የኢሳን (የሶማሌ ጎሳ) ውለታ ፣ አማራ እንዳይረሳ!! –  (ናኦድ አፍራሳ)

ህይወት ያለው ፍጡር  ሁሉ ፣ ቀኑ ሲደርስ እንደሚያልፍ ሁሉ፣ ክፉም ሆነ ደግ ነገር ፣ እድሜ አለው። ለአስራ ሰባት አመታት ኢትዮጵያውያንን ሲያሰቃይ የኖረው ብልሹው  የነመንግስቱ ሃይለማርያም አመራር፣ አገሪቷን ለወራሪዎች ሲያስረክብ፣ ‘አማራን የማጥፋቱን ነገር፣ አደራ’ ያላቸው ይመስላል።

በወያኔና ኦነግ ስር የወደቀቸው ኢትዮጵያ ፣ የመጀመርያው ሰለባ ፣ የሆነው ያው የፈረደበት፣ ያልጠረጠረና ያልተሰናዳው አማራ ነበር። በደርግና በገዛ መሃይምን ልጆቹ፣ በአድሃሪነት ተፈርጆ፣ ትጥቁን ፈትቶ፣ ሃብት  ንብረቱን ተዘርፎ፣ መሬቱን ፣ ተቀምቶ ፣ በጅምላ ብዙ ሺህ አማራ እንደተፈጀ ይታወቃል። የተረፈውም፣ ለድህነት ተዳርጓል ።  በዳር አገር ይኖር  የነበረው አማራ ፣ ከደረሰበት መከራና  ድንጋጤ ሳያገግም ፣ ወያኔና ኦነግ በአዋጅ  ጦርነት አውጀው በርካታ ሺ አማሮች ተፈጁ። እልቂቱ እድሜ ለኦነግ እና ወያኔ፣ ዛሬም አላሰለሰም ። በተለይ በሃረር ፣ በአርሲ፣ በባሌ ፣ በወለጋ፣ በጂማ፣ በኢሉባቦር፣ እልቆመሳፍርት የሌለውን አማራ፣ ኦነግ በቁም እያቃጠለና ቆዳቸውን እየገፈፈ፣ አይን እየጎለጎለ፣ ምላስ እየቆረጠ፣ አንገት እየቀላ፣ ገደል እየከተተ፣ ሴቶች እየደፈረ፣ መፍጀቱ የቅርብ ግዜ ትወስታ ነው። ጉድ እኮ ነው ያሰኛል።  የዛሬቱ ኢትዮጵያ፣ ወራሪ ኦሮሞዎች አሳዳጅ፣  ነባሩ አማራ ደግሞ ተሳዳጅ፣ የሆነባት አገር መሆኗ ።  የአቢይ ኦነግ መንግስት፣ ገና በመውተርተር ላይ ያለውን፣ ያማራ ድርጅት አባላት በሃሰት ወንጅሎ፣ አስሮ የሚያንገላታው፣ የሚገድለው፣ አይቀሬውን የሞት የሽረት ትግል፣ ለመግታት ነው። ይህ ከንቱ ሙከራ ነው። መሬት በሺህ አመቱ ለባለቤቱ ነውና፣ የኦሮሚያቸውን ህልም ፣ እንደ ጉም መትነኑ አያጠራጥርም። ጀግናው ሶማሌ ያለይሉኝታ  ተስፋፊን ኦሮሞ፣ ከኦጋዴን መንግሎ እንዳስወጣ ሁሉ፣ ሌሎችም ነባር ኢትዮጵያውያን፣ አያደርጉትም ማለት አያስደፍርም።

     ኢሳ (ሶማሌ )፣ አማራን ከኦነግ የታደገ፣ ጀግና ነው

‘’ሰው ማለት፣ ሰው የሆነ ነው፣ ሰው የጠፋ እለት ‘’ የሚለው ያበው አባባል ፣ የድንቅ ወገኖቻችንን ፣ የኢሳዎችን ማንነት እንድናነሳ ግድ ይላል። ኦነግ በገጠር ሃረርጌ  የፈጀው አማራ ሳያንስ፣ ድሬዳዋም ከተማ፣ ያልታጠቁን አማሮች ጭፍጨፋ፣  ከመቅጽበት ያቆሙት ጨዋና ጀግኖች የኢሳ (ሶማሌ) ያገር ሽማግሌዎች ነበሩ። የወራሪ ኦሮሞዎች ተጠሪ ነኝ ባዩ ኦነግ፣ አማራውን ከአጽመርስቱ የሚያፈናቅለው መጤ ነህ ብሎ ነው።   የዛሬ 28 አመት ኦነግ ድሬደዋ የፍጸመውን ማንሳት፣ ለዚህ ጸሃፊ ቀላል አደለም። በኢሳ/ ሶማሌዎች ጣልቃ-ገብነት ነበር የኦነጉ ፍጅት ፣ በ68 አማሮች ግድያ ብቻ  ያባራው።  ከሟቾች መሃል ፣ የዚህ ጸሃፊ እናትና አንድ አጎቱ ይገኙበታል። ‘’ዝናብ ሳይመጣ ሁሉ ቤት፣ እንግዳ ሳይመጣ ሁሉ ሴት’’ እንዲሉ፣ የሰው ማንነት የሚታወቀው በክፉ ግዜ ነው።  ቀን የጎደለበት አማራ፣  የጨዋው የኢሳን ፣ ውለታ ሊረሳ አይችልም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጭራቅ አሕመድ ግርማ የሺጥላን ገድሎታል - መስፍን አረጋ

አንባቢ ልብ ሊለው የሚገባው ሌላ ጉዳይ አለ። እነኝህ ሶማሌ ወገኖቻችን ፣ ይህን የመሰለ ለዕልና ያስዩት፣ ታምራት ላይኔ የተባለው፣ የወያኔ አገልጋይ፣ ድሬደዋ መጥቶ ፣  ‘’አማሮች ምንትስ ይሏችሁ ስለነበር ፣ አሁን ግዜያችሁ ነው፣ ፍጇቸው’’ ብሎ ጃስ ባለ፣ በወራት ግዜ ውስጥ ነበር። ታምራት ይህን ሲል ፣ ታዳሚ ሶማሊዎች እንደተጸየፉት ፣ ቪዲዎን የተመለከተ ይገነዘባል።  እግዜር ይባርካቸውና ኢሳዎች የበርካት ሺህ ያልታጠቁን አማሮችን ህይወት ድሬደዋ ታድገዋል። ጀግና ፣ ጀግናን ያከብራል። ኢሳ፣  ያማራን ጀግንነት ጠንቅቆ የሚያውቅ ስለሆነ፣ እነኝህን የክፉ ግዜ ወገኖቻችን፣ ድፍን ኢትዮጵያዊ በተለይ አማራው፣ አይረሳውም።

ሶማሌዎች ነባር ኢትዮጵያውያን እንደመሆናቸው መጠን፣ አትንኩኝ ባይ ስነልቦናቸው ግልጽ ነው ። የድሬዳዋ ኢሳዎች ፣ የኦነግን የፈሪ ድርጊት ፣ የተጸየፉት  ያልታጠቀን፣ ያልጠረጠረን፣ ሴትና ህጻናትን ጭምር አድብቶ መግደል ስለሚረዱ ነው። በሃይለስላሴ ዘመነ መንግስት፣ ከዲሮ ሰይድ የሚባል ብርቱ የኢሳ ተወላጅ  በትምርቱ፣ አቻ ያልነበረው ትዝ አለኝ።   ለአራት አመታት ፣ ወደ ድሬደዋ ሄዶ መማር ስለነበረበትና የወላጆቹ አቅም አልፈቀደም። ታድያ አንድ ሻለቃ ደጀኔ በሻህ የሚባሉ ሰው፣ ከሶስት  ልጆቻቸው ሳይለዩት፣ ልከው ያስጨርሡታል። ክዲሮ አሜሪካም ለትምርት ሄዶ፣ ከአንደኛ በታች ወጥቶ አያውቅም።  ኢትዮጵያዊ በዋለበት ሁሉ ቁንጮ መሆን አለበት፣ የሚል ጽኑ እምነት የነበረው ወዱ ኢሳ ጓደኛዬ።

             የሶማሌዎች ጥንታዊ ኢትዮጵያዊነትና፣ ወራሪን ኦሮሞ “ጋላ” ያሉበት ምክንያት   

የሶማሌዎች ታሪክ ከረዥሙ የእትዮጵያ ታሪክ ሊነጠል የሚችል አደለም። አማራው ጋር የነበራቸው ዝምድናም ፣ የረዥም ትውልድ ታሪክ ነው። የመን የኢትዮጵያ አካል በነበረችበት ግዜም ሆነ ቀደም ሲል፣ ሶማልያ የኢትዮጵያ አካል ነበረች ። አጼ ዘርዐያእቆብ ፣ በውሃ እጥረት ይቸገሩ የነበሩን ወገኖቹን ለመታደግ፣ ከ 300 በላይ ኤላ ( የውሃ ጉርጓድ ) በኦጋዴን ያስቆፈረው፣ በ 1450 አመተ ምህረት አካባቢ እንደነበር አይዘነጋም።  ዛሬ ድረስ ቀብሪ~ደሃር አካባቢ አገልግሎት የሚሰጡ ጉርጓዶቹ እንዳሉ፣ ምናልባት ብዙ ሰው አያውቅ ይሆናል። ይህ ክስተት ፣ ኦሮሞዎች ኢትዮጵያን ( ሃረርን ጨምሮ) ከመውረራቸው 120 አመታት በፊት ነበር።  የወያኔዎች አገልጋይ የነበረው አብዲ ኢሌ ፣ አማሮችን  በቅርቡ ያስጨፈጨፈና፣ ቤተክርስቲያናትን ያቃጠለው፣ በጌቶቹ በወያኔዎች ትዛዝና አይዞህ ባይነት ነበር። ስለዚህ ድርጊቱ፣ ሶማሌዎች አይመለከትም። ሶማሌዎች በአማራ ወገናቸው ተመሳሳይ ወንጀል ፈጽመው አይውቁም። በተስፋፊ ቱርኮች ይደገፍ የነበረውን የግራኝን የጥፋት ዘመቻም፣ የሶማሌን ማንነት አይገልጽም። ሶማሌ ጀግና ፣ ለፍትህ ሟች ህዝብ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ግንጊልቻ (Gingilchaa)- የጠቅላዩ የፓርላማ ውሎ ትዝብት... በ-ሙሉዓለም ገ/መድኀን 

ሶማሌ ከ 400 አመታል በፊት ፣ ጋል  የሚላቸውን ኦሮሞዎች ከድንበሩ እንዳበረረ ሁሉ፣ በቅርቡ ደግሞ፣ ከኦጋዴን ነቃቅሎ የጣላችው፣ ወራሪነታቸውን ስለሚያውቅ ነው። ጋላ የሚለው ስያሜ፣ ሶማሌ ለኦሮሞ ያወጣላቸው ነው። ፍቺውም ሃይማኖት የለሽ ነው። ዛሬ በሰው አገር፣ ኦሮምያ የሚል ምድር ከልለዋል። ይኽ ከንቱ ድካም ነው።  በማን አገር? ኦሮምያ ማለትም ወንጀል ነው።

ስለኢሳ ከተነሳ ፣ አንድ የሞቃዲሾ ተወላጅ የሆነ ሶማሌና ፣ ድሬደዋ (አፈተ-ኢሳ እሚባል ሰፈር) ተወልዶ ያደገ አማራን ታሪክ ላንሳ። ሁለቱ በስደት ካናዳ ገብተው ቶሮንቶ መሰናዶ ኮለጅ ይገናኛሉ። አማራው እንደ ወላጆቹ ፣ ሶማልኛን፣ አቀላጥፎ ስለሚናገር፣ ጓደኛሞቹ፣ ዋና ቋንቋቸው ሶማልኛ ነው።  ሁለቱም ብሪቲሽ ኮለምቢያ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በተለያዩ ምህንድስና ዘርፍ ከተመረቁ በኋል፣ የድህረ-ምረቃ ትምርታቸውን አገባደው፣ አንዱ ሞንትሬል፣ ሌላው ሎንዶን ኦንታሪዎ ይኖራሉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን ነው ያገቡት ።  ለ 38 አመታት ፣ ያልተለያዩት ጓደኛሞች ፣ ልጆቻቸውም፣ እንደ እህትና ወንድማማች ፣ የሚዋደዱ ናቸው።  ኢትዮጵያዊው የድሬው ተውላጅ ፣ የዚህ ጸሃፊ ታላቅ ወንድም ነው።  ስለዚህ ይህ ጸሃፊም እንደ ታላቅ ወንድም የሚያየውን  ፋራህ መቅተልን ፣ለ32 አመታት ያህል ያውቀዋል።  ከፋራህ የተማራቸው አንዳንድ ቁም ነገር በመትቀስ ጽሁፉን ይቋጫል።

ሶማሌዎች ለኢትዮጵያ የጠላትነት መንፈስ እንዲስርጽባቸው ያደረጉት የግብጽ መህምራኖች መሆናቸው አንዱ ነው። ይህም የሆነው፣ከሶማልያ ነጻነት በኋላ፣ መምህራኖች ይመጡ የነበረው ከግብጽ ስለነበር ፣ እነኚህ መህምራን፣  ኢትዮጵያውያንን እንድ ጭራቅ/ (ኢብሊስ) አድርገው ነበር የሚስሉት አለ ።

ቀጥሎም ፣አንድ ህዝብ መሆናችንን የተረዳሁት ፣ በስደት ቢሆንም፣ ከጥንት ታሪካችን ፣ አንድ ህዝብ እንደነበርን ብዙ መረጃ ተገኝቷል። ይሄም ፣ ሞቃዲሾ ውስጥ ፣ ለህንጻ ስራ መሬት በጥልቀት ሲቆፈር፣ ብዙ የኢትዮጵያ ጽሁፍ መገኘቱ ላንድነታችን አንድ ምስክር ነው የሚል ነብር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሃላፊነትና ተጠያቂነት ዜሮ የሆነባትን ኢትዮጵያን እንዴት እንታደጋት? - አክሎግ ቢራራ (ዶር)

ሌላው የጠቀሰው ነገር፣ ሶማሌዎች፣ ልክ እንደ ኢትዮጵያውያን በአለም ሁሉ በስደት መበተን ነው። ሆኖም ሶማሌዎች ፣ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ እንዳገራቸው ተደላድለው መኖራቸው ፣ አሌ የማይባል ሃቅ ነው። ይኽም የጠበቀና የጠለቀ የስነልቦና አንድነት  እንዳለን ፣ ሌላ ምስከር ነው የሚል ነበር።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

(ናኦድ አፍራሳ)

6 Comments

  1. you are just a hater. Somalia, isa, oromo and Amhara need each other and live together. you sound like a looser. and please dot spread your venom.

  2. “If we are not going to kick the gallas out of ogaden, they will claim berbera.” That was what one somali told me. Coward amhara have to learn. But amhara spend most of their time crying “bloody murder” time and time again.

  3. አላህ ይባርክህ ይኔ ወንድም። ወልታን ማወቅም ሆነ መክፈል፣ የትልቅነት መለኪያ ስለሆነ። ቋንቋን ቀርቶ፣ ምንንም ማወቅ ይበጃል። አማርኛ ዛሬ ፣ የማያስተምር እውቅ ያውሮጳና አማሪካ የትምርት ተቋማት የሉም። ጥልቅና ረቂቅ ስለሆነ ደግሞ ጠቀሜታው ፣ ቋንቋው ከሚያገለግልበት መገናኛነት በላይ ነው።
    በርካታ አመታት ከወላጆቼ ጋር ፣ ከደሴ፣ ያኔ አዳልና ኢሳ ይባል በነበረበት አካባቢ ሄጀ ሳድግ፣ ከማርኛዬ ሌላ፣ ሶማልኛና አፋርኛም የተካንኩ ነኝ። ደርግ ሲመጣ ከለቀቅሁ 45 አመታት ቢሆንም፣ እስከዛሬ ፣ ሁለቱንም ቋንቋዎች እናገራለሁ። ኦሮሚፋንም እሰማለሁ።
    ያንን እድል አግኝቼ ፣ ከነኚህ ወገኖቼ በቅጡ መተዋወቅ፣ እጅግ እንደበጀኝ፣ የተረዳሁት፣ ውጭ የኖርኩባቸው ሁለት ያውሮጳ ሃገሮችን ቋንቋዎችን ገርመናና ፈረንሳይን አቀላጥፌ መናገሬ ነው። አሁን እምሰራባት ለንዶን፣ የተመደብኩት፣ ሶስቱን ያውሮጳ ቋንቁዎች በመቻሌ ነው።
    አዎ፣ የአፍርና ኢሳዎች ( የሶማሌዎች) ኩራትና ጀግንነት፣ ጠቅልላ ስነ ልቦና፣ በዘመዶቼ ካየሁት የተለየ ባለመሆኑ፣ በእኔም በኩል፣ የነባር ኢትዮጵያዊነታቸው አንዱ መገለጫ ነው።

  4. The commendable piece by Suleiman Yimam resonates with my own experience.

    Having trodden thousands of miles across Africa from Gondar to Cape Town, in the company of mostly Somalis from the mainland as well as a few Ethiopians, I can never forget their singular commitment to help me oversome some of the challenges I had as far as food was concenened.

    They have always been by my side in adversity. When I was down with malaria and I had the most horrid experience in Tanzania, they were the ones who saved my life by pleading to the authorities of a mosque.

    I still vividly remember how Abdi used to address me as ‘Woriyah Mulugeta’
    Let me take this opportunity to say ” nebed galio” to my dear brothers Abdulahi Awalie, mohamed Shiek Adem and Adem Nur who have also happily been accorded asylum in Europe.

  5. The famous journalist and H/Selassie’s most trusted interpreter Ato Samuel Ferenj wrote a touching piece a very long time ago. Ato Samuel was president of Ethiopian Television for ten years. That article he wrote was about Ethiopian prisoners in Somalia and I think it was a response to some other guy in New York who believed he was going to Djibouti and landed in Somalia instead when he lost his way. The story was about how the refugees were innocent civilians but were imprisoned on suspicion of spying. The banana plantations described are exactly how the historian Tekle-Tsadiq Mekurya described them more than half a century earlier. Samuel the journalist claims the Ethiopian Somali broke prisons and freed all Ethiopian prisoners and gave them protection for days walking on foot to safety. The Addis Ababa guy from New York wrote almost the exact same thing and said the rebel soldiers were Somalians from Somalia but they were the same tribe with some of the Ethiopian Somali in prison with them.

  6. Yes..oromia yemibal neger yelem..Fetegar was Bale and Arsi…Enaria was Elibabur and Jimma..selezih oromia yelem.

Comments are closed.

Share