“ሰው ካልሞተ ወይ ካልሄደ አይመሰገንም” መባሉ እውነት ነው! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ (ma74085@gmail.com)

እንደመግቢያ፡- ኢትዮጵያን የገጠሟት ነጋዴዎች የለዬላቸው የቀን ጅቦች እንጂ በፍጹም ሰዎች አይደሉም፡፡ ኢትዮጵያን የገጠሟት ፖለቲከኞችም መሠሪ ሆዳሞችና ጎጠኞች አንዳንዶቹም የውጭ ጠላቶቻችን ቀጥተኛ ወኪሎች እንጂ ስለሀገርና ሕዝብ የሚጨነቁና የፖለቲካ ሀሁንም የሚያውቁ አይደሉም፡፡ ከነዚህ ፖለቲከኞች ብዙዎቹ በትምህርት ሲወድቁና ሥራ ሲያጡ የኑሮ አማራጭ በማጣታቸው ብቻ “ዛሬ ከምሞት ነገ ልሙት” በሚለው የአጋሰሶች ፈሊጥ በመነዳት በቀላሉ ወደሚገባበት የፖለቲካው ጎራ ዘው የሚሉ ናቸው፡፡…

 

የራስህ ሕዝብ በሞትና በሕይወት መሀል ሆኖ እየተጨነቀ ባለበት ሰዓት አንድ ኩንታል ጤፍ 5000 ብር ሲገባ፣ ሦስት በሦስት የሆነች አንዲት ጭርንቁስ ክፍል በወር ከ2000 ብር የበለጠ ስትከራይ፣ ኑሮ እንደመንኮራኩር በየቀኑ ሲወነጨፍ … ባለሁለት ሽህና ከዚያም በታች የሚያገኙ የወር ደሞዝተኞች እንዴት ይኖራሉ ብሎ ቅንጣት የማያስብ መሪና መንግሥት ያለን ብቸኛ ሕዝብ እኛ ነን፡፡ በኮሮና ቫይረስ ተጨንቀን ተጠበን የምንገባበትን አጥተን ሳለ ገብጋባ ነጋዴዎች አንዲት ሎሚ ብር 10 እና 15 እንዲሁም አንድ ኪሎ ነጭ ሽንኩርት 200 እና 250 ብር ሲሸጡ ዝም የሚል መንግሥት ማንን እየመራ እንደሆነ መረዳት አይቻልም (እርግጥ ነው በአንዳንድ አካባቢዎች ይህን ችግር ለመቅረፍ ውሱን እንቅስቃሴዎች እንደሚደረጉ ይሰማልና ለነዚያ ዓይነቶቹ የሥራ ኃላፊዎችና የሥምሪት አባላት ምሥጋናየን ማቅረብ እወዳለሁ)፡፡ ሁሉም እንደፈለገው ሆኖ ኳስ አበደችን የመሰለ የጨረባ ተዝካር በኢትዮጵያ ገንኖ ይታያል፡፡ በኪነ ጥበቡ አለን እንጂ መንግሥት ስለመኖሩ እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ በዚህ ላይ ነው ኮሮና ቫይረስ የመጣብን፡፡ በደምባራ ፈረስ ቃጭል ተጨምሮ፡፡ ቡሃ ላይ ቆረቆር፡፡ ዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ፤ ሌላም ካለህ ጨምርበት፡፡ እኛም እንደዚህ ሆነናል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከሰኔ 23፣ 2012 ጀምሮ በኢትዮጵያ ስለተፈጸመው ወንጀል የተሰጠ መግለጫ – ድልድይ በአወሮፓ ያኢትዮጲያዊያን መድረክ

መንግሥቱ ኃ/ማርያም ጨካኝ ይሁን እንጂ ኢትዮጵያዊ ጨካኝ ነበር፡፡ መንግሥቱ ዐረመኔ ይሁን እንጂ ዐረመኔነቱ በዘርና በጎሣ፣ በሃይማኖትና በጎጥ መደቦች ያልተከፋፈለ ለሁሉም እኩል ነበር፡፡ አሁን ያለን ዘረኛ መንግሥት ግን ዕድሜ ለሕወሓትና ለታሪካዊ ጠላቶቻችን ለአንዱ የእንጀራ ልጅ ለሌላው የሥጋ ልጅ እየሆነ ሀገርና ሕዝብ በመፍረስ አደጋ ውስጥ ናቸው፡፡ ግን አንፈርስም!

መንጌ በገብጋባ የበርበሬ ነጋዴዎች ላይ የወሰደውን የማያዳግም እርምጃ እናስታውሳለን፡፡ አካሄዱ ህገወጥና ጭካኔ የተሞላበት ቢሆንም ውጤቱ ግን ለሕዝብ አልጠቀመም ማለት አንችልም – ፈረንጅ እንዲህ ይላል – Little temper settles the dust.  ሌላም ላክልልህ –  Even the nicest people have their limits. አንዳንዴ ክፉ መሆን ባትፈልገውም እንኳን መልካም ነው፡፡ ስልሳ ሰው የጫነ አውቶቡስ አንድ ሰው ለማዳን ብሎ ስልሳ ሰው ገደል ሊከት አይገባውም፡፡ በተመሳሳይም ጥቂት ጅብ ነጋዴዎች ይከፋቸዋል ተብሎ ሰፊው ሕዝብ በቁሙ እንጦርጦስ ሊገባ አይገባምና አንዳንዴ እያመመንም ቢሆን ጨከን ያሉ እርምጃዎችን መውሰድ ሀገርንና ሕዝብን ከተጨማሪ ጉዳት ከማዳናቸውም በላይ አስተማሪነታቸው የጎላ ነው፡፡ ችግሩ ግን ሕግ አስከባሪ ተብዬውም በራሱ ወይ በቤተሰቡ ስም በንግዱ ዘርፍ  ከገባና የሌቦች ተባባሪ ሆኖ ከተገኘ ነው፡፡ ያ ዓይነቱ ጉዞ ተያይዞ ጥፋት ነው፡፡ ሕግ አስከባሪ ከሌቦች ጋር በጥቅም ከተሻረከና ሙስና ሀገርን ካጥለቀለቀ የሀገርና የሕዝብ ኅልውና ልክ እንደኛ እንዳሁኑ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ ይገባል፡፡ አሁን እኮ ሰው ገድለህ ብታመልጥ አንደኛ የሚከተልህ የለም፤ ሁለተኛ የሚከተልህ ቢኖር እንኳ የሙስና ድርሻውን ካንተ ወስዶ ፋይልህን መቼም እንዳይገኝ አድርጎ የሚቀብርልህ ኅሊናቢስ ሙሰኛ ነው፡፡ ሦስተኛ ወደየትም አቤት ብትል የሚሰማህ የለም (ሲጀመር አቤት መባያ ራሱ የለም)፡፡  ያለንበት ሁኔታ እኮ እኮ ያስጨንቃል ጎበዝ!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዕርቅ እና ድርድር አገር እና ህዝብ ወይስ ስልጣን ስልጣን መታደግ ?    

ጃዋር መሀመድን የመሰለ ዐረባዊ ኮሮኖና ቫይረስ እንደፈለገው ሲፈነጭ ማየት፣ በቀለ ገርባን የመሰለ ኢቦላ ቫይረስ እንዳሻው ትዳር ሲያፈርስ መታዘብ፣ ሕዝቅያስና ፀጋየ አራንሳን የመሰሉ ኢትዮ-ግብፃውያን ኤችአይቪዎች እንዳሻቸው ሕዝብን ሲያጋጩ ማየት ለእውነተኛ ኢትዮጵያውያን ትልቅ የኅሊና ቁስል ነው፡፡ ወቅቱ ነው ብለን ፍርዱን ለጊዜና ለፈጣሪ ብንተውም የቁስሉ ጥዝጠዛ ግን ዕረፍት ነሣን፡፡ ስለሆነም ክፉም ቢሆን ያለፈን መናፈቅ ልናመልጠው ያልቻልነው የወቅቱ ፍርጃ ሆነብን፡፡

ኢትዮጵያችን በሰብአዊና ተፈጥሯዊ የኮሮና ቫይረሶች ተቀፍድዳ እዬዬ እያለች ነው፡፡ ፈጣሪ በአፋጣኝ ይድረስላት፡፡ እንዳንዳች ነገር የሚከረፋውና የሚጠነባው ዘረኝነት ላይ ይህ ቫይረስ ተጨምሮ ሀገራችን ዓለም ባፈራቻቸው ቋንቋዎች ልትገለጽ የማትችል ቅርጸ ቢስ ሆናለች፡፡

ለማንኛውም መንጌ ሆይ ወዴት ነህ! በሃሳብ ደረጃም ቢሆን የበደልኩህን ይቅር በለኝ፡፡ ካንተ የባሱ የእፉኝት ልጆች መጥተው አሣራችንን እያበሉን መሆናቸውን ሳትከታተል አትቀርም፡፡ አንተ አሁን አርጅተሃል፡፡ ሥልጣን ቢሰጥህ እንኳ እንደዚያ እንደዱሮው በመስቀል አደባባይ እየተገማሸርክ በቀይ ቀለም የተሞላ ጠርሙስም ከግድግዳ ጋር እያጋጨህ እንደማትገዛን ግልጽ  ነው፡፡ ጊዜ ባለውሉ እንዲህ ነው፡፡

ይህን የጊዜ ባለውልነት ያልተረዱ ጎረምሦች ቤተ መንግሥትን በዘር ወር-ተረኝነት ተቆጣጥረው ፍዳችንን እያሳዩን ነውና ፈጣሪ ሆይ ቶሎ ድረስልን፡፡ አጋንንታዊነት በቤተ መንግሥት ብቻ ሳይወሰን ቤተ አምልኮቶችንም በግላጭ ተቆጣጥሮ ከሃይማኖትም፣ ከሞራል ዕሤቶችም፣ ከባህልም፣ ከዕውቀት አምባም አውጥቶናል፡፡ ሰው መሳይ በሸንጎ ከሆን ቆየት አልን፡፡ … በሁሉም የሰውነት መለኪያ ሚዛኖች ስንለካ ወርደንና ቀለን የለየለት እንስሳ ሆነናልና አምላክ ሆይ እንደገና ሥራን፡፡ እንደጠፋን እንዳንቀር ጀርባህን እንዳዞርክብን አትቅር፡፡

በነገራችን ላይ ከእንስሳትም እንዳነስን መጠቆሜ ስህተት መሆኑ ይሰማኛል፡፡ ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት እንስሳት ከኛ ይበልጣሉና፡፡ አንድ እንስሳ ከጠገበና ካልደረሱበት ማንንም አይተናኮልም – አይነካምም፤ እንስሳ ከተፈጥሯዊ ተግባሩ አያፈነግጥም፡፡ የወንድ እርግብ ሚስት ሴት እርግብ ናት – ሊያውም አንድ ለአንድ በሚለው ሕግ ተመርተው፡፡ አንዲት ጉሬዛ የምታገባው መሰሏን ወንድ ጉሬዛ ነው፡፡ አውሮፓውያን ከእንስሳት ጋር እንዲጋቡ ህጋቸውን ማሻሻላቸውን እየሰማን አይደል ሰሞኑን? እኛ ሰዎች ስንባል እንግዲህ የተሰጠንን አንጎል በከንቱ በማዋል ከሰውነት ተራ የሚያወጡ ተግባራትን እየፈጸምን ከራሳችን ኅሊናም፣ ከተፈጥሮና ከእግዜሩም ተለያይተናል፡፡ መጥኔ ለሰው ልጅ! ግን ግን ለዚህም ሁሉ ይከፈለዋል – ክፍያውም ጀምሯል፡፡ በቅርቡ ደግሞ ዓለማችን ትታደስና ሦሥት ዐይናማዎች በጉጉት የሚጠብቁት ወርቃማው ዘመን ይብታል፡፡ መንገድ ጠረጋው ነው ያለንበት፡፡ …

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመስቀል በዓል በጉራጌዎች ዘንድ - ከቅዱስ ሃብት በላቸው (ከአውስትራሊያ) [ጋዜጠኛ]

 

17 Comments

  1. ያለፈውን መናፈቅ ያለውን መፍራት መጪውን መጠራጠር የፖለቲካ ባህላችን ሆኖ መቅረቱ በእጅጉ ያሣዝናል። አሁን ብሎ ብሎ ጭራቁን መንግሥቱንና አገርና ህዝብን በቋንቋና በዘር የከፋፈለውን ዐረመኔውን መለሥ ዜናዊ የምንናፍቅበት ጊዜ ላይ መድረሣችንን ይህ ጽሑፍ ይጠቁማል። የወደዱትን ሢያጡ የጠሉትን ይቀላውጡ እንደሚባለው መሆኑ ነው። ይሄ ግም ዘመን ገና ብዙ ያሣየናል።

  2. Mengistu Hailemariam robbed the Ethiopian prosperous individuals their wealth ownerships , now we have a leader PM that encouraged prosperous individuals to accumulate more personal wealth the problem now is there is no guarantee the wealthy will be stripped of their wealth anytime , it happened non stop for the last half a century to so many wealthy individuals which is so unjust immoral and destructive.

  3. Correction:

    Mengistu Hailemariam robbed the Ethiopian prosperous individuals their wealth ownerships , now we have a leader PM that encouraged prosperous individuals to accumulate more personal wealth the problem now is there is no guarantee the wealthy will NOT be stripped of their wealth anytime , it happened non stop for the last half a century to so many wealthy individuals which is so unjust immoral and destructive.

  4. መግደልን የሚደግፍን ጽሁፍ ስለሆነ እዚህ ድረ ገጽ ላይ መለጠፉ የሚገርም ነው። ይህ ነው የዚህ ዘመን የ”ዴሞክራሲ” ታጋዮች ሚና።

  5. Obviously Colonel Mengistu Hailemariam was a ruthless dictator but was not involved in the rampant corruption and robbery of the country. The late TPLF ethnic chief Meles Zenawi was also a killer and persecutor. He was quoted as saying `we do not kill and announce in the media as the derg did`. He systematically committed egregious crimes against Ethiopians specially the Amharas who were displaced and killed en masse. Moreover, The TPLF leaders established a nexus of ethnic robbers who stole and embezzled the meager resources of the country.

  6. ታዴ ልክ ነህ:: እኔ ያልኩት ግን ጥfategna wonjelu behig tayto keteferedebet behig agbab yigedel enji kehig wuch ayhun new. Enji besme demokrasi wonjelegna bemot.ayketa maletma siratealbegninetinmasfafa new. Gebah?

  7. የሙሶሎኒን ታላቅነት የሚፅፉ፤ የሂትለርን አገር (ጀርመን) ወዳድነት የሚተርኩ በአለማችን ላይ አሁንም አሉ። የፋሺሽት እና የናዚ ፓርቲ ይቅርታ ጠያቂዎች (apologists) አፋቸውን ደጋግመው የሚከፍቱት በደል የደረሰበት ይቅር ብሎ በመቀመጡ ሳይሆን አይቀርም። የእስራኤል ሕዝብ እና መንግስት ግን የናዚን ካድሬዎች ከተደበቁበት እየፈለፈሉ ለፍርድ አቅርበዋቸዋል።

    መንግስቱ ኃ/ማርያም የተባለው ደንቆሮ ጨፍጫፊ የኢትዮጵያን ህፃናት፤ ወጣት እና ሴቶች በግፍ ጨፍጭፎ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ንብረት እና ገንዘብ ዘርፎ ወደ ዝምባቡዌ መፈርጠጡ አንሶ፤ በርዝራዥ ቡችላዎቹ አማካይነት አሁንም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይሳለቃል። ይህ ወራዳ ወታደር ተብዬ የሚያዘውን ጦር ለሞት አጋፍጦ ነፍሴ አውጭኝ ብሎ መፈርጠጡ በሚሊታሪ ፍርድ ቤት (court martial) ቀርቦ የሞት ፍርድ ሲገባው አሁንም በስተ እርጅና ደም እንደጠማው ነው። ይህ ማፈሪያ በታሪክ በኢትዮጵያ ከነበሩ መሪዎች ሁሉ አንገት የሚያስደፋ ነው።

    የወጋ ቢረሳ፤ የተወጋ አይረሳም።

    • ጠሐይ ደመቀ ልክ ነህ/ሽ። የመንጌን ዕኩይ ተግባራት አእምሮ ያለው ሰው አይክድም ወይም ሊክድ አይገባውም። ጥያቄው ግን አሁንም ያልተፈቱ እጅግ ብዙና ውሥብሥብ የኅልውና ችግሮች እያሉብን በዚያ ባለፈ ታሪክ ማላዘንና መቆዘም አለብን ወይ? ነው። እንጅ መንግሥቱ ለፍርድ መቅረብ አለመቅረብ ላይማ ላይ አንጣላም – መቅረብ አለበት ከተቻለ። “ጦር ፍርድ ቤት ቀርቦ ሞት ይፈረድበት” ማለት ግን በፍርድ ቤት ሥራ ጣልቃ መግባትና ፍርድን አስቀድሞ ለማዛባት መሞከር ስለሆነ ትልቅ ጥፋት መሆኑ ይታወቅ። ለፍርድ ይቅረብ ከተባለ ፍርድን በብላኔና በሥሜት መሥጠት ምን አመጣው?
      መንግሥቱ በኔ አማካይነት የደም ጥማቱን ለማርካት እንደሚሞክር መገለጡም ትልቅ ስህተት ነው – ለማለት ያልተፈለገ ገብቶኝ ከሆነ ግን ይቅርታ። ያኔ ልጅም ብሆን የመንግሥቱ ብርቱ ተቃዋሚ ነበርኩና ይህ አይታሰብም። ሌላው መንጌ የሀገር ሀብት ስለመዝረፉ ብዙም አልተወራ(በት)ምና ይሄ ነገር እምብዝም ሚዛን አያነሣም።…
      ውድ እህቴ/ወንድሜ! ረጋ እንበል። ከስሜት እንውጣ። ክፉም ሆነ ደግ ያለፈ አይመለሥም። ካለፈ ተምረን ግን ዛሬንና ነገን ማሣመር እንችላለን፤ ያቃተን ግን ይሄ ነው። ይህ ሥላቃተን ይመሥላል በምንችለው ያለፈን መቀጥቀጥ ላይ የምናተኩረው። አየህ/ሽ – “የምታሸንፈውን ምታ ቢሉት ወደ ሚሥቱ ሮጠ” ይሏል አሁን ነው። ባህላችን ያለፈን ማውገዝ፣ ያለውን መፍራት፣ መጪውን መጠራጠር… የሆነው ለዚህ ነው።

  8. ፀሀይ ደመቀ እግዚአብሄር ይካስህ:: ቃልበቃል የራሴ ህሊና የሚነግረኝን ነው የከተብከው:: መንግስቱ በግሌ ያደረሰብኝ በደል የለም:: ኢትዮጵያን ገድሎ ለወያኔ ያስረከበ 1. ፈሪ ቦቅቧቃ 2. አረመኔ ነው:: መንግስቱን የሚያደንቁ are low life individuals who probably participated in his atrocities.

  9. Tess ቲኒሽ አላጋነንክም? አንድ ሰው አንድን ሰው በተለያየ አቅጣጫ ማድነቅ ወይ አለማድነቅ መብቱ ነው። ሂትለርን የሚያደንቅ በሂትለር ጥፋቶች ተሣታፊ ነበር እንዳትል ያሰጋል። መንግሥቱ ግሩም ኢትዮጵያዊ ነበ። እንደወያኔ ሀገር አልሸጠም። መንግሥቱ ለሀገሩ አንድነት እንሥፍሥፍ ነበር። መንግሥቱ ጤፍን አራትና አምሥት ሽህ ብር እንዲገባ የቀን ጅብ ነጋዴዎችን ጃዝ እያለ ህዝብን በርሀብ አልጨረሰም። መንግሥቱን የኢትዮ ህዝብ ተንበርክኮ ፈጣሪውን ቢለምን አያገኘውም። የመንጌ ችግር ማይምነቱ ላይ የተመሠረተው ጭካኔውና ለሥልጣን ስሱ መሆኑ ነበር። በዚያም ሣቢያ ትውልድን ጨረሠ። ኢህአፓም ለጭካኔው ሚና ነበራት። በል እንግዲህ እኔንም low life … participant in his atrocities ምናምን የሚለውን ነጠላ ዜማህን ልቀቅና ጋብዘኝ። “ተለያይተናላ!” ያለው ማንኛው አርቲስት ነበር?

  10. Ethiopia closed all it’s borders , Mengistu is not coming back .The border closing law is only not enforced on the Ethiopian khat contraband exporter to Djibouti, the Oromia region PP representative SheMeles Abdissa who got invested huge sums of money in the depressed melting down Djiboutian economy , while the people in Oromia state are in need of money more than ever .

  11. AWEKECH-AWEKECH BILWAT YEKES LIJ METSHAFUN ATEBECH.

    colonel Mengistu was not the only soldier that loved his country; the great majority of Ethiopians did love Ethiopia.

    YALEMINIM DEM ENKENWA YIWDEM
    BEKENA MENFES ITYOPIA TIKDEM

    WAS the idea. The idea was getting rid of feudalism that was extremely unjust and separation of church and state so everybody can be regarded first class citizen under the law.

    Mengistu and his clique are trying to pass the guilt to prof Mesfin and the commission in charge of investigation for the killing of the SIXTY ministers and generals. Only brain dead people would excuse that crime done unprovoked and. Even if we believed Prof Mesfin told him to kill, did he have to? Is he a retard to take order from a geography professor with no power?

    Ethiopia thought she was much different than other African countries but Mengistu proved her wrong. He killed those sixty people and by African military savage book. Ethiopia has laws for God’s sake and there was no reason. EPRP panicked and went under ground. Tried to kill Mengistu nine times without success. EPRP guessed right that it was next b/c Menge killed MEISON too for no apparent reason later.

    By now Mengistu’s legacy should be clear.

    He was a very cruel soldier who even killed poor Paprika traders for supposedly hording without a day in court.

    you mention the price of onion and garlic too often in your writings.
    Do you have anything to do with the killings of the BERBERE traders?
    Ethiopia is a giant in Africa with her own stuff to this day and back then she was even greater. Everybody recognized Ethiopia had a long tradition of doing things her way. The Church in the north and the Imams in the law lands were scary people for colonialists. For three thousand years the mysterious Ethiopia stood only to be destroyed by Mengistu.

    The communist students like Tesfaye Debesay or Haile Fida might have done better or worst but we’ll never know because they were killed by Mengistu who copied every thing from a book written about Colonel Gamal Abdil Naser of Egypt. That colonel freed Egypt from colonization and built his country but colonel Mengistu destroyed his. The monarchy in Egypt was not Egyptian but the one in Ethiopia was authentic Ethiopian which included his own grand father, a DEJAZMACH.

    Some of us mentioned Mengistu to annoy TPLF mostly but we never forgot how cruel he was even when there was no threat to his power. For example he would kill prisoners from Ras Kassa’s old house. Some from MEISON who helped him destroy EPRP and old people from Asmara. For no apparent reason. Some say it was because some people begged him to free the old ones the night before.

    Mengistu killed the old emperor with his own two hands and a pillow and then sat over his dead body for years.

    Mengistu also killed 154 Ethiopian generals. Only six generals did Ethiopia lose in all her wars.
    If the war in Eritrea ended in peace there was no need for military govt. And there it was General Aman 100% Ethiopian and 100% Eritrean with great fame among the military and civilians alike. His only sin was he spoke in his native tongue at Saba Stadium and asked for the release of the female and children of the royal family. Mengistu gave two mattresses for nine princess and the only surviving daughter of the emperor.

    Mengistu also has a very dirty mouth not fit for officer of any country in the entire world. After killing the best generals that fought the fight he would accuse them of being homo sexual. And many like you would applaud and grin the evil smile.

    You might have escaped justice because WEYANE absolutely loved the DERG CADRES without whom it couldn’t even dream of getting to the old palace. The DERG CADRES made Ethiopians hate the govt so much Issayas Afeworki was their choice to govern Ethiopia in May 1991 according to some bewildered journalists.

    The Addis Ababans understood the pain the Eritreans were going through. Dawit’s Red Tears and specially Be’Alu’s OROMAY were banned but people paid lots of money to buy photo copies and read them. Red Terror was in Asmara before it started in Addis and still going on long after. Only idiots would expect a referendum in favor of unity. ‘yes I know I killed your parents and siblings but it was all for the revolution, nothing personal’

    said the IDIOT DERG CADRE.

  12. ለዚህ ሁሉ የጥፋት መንጋና ነጻነ አውጭ ተብዬ የዳረገን ይህ ከይሲ መንግስቱ ሃይለማርያም የራሱን ባልደረቦች ቁርስ አደረግን ብሎ ያሳረደ ለደርግ አባልነት ያጨውን አጥፋንፉ ኣበተን ገድሎ ሚስቱና ልጆቹን ከቤት በማስወጣት ያሳበደ ጳጳስ ቴዎፍሎስን ቄስ ጉዲና ቱምሳና የሙስሊም ሼኮችን ሳይፈራ የጨፈጨፈ እንኳን በህይወቱ አጽሙ ኢትዮጲያ መግባት የለበትም:: የቀድሞ ሰራዊት የሚል ያዋቀሩ ባለፈው ሲሰባሰቡ ሊያወድሱት ሲጀምሩ ከራሳቸው በመንግስቱ የተገረፉ ጥፍራቸው የተነቀለ ተቃውመው የመንግስቱ ፓርት የሌለበት ትረካ ጀምረዋል ግን ሁሉም ያው ናቸው ነፍሰገዳዮች:: በኢትዮጲያ ታሪክ በጭፍጨፋው ከግራሲያኒ ቀጥሎ መንግስቱ ሃይለማርያም ነው:: ሙጋቤን የመስለ ደንቆሮ ለፍርድ ሳይስተላልፍ ሞተ በዚምባብዌ ያሉ ወገኖች ዛሬ ጥረቱን ቀጥለው የቀረችው ዘመኑን ወህኒ መግባት ይኖርበታል::

  13. ጉዱ ካሳ አንተ በግልህ ስንት ነፍስ እንዳፍህፋ ንገረንና መንግስንቱ እናክብርልህ:: ጀርመን ተደብቀህ አትቀርም አንድ ቀን ለፍርድ ትቀርባለህ::

    • ሃሃሃሃ… ደሬ፣ በኮሮናና በኑሮ ውድነት ቆፈን በቤቴ ተቆፍኜ እያለሁ በነፍሥ ደረስክልኝና ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን በሣቅ አዝናናኸኝ። እንዳንተ ዓይነት ብልኆችና አሥተዋዮች ባይኖሩ ዓለማችን ምን ይውጣት እንደነበር ሣስበው ዘገነነኝ።
      ለማንኛውም እኔ የደርግ አባልም የኢሠፓ አባልም ወታደርም አልነበርኩም። ሰው መግደል ቢያምረኝ እንኳን አምሮ አምሮ ይተወኛል እንጂ ሰውን መግደል በሚያስችል ቁመና ላይ ተገኝቼ አላውቅም በሕይወቴ። ባጭሩ ልንገርህ ፥ ሙያየ መምህርነት ነው፤ ዘልዛላው ዕድሜየ 55 ነው፤ ግን በቅጡ ያልኖርኩበትን ከደርግ 7 ያህል፣ ከወያኔ 27፣ ከአቢይ አህመድ 2 ሥትቀንሥለት ዕድሜየ ከወጪ ቀሪ 19 ዓመት ገደማ ነው።
      ጀርመን አገርን በዜናና በጂኦግራፊ ትምህርት ነው የማውቃት። በዚህ ታሪኬ ለፍርድ ካቀረብከኝ መብትህ ነው ወንድሜ።
      አብይንና እነብሬን ግን ሣትወዳቸው አልቀረህም። እኔም ካንተው ባልተናነሰ እወዳቸዋለሁ። የምጠላው የህዝብንና የሀገርን ችግር ያለመረዳታቸውን መጥፎ ጎን ነው፤ ይህ ደግሞ አለመታደል ነው፤ በዚህም ያሣዝኑኛል። … ውለታህን በመጠኑም ቢሆን እንደከፈልኩ ይሰማኛል ፥ ትንሽ አዝናንቼህ ከሆነ!

  14. “በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት” የሚለው ብሂል የሚሰራው ይህንን የዘመናችንን የለየለት ጨካኝ አረመኔ መንግስቱ ሃይለማርያምን ለሚናፍቅ ብቻ ነው:: በመቶሺዎች ተቃዋሚዎችን በቀይ ሽብር በነጻ ርምጃ ያሳረደ ጳጳሱን ቴዎፍሎሱን የፕሮቴስታንቱን ቄስ ጉዲና ቱምሳን ለጎጃምና ለኦሮሞ ቆማችሁ ብሎ አሳንቆ የገደለ የራሱን የትግል አጋር ለደርግ አባልነት የመለመለውን ኮሎኔል አጥናፉ አባተን ገድሎ ሚስቱንና ልጆቹን ከመንግስት ቤት አባርሮ ልጆቹ የተበተኑና ዛሬ ድረስ ታማሚዎች በግርፋቱ የሚጥል በሽታና ትራውማ የገቡ ብዙ ሺዎችን ስሜት የሚጎዳ ቁስልን የሚያደማ አስተያየትን ቅን ሰው አይሰማውም:: የመንግስቱ የስልጣን የጥቅም ተካፋዮችና ባባዶ ወኔ የሚኮፈሱ ተከታዮቹ ቢሉን አይደንቅም::

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share