March 9, 2017
2 mins read

እኛ በኛ እንኩራ

እንደ ትላንትናው ፣ እንዳባቶቻችን

ከመሃል ከተማ ፣ እስከ ጠረፋችን

ካመፀኞች ጋራ ፣ ይጀመር ፍልሚያችን

ምንሽር ጓንዴውን ፣ ያጩኸው ህዝባችን ።

አገሬ ኢትዮጵያ ፣ ቴዎድሮስ ያደገባት

ጋራው ሸንተረሩ ፣  ታሪክ የሰራባት

ሜዳ መስሎት ዛሬ ፣ ባንዳው ፈነጨባት ።

ሞቅ ሞቅ አድርገው ፣ ወያኔ ይሸበር

ትንፋሽ አሳጥረው ፣ በማሰው ይቀበር ።

ለእናት ኢትዮጵያ ፣ ባንድነት ዝመቱ

ትርጉም አልባ ፣ እንዳይሆን አገሬ ማለቱ

ግዴታን መወጣት ፣ ይሁን እንደጥንቱ

ሬሳን ይመስል ፣ ይብቃ መጨመቱ ።

ሁሉም ጦሩን ያንሳ ፣ ጠላት ላይሆን ወዳጅ

ሉአላዊነቱን ፣ ያስከብር በግዳጅ ።

ጀግና የጀግና ልጅ ፣ የሃገር አለኝታ

ግንባሩን የሚሰጥ ፣ ሳይፈራ ላንዳፍታ

ና ግጠመኝ የሚል ፣ ሞልቶ በየቦታ

ውድ የሚሞትላት ፣ አገሬ መች አጥታ ።

ህጻን ሽማግሌ ፣ ወጣት ወንድ ሴቱ

ዝናን ያተረፈ ፣ ዛሬም እንደጥንቱ

ባገሩ የሚኮራ ፣ ቆፍጣናና ብርቱ

ችግር የማይፈታው ፣ የጥንት የጠኋቱ

ንቅንቅ የማይለው ፣ ቆርጧል አንዴ ሃሞቱ ።

ያሳለፍነው ይብቃ ፣ ጠንክረን እንስራ

ሸክማችንም ይቅለል ፣ እኛ በኛ እንኩራ

ንፋስ ሳይገባብን ፣ ባንድነት በጋራ

ፋኖው ተነስና ፣ ጓዶችህን ጥራ

ልክህን አሳየው ፣ ለባንዳው ኩታራ ።

 

 

ታዛቢው

 

Previous Story

የጭለማ ዘመን ከኢትዮጵያ ማህጸን ደጋግሞ የመፍለቁ ሚስጢር ምን ይሆን? – ሸንቁጥ አየለ

Next Story

በትምህርት ሥርዓቱና በመምህራ ላይ የተደቀነ አደጋ | ዜና ትንታኔ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop