አማራና ኦሮሞ አንድ ታላቅ ጦርነት ተዘጋጅቶላቸዋል! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

ይህችን ጦማር ባልጽፋት ደስ ባለኝ፡፡ ግን እውነትን ተናግሮ እመሸበት ማደርን የመሰለ የለም፡፡ በመሳጭ የቃላት ፕሮፓጋንዳ “ኦሮማራ” እያልክ ብታሽሞነሙነው እውነቱ እንደሆነ ፈጥጦ እየመጣ ነው – ሴተኛ አዳሪዋ ጨርሳዋለች – “አጭበርባሪ አይተኛኝም!” ብላ፡፡ የምታታልለውንም ሰው ተፈጥሮና የትግስት ልኬት መረዳት አግባብ ነው – ለስንት ጊዜና በምን ያህል ድግግሞሽ ልታታልለው እንደምትችል ጭምር፡፡ ግልጹን ልንገርህ በኦሮሞና አማራ መካከል እኔ ነኝ ያለ ትልቅ ጦርነት ሊከሰት ሰዓታትን ምናልባትም ደቂቃዎችን እየተጠባበቀ ነው፤ መቼስ አርጂን አይከብደውም፡፡ መርዶህን ስማና ተዘጋጅህ ጠብቅ፡፡ ደግሞም ውሸት እንዳይመስልህ፡፡ “የማነው ሟርተኛ”ም አትበለኝ፡፡ ዝኆንና ዝኆን ሲፋለም ሣሩና ዛፍ ቅጠሉ ሁሉ ስለሚደቀደቅ “ጦርነቱ በነሱ ላይ ብቻ ነው ጉዳት የሚያስከትለው” ብለህ ጮቤ የምትረግጥ “ሌላ” ካለህም ውርድ ከራስ፡፡ የጦርነቱ ማስጀመሪያ ፊሽካ መቀሌ ላይም ይሁን ካይሮ ላይ የዐዋጁ እምቢልታና ከበሮ ግን በአክራሪ ኦሮሞዎች ደጅ ፀሐይ እየሞቀ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ካልሞተች አትነሳም፡፡ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች የሆኑ ማንነቶችንና ምንነቶችን አጥርተን እናውቅ ዘንድ 27 እና 2 ተከታታይ ዓመታትን በተለያዩ የስሜት ጡዘቶች ውስጥ ሆነን አሳለፍን፡፡ አሁን ግን ጊዜው የ“በቃ!” ሊሆንና ሰማይ ኮረጆውን ከፍቶ የመከራ ዶፉን ሊያዘንብ ምድርም ልትቀበል ሁሉ ነገር አልቋል፡፡ ከይሲ ከይሲው ማገዶ ይሆናል፤ ተራፊው ጥቂት ነው፡፡ ያን ወቅት የማያይ ብፁዕ ነው፡፡

ከየት እንደምጀምርልህ አላውቅም፡፡ ብቻ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ ጃዋር መሀመድ ቆይ ቆይማ …. ዶክተር አቢይ የዚህ ጦርነት መሃንዲስ ስለመሆኑ በቂ መረጃ የለኝም፡፡ አንድ የምገምተው ጉዳይ ግን ከራስ ፀጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ በአክራሪ ኦሮሞዎች ተጠፍንጎ በመያዙ ጦርነቱን ማስቆም አይችልም፡፡ የሚለውና የሚያደርገው ስለሚለያይ ቃሉን መጠቀም ቢያስጠይፈኝም “ልፋቱ”ን ሁሉ በዜሮ የሚያባዙ ኦሮሞዎች የፌዴራል መዋቅሮችን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ተቆጣጥረው ኢትዮጵያን የሥንግ አንቀዋታል፡፡ እስትንፋሷ በአምላክ እጅ ሆኖ እንጂ እንደነሱ ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ አብቅቶላት ነበር – አሁን አላበቃላትም ካልን፡፡

ክርስቲያን ታደለ ከባህር ዳሩ “መፈንቅለ መንግሥት” ጋር የሚያያይዘውን ነገር አጢንልኝ፡፡ ጃዋር መሀመድ ምንጩ በሚገመት ገንዘብ እንዴት እንደሚኖር፣ ምን ለ(ነ)ማን እየሰጠ ምን እንደሚሠራ፣ በርሱ ጦስና በርሱ ትዕዛዝ በሀገርና በወገን ላይ ምን እየተከናወነ እንደሆነ፣ በአንዲት ሀገር ሁለተኛ መንግሥት መሆኑንና ለዚያ አፍራሽ ተግባሩም እንደወሮታ በመንግሥት እንደሚጠበቅ ደግሞ አስብ፡፡ ዕንቆቅልሹ ሁሉ ቁልጭ ብሎ ይታይህ – ጤነኛ ሰው ከሆንክ፡፡ የምስኪን አማሮችን ኑሮና ቢሯቸውን ሳይቀር በምናብህ ሳላቸውና ተመልከት – ከፈለግህም ወደ ግንፍሌ አካባቢ ብቅ በልና ያቺን የተላላጠች የጭቃ ቤት ቢሯቸውን እይ፡፡ … አያ ጅቦ ከላይ ሆኖ ውኃ እየጠጣ ታች ሆና የርሱን እርጋጭ የምትጠጣዋን አህይት “አታደፍርሽብኝ!” ይላታል፡፡ እርሷም “አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ!” አለችው ይባላል – በኦሮሞና አማራ መካከል ያለው ወቅታዊ ስዕልም ይህን የእንስሳት ታሪክ የሚያስንቅ ቁጭ በሉ ነው – ሃሳብን ከጣሉ አይቀር ደግሞ እንዲህ ነው፡፡ እነ ክርስቲያን ታደለ ለእስር የተዳረጉትና እየደረሰባቸው ለሚገኘው እንግልትና ውርደት የተጋለጡት አማራ በመሆናው ብቻ ነው፡፡ ዘርን መሠረት ያደረገ ምን ዓይነት ስድብና ከወያኔ ያልተናነሰ ስብዕናን የማጉደፍ ተግባር እየተፈጸመባቸው እንደሆነ ከየእስር ቤቶቹ ከሚወጡ ጽሑፎች እየተረዳን ነው፡፡ ስለሆነም ለውጡም ሆነ የአቢይ እንቅስቃሴ ሁሉ “ብጥለው ገለበጠኝ” ዓይነት የዘረኝነት መተካካት መሆኑን ለመረዳት እማኝ መቁጠር አያሻም፡፡ አቢይም ሆነ እነሱሴዎች በዚህ ማፈሪያ ተግባራቸው ማፈር አለባቸው፡፡ ችግሩ ግን በዘረኝነት ማዕቀፍ ውስጥ ሀፍረት ወይም ይሉኝታ ብሎ ነገር በመዝገበ ቃላታቸው ሳይቀር አይታወቅም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር  ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል - ከያሬድ አውግቸው

ስለዚህ የኅልውናው ጦርነት አይቀርም፡፡ ጠላት ደስ ይበለው፡፡ ወዳጅንም ይክፋው – ‹መቼስ ማልጎደኔ› ይላሉ አዲሶቹ ጌቶቼ፡፡ ይህ ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ያለ ጦርነት ባላሰብነው ሰዓትና ባላሰብነው ሁኔታ ይነሳል፡፡ የድርሻውን አጥፍቶም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይቆማል፡፡ ከዚያን በኋላ ነው የኢትዮጵያ ትንሣዔ የሚበሠረው፡፡ ውጭ ያሉት የሀገራችን ጠላቶች እነጃዋርንና መሰሎቹን በማንኛውም ረገድ እስከጥግ አስታጥቀው ልከዋቸዋል፡፡ እንደሚያሸንፉም እርግጠኞች ናቸው፡፡ ግን እውነት እንጂ ዶላርና ዘመናዊ የጦር መሣሪያ አሸንፈው አያውቁምና አሸናፊው የእውነትን ዘገር የጨበጠ ብቻ ነው፤ ይህ የኔ ቃል አይደለም፡፡ ቋሚና ዘላለማዊ እውነት ነው፡፡

ጅል ሰው አያሸንፍህ፤ ሞኝ ሰው አይርታህ፡፡ ፈሪ ሰው ጌታህ አይሁን፡፡  ገረድ የጌታዋን ባል በቀማች ጊዜ አገር ምድሩ አይበቃትም፡፡ ደግሞም የደስታዋ ምንጭ የመጥፊዋ ሰበብ እንደሚሆን አታውቅምና አቅሏን ስታ ትቦርቃለች፡፡ የምታደርገውን ስለማታውቅ የምታደርሰው ጥፋት አንዳንዴ እጅግ ከባድ ሊሆን ይችላልና ከዚህ ዓይነቱ መጥፎ አጋጣሚ ለመዳን በርትቶ መጸለይ ተገቢ ነው፡፡ አይሆንም ተብሎ የሚናቅ ነገር ሊኖር እንደማይገባ በተለይ እንደሀገር ያሳለፍናቸው አርባና ሃምሣ ዓመታት በቂ ምሥክር ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ ከኦሮምኛ በቀር ሌላ ቋንቋ መናገር በሕይወት እስከ መወራረድ እየደረሰ ነው፡፡ ቄሮ አልተቻለም፡፡ ቄሮ በየተራ ሀገሪቱን እየዘረፈና እየመዘበረ በአንድ አዳር ሚሊዮነር ከመሆን አልፎ የንጹሓንን ነፍስ እስከመቀማት ደርሷል፡፡ የኦሮሞ ጢነኞች ማዕከላዊ መንግሥቱን የያዘውን ኃይል በመተማመንና ከርሱም ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ በማግኘት በአሁኑ ወቅት የማያደርጉት የለም፡፡ በስሙ ከዐርባና ሃምሳ በላይ ካርታ ፕላን የያዘ ቄሮ መኖሩን ስትሰሙ ወያኔ ማረኝ ልትሉ ይዳዳችኋል፡፡ የምስኪን ሠራተኞችን ኮንዶምኒየም ቀምቶ መውሰድ መንግሥታቸው የሰጣቸው መብት ነው – ለዚያውም “ጨርሳችሁ ካላስረከባችሁን አንወስድም” እያሉ እንደሚንቀባረሩ ሰምቻለሁ፡፡ እነዚህን ሰዎች ጅሎች የምላቸው ለዚህ ነው፡፡ ወያኔ ብልጧ በሃያ ሰባት ዓመታት የሠራችውን ግፍና በደል እንዲሁም ዝርፊያ እነዚህ ገልቱዎች ሁለት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው እያቀላጠፉት ነው፡፡ ደግሞም ባፈሱ ሳይሆን በጎረሱ መሆኑን አያውቁም፡፡ካለዕውቀትና ካለጥበብ ሀብትን ቢያጋፍሩት ዋጋ የለውም፡፡ አንዳንዱ ቄሮ ዛሬ ከብሮ ያድርና ነገ ድሃ ይሆናል – የገንዘብ አያያዙን ስለማያውቅበት፡፡ ብዙ ነገሮች ምናልባትም ሁሉም ነገሮች ዕውቀትን ይጠይቃሉ፡፡ ለመግደልም እኮ ዕውቀትን ይጠይቃል – አሁን የቄሮዎችንና የወያኔዎችን “የአገዳደል ሥነ ሥርዓት” እስኪ ታዘቡልኝ፡፡ እነዚያ በሥውርና በዘዴ ነው – እነዚህ ደግሞ በግልጸጥና በሜንጫ፡፡ አስተዳደግ የበደለው ሰው እንኳን ማዳንን መግደልንም በቅጡ አያውቅበትም፡፡ ታዲያ ሰው መሆን አይቀድምም ትላላችሁ? ነገር አትዘርጥጡብኝ – እያልኩ ያለሁት በጥፋት መንገድ ገብተው ሀገርን እያተረማመሱ የሚገኙ የማንኛውንም ወገን አባላት ነው፡፡ ከዚህኛው ብዙ ከዚያኛው ጥቂት ቢሆኑ የአጋጣሚ እንጂ የኔ ጉዳይ አይደለም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጥንብ ባለበት ጂብ ይሰባሰባል

ወደ ቀበሌ ሂዱ፡፡ ወደ ከፍተኛዎች አቅኑ፡፡ ወደ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እግር ጥሏችሁም ሆነ ለሥራ ጎራ በሉ፡፡ ወደ አየር መንገድ ሂዱ፡፡ ወደ ጉምሩክ ግቡ፡፡ ወደ ባንክ ሂዱ፡፡ ሥራ የሚቀጠሩ ዜጎችን ማንነት ፈትሹ፡፡ ባለሥልጣኖችን ሁሉ ተመልከቱ፡፡ ዱሮ አብዚሎ ቅብዚሎ ትሰሙ ነበር፤ አሁን የዚያኑ ግልባጭ “አካም ነጉማ ፈዩማ”ን ትሰማላችሁ፡፡ የቋንቋው ጉዳይ ችግር አይደለም፡፡ ሁሉም የኔው ነው፡፡ ችግሩ ይህን ተራ የቋንቋ ነገር ተመርኩዘው የሚሠሩት ፍትህንና ርትዕን የሚያጠፋ ሥነ ልቦናዊ ስካር ገዝፎ መታየት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊነቴ በዚህ እጅግ አፍራለሁ፡፡ የዚህ ማኅበረሰብ አባል መሆን በዚህ ዘመን ካላሳፈረ መቼም አያሳፍርም፡፡ በየሴከንዱ ሽቅብ ስለሚወነጨፈው የኑሮ ውድነት አንድም አልተነፈስኩም፡፡ እርሱም አንዱ የጦርነቱ ሰበብ እንደሚሆን አትርሱ፡፡ ስለሙስናውና ስለአስተዳደራዊ በደሎች ምንም አልተናገርኩም፡፡ ያም ለጦርነቱ መነሳት ቀላል አስተዋፅዖ የለውም፡፡ የትኛውም ቢሮ ይሁን በእጅህ ካልሆነ በእግርህ ሄደህ የምታስፈጽመው ጉዳይ የለም ወይም ጥቂት ነው፡፡ አዲሶቹ ሰዎችማ ለትንንሽ ጉዳዮች ሳይቀር የሚጠይቁት የገንዘብ መጠን ሲታሰብ ቁጥር ማወቃቸውንም ትጠራጠራለህ፡፡ ለምሣሌ አሥር ሽህ ብር ለምታገኝበት አንድ ጉዳይ ከግንዛቤ ዕጥረት የተነሣ የ50 ሽህ ብር ጉቦ ሊጠይቁህ ይችላሉ፤ ትዕቢታቸው ደግሞ ለጉድ ነው አሉ፡፡ “እከሳችኋለሁ” ብትል ከላይ እስከ ታች ሁሉም በነሱ ቁጥጥር ያለ መሆኑ እንዲገባህ በሚያሳብቅ የሰውነት እንቅስቃሴ ታጅበው “ሰባራ ዶሮ ሳቲቀድሚህ የትም ሄዳህ ኪሰስ” ሊሉህ ይችላሉ፡፡  እንዴ! ጉቦና ጉቦኝነት እኮ ዱሮም ነበር፤ ግን የያኔው ቅጥ ነበረው – “ሞራላዊ ሙሰኝነት” ነበር ያኔ፡፡ዱሮ በስልክ ሲያወራ በአላስፈላጊ ሁኔታ እየጮኸ አካባቢን የሚያደነቁረው የወያኔ ጥጋበኛ ነበር – አሁን ደግሞ ቄሮ ሆኗል፤ ለመጮህም ተረኝነት ማስፈለጉን ተመልከትልኝማ፡፡ ምድረ አሽቃባጭ ባለሆቴልና የምሽት ክበብ ባለቤት ደግሞ ዱሮ “ኮበለይ”ን እየከፈተ እንዳላስደነከረ አሁን “ያ በሬዱ”ን እየከፈተ ያዘልላል፡፡ … ስንገርም! እንዴት ብንረገም ነው!

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያዉያን ስቃይና መከራ በሳዉዲ አረቢያ - በሳዲቅ አህመድ (ጋዜጠኛ)

መነሻና መድረሻየን ወደድከውም ጠላኸውም ይህንን ግን ያዝልኝ – ጦርነቱ አይቀርም፡፡ ሕጻናትና አእሩግ ያላችሁ ለተወሰነ ጊዜ እንዲያገለግላችሁ ከሚበላውም ከሚጠጣውም ለመያዝ ሞክሩ፡፡ ከሁሉም በበለጠ ግን የጦርነቱን ጊዜ እንዲያሳጥርልንና የመስዋዕትነቱን መጠን ከተባለውና ከሚባለውም እንዲያሳንስልን ለፈጣሪ እንጸልይ፡፡ ጥጋበኞችም ሰከን ብትሉና ማሰብ ብትጀምሩ የጥፋት አድማሱ ይጠብና ወጪያችን ይቀንሳል፡፡

12 Comments

  1. ተወደደም ተጠላ ጥሬ ሃቁ ከዚህ በላይ የተቀመጠው ነው። እውነትን እንዳለች የሚያስቀምጡትን አንዳንድ አስመሣዮች ሊጠሏቸው ቢችሉም እውነት ግን አትለወጥም።

  2. ቤንዚን አርከፍክፈን ክብሪት እንጫርበት ባይ ምነው በዛ ። ጥላቻን የዘራ ጥላቻን ያመርታል ። በኦሮሞ ሕዝብና በአማራ ሕዝብ መካከል ክብሪት እንጫር ባትል ጥሩ ነበር ፤ ሁለቱ ሕዝቦች በኅብረት ለሀገሪቱ ዕድገት ቢሠሩ ይሻላል ።

    • Gobez ትክክል ብለሃል፤ “ጥሩ ተመኝ ጥሩ እንድታገኝ” ሥለሚባል ጥሩ መመኘትህን ወድጄልሃለሁ።ግን ምኞት ብቻውን የትም አያደርሥም። ለመጪ አሥከፊ ሁኔታዎች ካልተዘጋጀን በአካልም በመንፈሥም እንጎዳለን። ካልኩት ሁሉ አንድ ሀሰት ቢገኝ እቀጣለሁ። እንዲያውም ሀሰት በሆነና ቃላባይ በተባልኩ። ግን ለዚያ ሥድብ “የምታደል” አይመሥለኝም። ጥሩ መመኘትህን ቀጥል/ይ። ጥሩ ነው። መሬት ላይ ፈጥጠው የሚታዩ ሥጋቶችን ግን አትናቅ። የምትለው ቢሆን እልል በቅምጤ ነው። ለሀገሬ ካንተ ባልተናነሰ እንደምጨነቅ ደግሞ ተረዳ። ስለዚህ እውነትን ብቻ ከመናገር ውጪ አላሟርትም።

  3. Gobez ትክክል ብለሃል፤ “ጥሩ ተመኝ ጥሩ እንድታገኝ” ሥለሚባል ጥሩ መመኘትህን ወድጄልሃለሁ።ግን ምኞት ብቻውን የትም አያደርሥም። ለመጪ አሥከፊ ሁኔታዎች ካልተዘጋጀን በአካልም በመንፈሥም እንጎዳለን። ካልኩት ሁሉ አንድ ሀሰት ቢገኝ እቀጣለሁ። እንዲያውም ሀሰት በሆነና ቃላባይ በተባልኩ። ግን ለዚያ ሥድብ “የምታደል” አይመሥለኝም። ጥሩ መመኘትህን ቀጥል/ይ። ጥሩ ነው። መሬት ላይ ፈጥጠው የሚታዩ ሥጋቶችን ግን አትናቅ። የምትለው ቢሆን እልል በቅምጤ ነው። ለሀገሬ ካንተ ባልተናነሰ እንደምጨነቅ ደግሞ ተረዳ። ስለዚህ እውነትን ብቻ ከመናገር ውጪ አላሟርትም።

  4. የነፍጠኞች የጩኸት እስትራተጂን እውነት ለመፈለግ ና ለማግኘት በጩኸቱ በተቃራኒው አቅጣጫውን መመልከት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡

    ኦሮሞ ተረኛ ሆነ ብለው ጩኸት ካበዙ እነሱ ተረኛ እየሆኑ ነው ማለት ነው፡፡

    ተገደልን ተጨፈጨፍን ብለው ጩኸት ካበዙ እነሱ እያደረጉት ነው፡፡

    ተገፋን ተበደልን ብለው ጩኸት ካበዙ እነሱ ሌላውን እየገፉ ነው፡፡

    ተፈናቀልን ተሰደድን ብለው ጩኸት ካበዙ ወይ እያፈናቀሉ ነው ወይ ነዋሪውን እየተተናኮሉ ነው ፡፡

    ቤተክርስቲያን ተቃጠለ ብለው ጩኸት ካበዙ ወይ እራሳቸው እያቃጠሉ ወይንም የሌላውን ለማቃጠል እየተዘጋጁ ነው፡፡

    ስለዚህ እስከ ዛሬ እንደታየው ነፍጠኞቾ ስለማናቸውም ጉዳይ መጮህ ፤ ማጯጯህ ና ማስጮህ ከጀመሩ እውነቱ ያለው በተቃራኒው መሆኑን ሌላው ህዝብ መረዳት አለበት፡፡

  5. አማራው ከነኚህ አረመኒዎች ጋር ፣ የሞት የሽረት ጦርነት ማድረጉ አይቀሬ ነው። ይለያል። ለዚያ ያብቃን

  6. “Biet yqaTelal!” alech alu ibd. A mad woman shouted “a house will be on fire!”. She repeated it all the time, but people ignored her “warning” as the usual non-sense of a deranged person. On the 3rd day she herself set a house on fire, and satisfied at her did stated, “I told you!”.
    Here, Gudu Kasa is warning us in the same fashion. And mind the history of his name sake, the Kasa aka Emperor Teodros of the 1840s, who used to squeeze as many humans, including children, women and the elderly, into a hut and burn them alive!

    • Abba Caala, my name sake is not the Emperor you mentioned. It is the name of a character in the Amharic novel ‘Fikir eske Meqabir’ written by (H)addis Alemayehu. And I don’t have the cruelty you mentioned; perhaps,you might have it. Please try not to be over-judgmental.

  7. ወንድሜ ጉዱካሳ!
    ነግርዬው እንዲህ የከፋ ነው ብለህ ነው? ምናልባት እንደዛ የመሰለህ የነዛ ጽልመቶች የተወሳሰበ መዋቅር ምንም ባለመነካቱ ሆን ብለው አማራውና ዖሮሞው ሆድና ጀርባ ሆኖ ማዶ ለማዶ እንዲቆሙ ስላደረጉ ይመስለኛል። ባለፉት አመታት ከበጣም ጥቂት የኦህዴድ ባለሟሎች በቀር እንደ ምድር አሸዋ የበዙት የኦህዴድ ለወያኔ ጃንጥላ ያዦች አሁንም ከአክራርያን ጋር በመመሳጠር አቢይን ለማሳጣት ከፍተኛ ደባ እየሰሩ መሆኑን አትዘንጋ። ከቀበሌ እስከ ላይ መዋቅርም የ ፭ ለ ፩ ስምሪት ይህንኑ ነው አሁንም የሚያሳየው። መች ተፈታና። ይህም አንተ የፈራህውን መአት ሊያመጣ ጊዜው የቀረበ ቢያስመስልም እውነታው ግን ሲሞቱ ይንፈራገጡ እንደሚባለው በሸገር ላይ ይህ ሁሉ ያንዣበበ ያስመስላል። እመነኝ ምንም በሁለቱ ህዝቦች መሀል ጦርነት አይመጣም። በአክራርያንና በጽልመቶች ላይ ግን መአቱ ይመጣል። ወይ በህብረታችን ካልሆነም ከፈጣሪ። ይህው ነው። ሌላው ደግሞ ማስተዋል ያለብህ አገርወዳድ ሁሉ ድምጹን ከፍ አድርጎ ስለአብሮነትና በጥንካሬ መመከትን እንጂ የጽልመትን ምኞት ከፍ አድርጎ አደባባይ ምሬትን ለጠላት እጅ እንደ መስጠት ነው። በጭራሽ እምቢ ማለት ነው እንጂ ። ይቺን የመከራ ጊዜ እንሻገራታለን። አይዞን።

    • Abbawirtu, endafih yadrgilin. yenegerochin ayayazina akahed tazbe endih alku enji yefetari sirama enkuanis kefokere keworeworem slemiawotta nigirtu bayqerim ye’eskahunun megefatachinin qotrolin antem endalkew beqelalu liashagren yichilal.Bertalign wondime,gembina astemari tsihufochihin begugut kemiketatelu andu negn.

  8. Your guess about the possible war between Oromo & Amhara is far from truth. The Amhara & Oromo political elites are those instigating the war. If you are not the one from Amhara and Oromo political elites contributing to this war, try to reach out to the likes of you clearly understand the root causes of the struggle between the political elites. As I understand, the Amhara extremists are not ready to negotiate with the other people who complained that they were supressed under the existing Ethiopian rule. on the contrary, the oppressed people are not well prepared to clearly tell to the public that the main sources of the current conflict is based on false historical narratives that were established by admirers of the Abyssinian rulers. The Amhara elites wanted to maintain the status quo by advertising and modelling that the Amharas are the core people for the establishment of the Ethiopian Empire irrespective of the vast resources mobilized from the original lands of the subject people which used to be humiliated on their own ancestral lands attaching to them vulgar names they have never heard of. so, the should be the time to reflect on the past history and agree on what has been done and confess the crimes committed by the kings the Amhara elites are appreciating. The other ethnic groups should also be prepared to negotiate on how to live together in the future after the elites confessed the crimes committed by their forefathers, under the pretext of unifying the country. Therefore, lack of appreciating the problem of each other and only resisting to stick to old false narratives will take us anywhere.

  9. አቶ ባራባስ፣
    ማን ማንን ይቅርታ እንደሚጠይቅ በቅርቡ ማየታችን አይቀርም። ከ20 በላይ ነገዶችን ከኢትዮጵያ ምድረ ገፅታ ማን እንዳጠፋ ታሪክ ያውቀዋል። የፅንፈኞች ትርክትሀን ወደ ጎን። የማይታወቁበት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ሆነ ያንተ ነገር። ሀሰት ሲደጋገም እውነት ይሆና ያለው የጀርመኑ ፕሮፖጋንዳ ሚንስትር ጎብልስ፣አለመሆኑን ተገንዝቦ እራሱንም ቤተሰቡን በመርዝ ገድሏል።ጀርመንንም ለትልቅ ፍዳ ዳርጓትም ነበር። ጀርመኖችም የአለምን ሕዝብ ላደረሱት ስቃይ ይቅርታ ጠይቀው የህሊና ሰላም አግኝተውበታል።ለዛም የአሁኑ እድገታቸው ምስክር ነው።

Comments are closed.

Share