነዉ አሳምነዉ እና ዶር አምባቸዉን ምናለ ለደብረጽዮን ያደረገዉን ደግነት ቢቸራቸዉ? የኢትዮጵያ የመከላለከያ መሳሪያዎች በትግሬዎች ታግተዉ እጂ ሰጥተን ቁጭ ብለናል የሀገር አጥንት የጋጡ ወንጀለኞች ነብሰ ገዳዮች እድሜ ለአብይ መቀሌ ከትመዉ ቁጭ ብለዋል ሀብታቸዉ እና ንብረታቸዉ ህጋዊ ሁኖ ተከብሯል። ሌንጮ ባቲ፤አርከበ እቁባይ ሌሎችም ወንጀለኞች የአብይ ዋና አማካሪ ሁነዉ ቁጭ ብለዋል ከወንጀለኛ ዉጭ ደህና ሹመኛ ማግኘት ሳይችል ቀርቶ ነዉ ወይስ ከጀርባዉ ምን ነገር ተገኘ? እነዴት ነዉ በዘመነ አብይ ሰዉ በወንጀሉ ላይጠየቅ ነዉ ወይስ ይሄ ምርመራ ከገፋ ወደእኔ ይመጣል ብሎ ሰግቶ ነዉ? አብይን ፍጹም አድርጎ ለማቅረብ መሞከር የሚመች ነገር አይደለም።
    ዲማ ነጋዎ/ሌንጮ ለታ/አረጋዊ በርሄ/ግደይ ዘርአጽዮን/በያን ሱጳ/ዳዉድ ኢብሳ አረ ሰንቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን ይሰራሉ ቤት ተሰጥቷቸዉ ቀለብ ተቆርጦላቸዉ በአጃቢ እድሜ ለአብይ ብለዉ ይኖራሉ። ትግሬዎች የሰሩትን ህንጻ የዘረፉትን ሀብት አዲስ አበባ ሂደዉ አይተዋል? እድሜ ለዶ/ር አብይ ገንዘቡን አጥበዉት በሰላም እየኖሩ ነዉ። ስለዚህ ዶ/ር አብይ በእርግጥ በአነጋገር ደረጃ ከመለስ ዘራዊም ሆነ ከመንግስቱ ሐ/ማርያም ይሻል ይሆናል እነዲህ አይነቱን ስልት እንዲይዝ ያስቻለዉ ጥሩነቱ ሳይሆን ትምህርቱና አንዳንድ በጣት የሚቆጠሩና የሚወገዙ አማካሪዎቹ ሊሆኑ ይችላሉ (ዳንኤል ክብረት፤ዶ/ር ወዳጄነህ) በተረፈ ዶር አብይ በነጻ አእምሮ የሰራዉ ስራ ሲታይና ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ ለማቅረብ ባለመቻሉ ከወንጀለኞች የሚያንስ አይሆንም። ከሾማቸዉ ሹመኞች ከፕሬዚዳንቷ በስተቀር አይን የሚገባ የለም።
    ጉዱ ካሳ
    አቅሙ ያለህ ሰዉና አስተማሪ ነህ ከነቀጀላ ጋር ግጥሚያ ከወረድክ ለጥጠዉ ይይዙሀል እነዲህ ሲበሳጩ አገልግሎትህ ፍሬ አፍርቷል ማለት ነዉ መልስህ ሊሆን የሚችለዉ አጠር አድርገህ ከከከከከ ማለት ብቻ ነዉ። የሚገርምህ እንዲህ አይነቱ እሰጥ አገባ አንዱ ስልታቸዉ ነዉ ከስብእናህ አዉርደዉ ብሺሺቅ ዉስጥ ይከቱሀል ያበሳጩኸል ነዉ እንዴ ብለህ ስቀህ እለፋቸዉ አስብበት ጽሁፍህ በአጽንኦት ከሚነበቡ ሰዎች መሀል አንዱ ስለሆንክ ደረጃህን ጠብቅ። እነ ቀጀላ በሃሳብ የተጎዱ፤ ከነሱ አእምሮ በላይ የሆነ ሰዉ በርቀት መቆጣጠሪያ የሚጋልባቸዉ፤ የሌላቸዉን ትልቅነት የሰጣቸዉ፤ የሌላዉን ንብረት ያከፋፈላቸዉ አካላት የሚቆጣጠራቸዉ የዋሆች ናቸዉ። እዘንላቸዉ ነገሩ ሳይበር ሆነ እንጂ እኛንም እኮ ዘቅዝቀዉ ይሰቅሉን ነበር

  13. አይሄሄ አቶ ሰመረ። አልተረዱኝም ማለት ነው። እኔ እንኳ የነሸኔን ታሪክ ያመጣሁት የአቢይ ጦር ሸኔን እንደወቃ ሁሉ ፋኖ ተብዬን ሸኔ አይነት ሽፍታ ሲነካ ምነው ጩህት በዛ? ምነው ያኔ ለነሸኔ ጊዜ በአቢይ ምሬቱ አልታየም ከአማሮቹ ለማለት ያመጣሁት ስላቅ ነው። በበኩሌ መንግስት የገዛ ህዝባቸውን በሚያዋክቡና በሚዘርፉ ሽፍቶች – ሸኔ ይሁን “ፋኖ” ተብዬ – የሚወስደውን እርምጃ እቀበላለሁ ከሰብአዊነት አንጻር። እንግዲህ ለትግል የቆሙትን ሀቀኛ ፋኖና ቄሮዎችን አይደለም እያልኩ ያለሁት፣ ሽፍቶቹን እንጅ ። ከህዝቡ እራሱ በምወደው ቪኦኤ ሰምቻለሁ። በገፍ አሉ ሽፍቶች በአማራም ፣ በዖሮሞም ምድር። እነዚህ ስግብግቦች ሀይ መባል አለባቸው። እንግዲህ እኔ እንኳን በዚህ እድሜዬ ቀርቶ በልጅነቴም ከፈጣሪ በቀር አምልኮተ ስጋለባሽ ሆነ ነዋይ ችግር የለብኝም። ይወቁት ይህን። አቢይን በግል ግን በሚሰሩት ስራ ትልቅ ክብር አለኝ። ሰውዬው ስራቸው ይመሰክራል። በአይን ይታያል፣ በእጅምይዳሰሳል። መረጃ በሌለኝ ነገርና እርስዎ በከሰሱዋቸው ጉዳይ በሀሜት ደረጃ እኔም ሰምቼዋለሁ። ከጥንትም ከጃንሆይ ጀምሮ ሀሜት የተለመደ ነው። የጃንሆይን ብዙ መልካምነት(ስህተቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆኖ) ህይወታቸው በዛ ከሀዲ መንግስቱ ካለፈ በሁዋላ ነበር ብዙው መልካምነታቸው የወጣው። የአቢይም አሁን ላይታየን ይችላል እንደኔ ሀሳብ። በአጠቃላይ ገለልተኛ ሆኜ ሳየው፣ የአማራው ወገናችን ምሬት ባብላጫው እነ ህውሀቶች በዘሩት ዘርና በተለይ ሁኔታ የአማራውን ግዛት አንቀው እዛው በመሰንበታቸው ነው። የነፋኖ ሽፍቶችም ልብ ልብ ደርሰው የገዛ ህዝባቸውን እንዲህ ማሰቃየት የነሱው የስራ ፍሬ ነው። እውነት ለአማራው ይሁን ለዖሮሞው ወገን የሚጨነቅ ዜጋ መንግስት በነሸኔና “ፋኖ” የሚወስደውን እርምጃ መቀበል አለበት ባይ ነኝ እንኳንስ ላበላልጥ። ያንብቡኝ ወደሁዋላ ሄደው አቋሜን በሽፍቶቹ ላይ። አንዲት መወላወል አያገኙብኝም። አማራ ለሆነ ወገን በሙሉ የማስተላልፈው ቢኖር (በቅርቡ በጻፉት የማከብራቸው ዶር አክሎግ ቢራራ እንኳ ይቺን እንዴት እንዳልተረዱ ገርሞኛል) እንዲህ ነው፣ ማነው ባሁኑ ጊዜ የአማራው ክልል የጦር አውድማ እንዲሆን የሚመኝ? ከዚህስ ጽልመታዊ ስራ ማን ያተርፋል? ማንስ ይጠቀማል? እውን አቢይ አህመድ ነው ወይስ ህውሀትና የነሱ ሆድአደር ቅጥረኞች ናቸው? እስቲ አስቡት አቶ ሰመረ፣ አማራው ላይ በመዝመት አቢይ ምን አይነት ምድራዊ ይሁን ሰማያዊ ጥቅም ያገኙበታል? ፍርዱን ለህሊናዎ ለእኔ ግን ምንም ነው። ይህው ነው። መልካም የምህላ ሳምንት። በነገራችን ላይ ከሁሉ ሹማምንት አንድ በትክክል ስራውን የሚሰራ ሰው ያየሁት ከበጣም ጥቂቶች ዶር አቢይ ናቸው። እንግዲህ ከማየውና ከምረዳው።

  14. አይ አባ ዊርቱ ፣ ከዚህ በላይ አምልኮ ከየት ይምጣ።አንድን መሪ መውደድ ግላዊ መብት ቢሆንም የአንድ ሐገርን ህዝብ ህልውና የሚያጠፋና ብሎም አቅም እና እውቀት የለሽ መሪ ፤ ወደፊት ታሪክ ይመሰክራል፤ እደአሁኑ አብይን መሳይ ኢትዮጵያን አጋጥሟት አያውቅም ።መሪ የሚገመተው በአመራሩ ነው ።እሱን ከከበቡት፣ ከመሾማቸው ባለሰሥልጣናትና የነርሱ ተዋራጅ ሃላፊዎች በሚያደርጉት ነው መንግሥት የሚገመገመው።አሁን በኢትዮጵያ ምድር የሚካሄደውን ከአብይ ነጥሎ መመልከቱ የፓለቲካ ሂደትን አለመረዳት ሳይሆን እውነትም ጭፍን አምልኮ ነው።በሌላው በታደሉት ሐገራት እንዲህ ያለ አፈጮሌ መሪ እንደዚህ ነገር ሳይበላሽ ከስልጣን ያወርዱታል። ትንሽም ቀሪ ይሉኝታ ካለው በፈቃዱ ይለቃል።ሐገርን ለመምራት በአፍ ገብስ መቁላት በቂ አይደለም።ሰውዬው ውዳሴ ከንቱ ይወዳል፣ይሁን አራግቡለት ጊዜው ሲመጣ ግን እንዲህ አልመሰለኝም ብሎ ማምለጫ ምክንያት ከፍትህ በትር አያድንም ።ጀርመን ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናት።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share