ፌደራሊዝም እነርሱ ሲሉን እኛ ፌደራሊስም ስንል እና የአፓርታይድ ስርአት – መንግስቱ ሙሴ

የዛሬ 69 አመት ህወሓት እና ኦነግ ከመፈጠራቸው 17 አመታት ቀደም ብሎ የደቡብ አፍሪካ የትቂት ነጮች አፓርታይድ መንግስት ለደቡብ አፍሪካ እና ለደቡብ ምእራብ አፍሪካ ሕዝቦች የራሳቸው ፌደራሊዝም ሰጥተው ነበር። የአፓርታይድ ነጮች የመሰረቱት ፌደራላዊነት ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለው አይነት የሚመሳሰል ፌደራላዊነት ነበር። የአፓርታይድ ነጮች 10 Ethno-linguistic (የዘር እና ቋንቋ) ተመሳሳይነት ለአላቸው የደቡብ አፍሪካ ጎሳወች Bantu homeland በሚል የራሳቸው የሆነ የዘር ክልሎች መስርተው ሰጧቸው። እነዚህ የባንቱስታን ክልሎች በተለያየ አመት የተከለሉ ሲሆን ትራንስካይ (Transkei) 1976, Bophuthatswana 1977, Venda 1979, Ciskei 1981 እና ሌሎች ስድስቱን ጨምሮ  Gazankulu, KwaZulu, Lebowa, KwaNdebele, KaNgwane እና Qwaqwa ን በተመሳሳይ አመት ከልለው ለጥቁሮች ከሰጡ በኋላ ባንቱስታ የጥቁር አፍሪካውያን ሆምላንድ በሚል የዘረኛ ስርአታቸውን አጠናክረው ነበር።

ህወሓት/ኢሕአዴግ በ 1987 አም ባጸደቁት ህገመንግስት የደቡብ አፍሪካ ነጮች በደቡብ አፍሪካ ጥቁሮችን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ጉዳይ ተሳትፎ ለማሳነስ እና ለትቂት ነጮች የተመቸ የማያስቸግር የስልጣን የበላይነታቸውን ማስቀጠል የሚያስችል በ 1950 እ ኤ አ ያደረጉት ህገመንግስት የባንቱስታን ወይንም Ethnic homeland ለአስር ጎሳወች የየራሳቸው ሆምላንድ ፈጥረው ሰጡ። ይህ የጎሳ ክልል በአለማቀፍ ማህበረሰብ የተወገዘ እና ፍጹም ዘረኛ የሆነ ስርአት ተብሎ የአፓርታይድ ነጮች እስከወደቁበት ተወግዟል። በሀገራችን በተለያዩ ጦርነቶች የተዳከመች ሀገራችንን ድል አድርገን ስልጣን ያዝን የያዙት የዘር ድርጅቶች አንዱ ሀገር ከፋፋይ እና ለእራሱ ከአልኋ ምላሽ በሚል ስሌት አስፋፊ ሌላው ከሀገር ገንጣይ በመሆን ድርሻ ድርሻቸውን ከወሰዱ በኋላ ቀሪዋን ኢትዮጵያ ልክ እንደአፓርታይድ ደቡብ አፍሪካ የባንቱስታን ክልል ግዛቶች የተመሳሰለ Ethnic homeland መሰረቱ። ከጥንት ሲዋረድ የመጣውን የአገዛዝ ድንበር አንዴ ጠቅላይ ግዛት፣ ሌላ ግዜ ክፍለሀገር ይባል የነበሩትን አፍርሰው ቋንቋን እና ዘርን የተንተራሱ ዘጠኝ ክልሎች አድርገው ሰሯቸው። ልክ እደደቡብ አፍሪካ የጎሳ ባንቱ ግዛቶች ሁሉ ኢትዮጵያም ውስጥ ምልአተ ሕዝቡ ያልተሳተፈበት አግላይ የሆነ የፖለቲካ ፕሮግራም በማጽደቅ ሕገመንግስት አጸደቅን ብለው በ 8ኛው አንቀጽ የኢትዮጵያን ሉአላዊ ሀገርነት ሰርዞ ብሄር፣ ብሄረሰስቦች፣ እና ሕዝቦች ሏላዊ ናቸው የሚል ህግ ደነገጉ። ዘጠኙ የጎሳ ክልሎች ልክ እንደ ደቡብ አፍሪካ የባንቱ ክልሎች መስፈርታቸው ቋንቋ ሆነ። እነዚህን የቋንቋ ግዛቶችን ከፈጠሩ በኋላም እስከመለየት የሚያበቃ መብትም አንቀጽ 39 ብለው ጨመሩላቸው።

የደቡብ አፍሪካ ነጮች ነጻ ግዛት ለጥቁሮች ሰጠን በሚል የራሳቸው ስልጣን አላቸው በሚባሉ ስድስት የባንቱ ግዛቶች 1/3 ኛው የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ተገዥወች እንዲኖሩበት ተደረገ። የውጭ ፖሊሲ፣ የወታደራዊ እና ደህንነት አለማቀፍ ግንኙነት እና አለማቀፍ ንግድ በትቂት ነጮች ስር ሆኖ የአፓርታይድ ነጮች በዘር እና ቋንቋ ከፋፍለው መላ የደቡብ አፍሪካን ግዛት በእነርሱ ቁጥጥር በማድረግ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ገዙ።

ኢሓዴጎች የሚሉት ፌደራሊዝም

በአይነቱ ልዩ የሆነ በየትኛውም አለም ያልተሞከረ ከላይ ካሳየሁት የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ መንግስት ውጭ በነጻ ሕዝቦችም ሆነ በነጻ ሀገራት ያልታየ ፌደራሊም የህወሓት/ኦነግ/ኢሕአዴግ ፌደራሊዝም ተብሎ ለኢትዮጵያ ስርአትነት ተደነገገ። ይህን ፌደራሊዝም ልዩ የሚያደርገው

The Constitution provides sovereign power to all nationals and people of Ethiopia.

The sovereignty can be determined by selecting representative as per Constitutional laws and by actively participating in the democratic process.

ይህ ማለት ህገመንግስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ እራሳቸውን የቻሉ ሉአላዊ ሀገራት እና ሕዝቦች እናዳሉ መደንገጉ ነው። በአንድ ሀገር ውስጥ የተለያየ ሏላዊነት ሊኖር ግን አይችልም። በዚህ ሀገመንግስት ኢትዮጵያ ልክ እንደአፍሪካ ወይንም እስያ ክፍለ ሀጉር የብዙ ሏላዊ ሀገራት ስም መሆኗ ነው። የእነርሱ ፌደራላዊነት ማለት እንደደቡብ አፍሪካ ባንቱስታን የነገድ ግዛቶች ማለት ነው። የደቡብ አፍሪካ 10 የባንቱ ግዛቶች ሉአላዊ ናቸው የሚል የአፓርታይድ ህግ ነበረው። ይህ ልዩ የሆነ ህገመንግስት ልክ እንደአፓርታይድ ደቡብ አፍሪካ የባንቱ ሆምላንድ ሁሉ በአንቀጽ 46 የክልል መንግስታት እና ድንበር የተወሰነው (የተከለለው) ቋንቋን መሰረት በማድረግ ነው ይላል። ልክ እንደ ባንቱ የደቡብ አፍሪካ ግዛቶች ሁሉ የአንቀጽ 46 ድንጋጌም በኢትዮጵያ የተከለሉት ግዛቶች ዘርን እና ቋንቋን መሰረት እንዳደረጉት ሁሉ ስማቸውም ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ አማራ፣ ሶማሌ ወዘተ በሚል ነው። ይህ ደግሞ ለምሳሌ በባንቱ የክልል አከላለል ስዋዙሉ የሚባለው ክልል የዙሉ ሕዝብ ክልል የተሰጠ ነው። ትራንካይ እና ሲስካይ የተባሉት የዘር ክልሎች ለ ዥሆሳ ለተባለ ዘር የተከለሉ ናቸው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የተሳሳተው ማነው? የአሜሪካ መንግሥት ወይንስ የዐብይ መንግሥት?

ህወሓት/ኢሕአዴግ እንደመከራከሪያ በኢትዮጵያ የተንሰራፋውን የዘር ከአፓርታይድ የሚመሳሰል ስርአት በሌሎች ሀገራትም አለ ለማለት የሕንድን፣ የካናዳን፣ የስዊዘርላንድን ያቀርባሉ። በመሰረቱ ይህ መከራከሪያቸውን ብዙ የሚያፈርሱ መሰረታዊ የሆኑ ነጥቦችን ለአንባቢ ለማሳየት እንዲህ እንየው። በአለም ላይ 195 ሉአላዊ ሀገራት እና 193ቱ የተባበሩት መንግስታት አባል ሲሆኑ ከነዚህ የአለም ሀገራት ውስጥ ፌደራል ነን የሚሉት 25 ናቸው። የኢትዮጵያው ባንቱስታን ክልሎች ፌደራል ተብለው ከተቆጠሩ 26 ሀገራት ማለት ፌደራላዊ ስርአት አላቸው ማለት ነው።

ሌሎች ዘርን እና ቋንቋን ያካለሉ ፌደራል ስርአት ዋና መሰረት ያደረጉ ሀገራት ናፓል፣ ፓኪስታን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ዮጎዝላቪያ አይነቶች የመፍረስ እንጅ የመቀጠል እና ጥንካሬ የማሳየት የተረጋጋ ስርአት አይታይባቸውም ወይንም አልታየባቸውም አለያም ፈርሰዋል። ሕንድን እና ካናዳን እንደሞዴል የምትቆጥረዋ ዘረኛ የህወሓት መራሽ ኢሕአዴግ ሁለቱም በስልጣኔ እና በመረጋጋት የቀጠሉበትን አብይ ጉዳይ ለማሳየት እና ትምህርት ለመውሰድ ግን ፈቃዱም ሆነ ፍላጎቱ በሀገራችን ያሉ ጠባብ ብሄርተኞች ፈቃደኝነት አይታይም። ለምሳሌ ካናዳን አስመልክቶ ቋንቋን እና ዘርን ተኮር ፌደራል ስርአት ለመቀጠሉ ሁነኛ ጉዳይ ብዙሀኑ የካናዳ ሕዝብ ከእንግሊዝ በ16ኛው እና ከዚያ በኋላ የፈለሱ የአንግሎ ዝርያ ያላቸው እና እንግሊዝኛ ተናጋሪወች ስለሆኑ “የኩቤክ ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ላቲኖች” የመለየትን ጥያቄ ከሁለት ግዜ በላይ አንስተው ከሁለት ግዜ በላይ ለሬፈረንደም በማቅረብ ሀሳባቸው በብዙሀን ተሸንፈው በአንድነት ለመቀጠል የተገደዱበት ሁኔታን አይተናል። ከካናዳ የምንማረው ልምድ የሚያሳየን Ethno-Federalism በተረጋጋች ካናዳ እድገት ባላት ሀገር እንኳን ምን ያህል የህብረተሰብ በሽታ መሆኑን እንጅ ጥሩ ምሳሌነቱን አይደለም። ደካማ፣ ወይንም ደሀ ካናዳ ብትሆን ኖሮ “ኩቤክ” የፈረንሳይኛ ተናጋሪ ክፍለሀገር እስካሁን እራሷን የቻለች ግዛት ልትሆን እንደምትችል ለማየት በቅርቡ የተደረጉ የሕዝበ ውሳኔወች ከባድ ጫና አሳድረው እንደነበር አሳይቷል። ያውም ያደጉት የአንግሎ ዝርያ ያላቸው ሀገራት አሜሪካንን እና እንግሊዝን ጨምሮ ምን ያህል በካናዳ አንድ ሆኖ መቀጠል ላይ እንደተረባረቡ የቅርብ ግዜ ትውስታ ነው። ካናዳ የታየው በእኛዋ ደሀ ሀገር ቢሆን ኩቤክ ከኢትዮጵያ ልክ እንደኤርትራ ከሄደች ሰነባብታ ነበር።

የሕንድ ተመክሮም እንዲሁ ከካናዳ የተለየ አይደለም። ይኸውም አንድ ትልቅ ጎሳ “ሒንዱ” ሀገሪቱን ሰብስቦ በመያዙ ቀሪወች ትንንሾቹ ምርጫ ኖራቸውም አልኖረ ስርአቱ የሰጣቸውን የተሻለ ምርጫ ይዘው ባይቀጥሉ እና ሁሉም ደካማ ጎሳወች ቢሆኑ ኖሮ የህንድ እንደሀገር መቀጠል የሚታሰብ አልነበረም። ይህም ሆኖ ሕንድ ጥሩ ምሳሌ ልትሆን ለኢትዮጵያ የዘር ፖለቲካ አትችልም። ሕንድ ነጻነቷን ባገኘች በ 1947 እ ኤ አ ማግስት ፓኪስታን እና ባንግላዴሽ የተባሉ የእስልምና ተከታይ ብዙሀን ያላቸው ግዛቶች ተገንጥለው እራሳቸውን የቻሉ ሀገራት እንደሆኑት ሁሉ።፡ለአለፈው ግማሽ ምዕተ አመት የካሽሚር እንቅስቃሴ አንዴ ሲግል፣ ሌላ ግዜ ሲበርድ የቀጠለ እንጅ ሕንድ የተረጋጋ እና ፍጹም ሰላም የሰፈነባት ሀገር ሆና አልቀጠለችም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የድንበሩና የዐባይ ጉዳይ!! (አንተነህ ሽፈራው)

የካሽሚር የመገንጠል ጥያቄ እና ትግል ይዋል ይደር እንጅ ቀጣይ እና ንዑስ ክፍለሀጉሩን በቀጣይ ለጦርነት የሚያዘጋጅ እንደሆነ ግልጽ ነው። በሰሜን ምስራቅ ከ ሲንጃግ እና በምስራቅ ከቲቤት ጋር የምትዋሰነው ካሽሚር ጠቅላላ ሪጂኑን የሰላም እጦት ቀጠና እንዳደረገችው በየግዜው የሚወጡ ዜናወች ያስረዳሉ። በዘመናዊ አለም የዘር ፌደራሊዝም ይሰራል እያሉ የሀገራችን ዘረኞች የሚፎክሩበት በመሰረቱ የእኛ ፌደራላዊነት ከላይ እንዳሳየሁት የባንቱስታን አይነት ለብሄር በሄረሰብ እና ሕዝቦች ስለሚላቸው ሏላዊነት ሰጥቶ ለሽህ አመታት የዘለቀውን ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ያፈረሰ ብሎም አንዱ ከሌላው እንዳይገኛኝ ሆኖ የተቀረጸ ስርአት ነው።

ለምሳሌ የሕንድም ሆነ የካናዳ ፌደራል አሰራር ዴሞክራሲን መሰረት በማድረጉ ዜጎች የኩቤክ ክፍለሀገር ተወላጅም ሆነው ለካናዳ ሊመርጡ የሚችሉ እንጅ አንተ እንግሊዝኛ ተናጋሪ ወይንም ላቲን ፍራንኮ ስላልሆንህ መምረጥ አትችልም ወይንም መመረጥ አትችልም የሚል መብት የነፈገ አይደለም። ኢትዮጵያ ውስጥ የታየው እና አሁን በስራ ላይ ያለው ለሚሊዮን አማርኛ ተናጋሪ ወይንም አማሮች በደቡብ እና በኦሮሚያ ለሚኖሩ ወይንም እዚያው ተወልደው ላደጉ ሳይቀር ድምጽ የነፈገ ስርአት ነው። ለምሳሌ ሀረር ከተማ ውስጥ ብዙሀን አማርኛ ተናጋሪ እንደመሆኑ እና በይበልጥም አማሮች እና ጉራጌወች ብዙሀን መሆናቸው ግልጽ ሆኖ እያለ ማንነታቸውን እንዲለውጡ አለያም ድምጽ አልባ እንዲሆኑ የተደረገ እና በየትኛውም የከተማዋ መንግስት ተሳታፊ እንዳይሆኑ የተገፉበትን ድምጻቸው የታፈነበት ሀገር ነው  ፌደራል ብለው የሚያሾፉብን።፡የኢትዮጵያ ስርአት ወይንም ፌደራል አስተዳደር ተብየው ዴሞክራሲ የሌለው በመሆኑ ከፌደራሊዝም ይልቅ ለአፓርታይድ ባንቱ ሆምላንድ እጅግ ቀራቢ ነው።

ፌደራሊዝም ስንል

ኢትዮጵያን ፌደራላዊ ማድረግ ችግር የለውም። ለመስማማት ሁሉም ሀሳብ ሊያቀርብ ይችላል ይገባልም። እንዴውም ለሦስት ሽህ አመታት የዘለቀው ንጉሳዊ ታሪካችን የሚያሳየኝ ነገስታቱ አንድ ንጉሥ ብቻ ሳይሆን ብዙ የአካባቢ ንጉሦች የነበሩባት እና ንጉሠ ነገስት የሚለው ስያሜ የዘመናዊ የፌደራል አውቶኖሚን የሚያሳይ የቆየ ስርአት እንደነበረን ያሳያል። ሆኖም ፌደራሊዝም ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እና አሰራርን የሚከተል ነው። ዴሞክራሲ ከሌለ ፌደራሊዝም ሊኖር አይችልም። በሀገራችን የተንሰራፋው የዘር ፖለቲከኞች የሚያሳዩን ባህርይ ግን በጭንቀት፣ ባለመረጋጋት እና ሰላም የለሽ የፈረሰች ሀገር ሆና እንድትቀጥል እና እነርሱ መገንጠልን ሳያውጁ ነጻ የሆኑባት የዘር ክልል የመፍጠር በመሆኑ ስለዴሞክራሲ አይጨነቁም። ይህን ስለዴሞክራሲ መኖር አለመኖር ጉዳያቸው አለመሆኑን ባሳለፍነው የህወሓት 27 አመታት አገዛዝ አይተናል። ትግሬ ገዛ ብላችሁ ነው የምትቃወሙን ይሉን የነበሩ ተራ የእኛ ብጤወች እንደነበሩ ማስታወሱ በቂ ነው። ዛሬ ኦሮሞ ስልጣን ላይ መቀመጡን እንጅ ስለዜጎች ሙሉ መብት መኖር ያለመኖር ወይንም ሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊ የሆነ ሁለንተናዊ መዋቅር ይኑራት አይኑራት ጉዳያቸው ያልሆኑ ብዙ ሽሆች ዛሬ ኦሮሞ ስልጣን ስለያዘ ነው እንዲህ የምትሆኑት የሚሉ እንደተከሰቱ መገንዘብ በቂ ነው። እናም ዴሞክራሲ የሌለው ስርአት ፌደራሊዝምን ሊተገብር አይቻለውም እንላለን። ፌደራሊዝም ስንል ዴሞክራሲያዊ ሰፊ አስተዳደር ማለታችን ነው።

ይህን ስርአት የምንቃወም ዜጎች ስርአቱ አግላይ፣ ጨቋኝ፣ የሀገርን አንድነት አፍራሽ ብሎም ኢትዮጵያን አፍርሶ በሀገራችን የመጨረሻ መቃብር የቦልካን አይነት ትናንሽ ሀገራትን የመመስረት ሀሳብ እና ፍላጎታቸው ግልጽ እየሆነ መምጣቱን ስለአምናይ ነው። ፌደራሊዝም ስንል ዜጎች በየትኛውም ክልል ይኑሩ የመምረጥ እና የመመረጥ ሙሉ መንብት ይኑራቸው ማለታችን ነው። ፌደራሊዝም ስንል በየትኛውም ክልል የሚኖር ኢትዮጵያዊ መብቱ እኩል እንዲከበር ማለታችን ነው። ፌደራሊዝም ስንል የኔ የሚባል ክልል ሳይሆን የእኛ የጋራ ሀገር ብሎ ዜጋ በሙሉ ልብ አምኖ እና የመኖር መብቱም ያልተሸራረፈ ሆኖ፣ አንተ ከዚህ አይደለህም ውጣ የሚባልበት ሀገር መፍጠር ማለት አይደለም። እንደምሳሌ ለማንሳት የአሜሪካን የሁለቱ ፕሬዜዳንቶች የአባት እና ልጁ ቡሽ የትውልድ ሀገር ሜን የሚባለው በሰሜናዊ ምስራቅ አሜሪካ የምትገኝ ትንሽ ክፍለግዛት ስትሆን። የቡሾች የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የሀብት እድላቸው የሰመረ ግን ቴክሳስ ወደተባለው የነዳጅ ዘይት ሀብት ወዳለበት ሄደው በመኖራቸው እና ሀብት እና ንብረት በማፍራታቸው ሆነ። ታላቁ ቡሽ ፕሬዜዳንት ከመሆኑ በፊት ቴክሳስን በኮንግረስማን እና በሴኔትነት በመመረጥ ያገለገለ ሲሆን። ልጅየው ቡሽ ባልተወለደበት ቴክሳስ ገዥ ሆኖ በመመረጥ አገልግሏል። እንደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ቢሆን ኖሮ ቴክሳስ በአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት ተቸናፊ ከሆኑት የደቡባዊ አሜሪካ የኮንፌደሬሽን ፈላጊ ተገንጣይ ግዛቶች አንዷ እና በያንኪ አሜሪካኖች እጅ ከባድ ቅጣት የደረሰባት ናት። ይህ ማለት አሸናፊው የእነቡሽ ቤተሰብ ወደተሸናፊው ተገንጣይ ክፍለሀገር ሄዶ ለስልጣን እና ሀብት መብቃት ባልቻለ ነበር። ዛሬ ኢትዮጵያ ቢሆን ኖሮ እንደቡሽ አይነቶቹ ነፍጠኛ/ትምክህተኛ ተብለው ሀገር ለማስተዳደር ሳይሆን ለመኖር የማይችሉበት ሁኔታ ይኖር እንደነበር የአርባ ጉጉ፣ ብሎም የቅርቡ የሲዳሞ እና የለገዳዲ ፍልሰት አስተምሮናል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ትግሉ ኑረምበርግ ደርሷል"

ፌደራሊዝም ለመጀመሪያ የተጀመረው በአሜሪካን ሲሆን አሜሪካኖቹ ከ1861-1865 ያጋጠማቸውን ከባድ የእርስ በእርስ መተላለቅ ተከትሎ የነበረውን ህገመንግስት በማስተካከል የፈጠሩት የሁለት መንግስት ስርአት ነው። ትንሹ መንግስት አካባቢ ነዋሪወች የሚመረጥ አስተዳደር ሲሆን፣ የፌደራሉ መንግስት በሁሉም ስቴቶች የሚመረጥ በማድረግ እና የአካባቢው መንግስት ነጻነቱን እና መብቱን አውቆ በፌደራሉ ስር እና በፌደራሉ ሕገመንግስት መሰረት የሚያስተዳድር ነው። በየስቴቱ የሚኖር ዜጎች ባሻው ሄዶ የመኖር፣ የመስራት፣ ሀብት የማፍራት፣ ብሎም የመመረጥ እና የመምረጥ መብታቸው የተከበረበት ስርአትም ነው። ዜጎች የሚዳኙት በአሜሪካዊነት እንጅ በየሚኖሩበት ክልል አይደለም። ለምን ወደዚህ ክልል መጣህ ብሎ የሚጠይቅ ወይም ለመጠየቅ መብት የተሰጠው ሀይል የለም።

አሜሪካ የመገንጠልን መጥፎ ገጠመኝ ስላየች በህገመንግቷ ቃሉ ከህግ ውጭ ነው። የሚያነሳ ካለ የሀገሪቱን ደህንነት የተፈታተነ በመሆኑ ጥያቄ ዴሞክራሲያዊ ሳይሆን የጠላት እና የሀገሪቱን ሕገመንግስት የሚጻረር ነው በሚል ለፍርድ ይቀርባል። የአሜሪካ ሕዝብ አንድ ሕዝብ ነው እንደዜግነት የአሜሪካ ሕዝቦች ግን አይደለም። ይህ የሚያሳየው አሜሪካን ውስጥ ያሉ ክፍለ ግዛቶች ምንም እንኳን በሀብት እና በስልጣኔ እጅግ የላቁ ቢሆንም ዜግነት አንድ እና አንድ ብቻ በመሆኑ እራሳቸውን አንድ ሕዝብ  አንድ ሀገር አድርገው ይቆጥራሉ።

ፌደራሊዝም ስንል ዘጠኝ ሀገራት ፈጥረን የተለያዩ ሕዝቦች የሚኖሩበት ማለት አይደለም። ፈደራሊዝም ለአስተዳደር እንዲመች፣ ዜጎችን በቅርብ የሚከታተል እና የሚታዘዝ መንግስት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ስርአት ማለት ነው። የዜጎችን ኢትዮጵያዊነት የሚተካ ሊሆን ግን አይችልም። ኢትዮጵያ አንድ ሀገር አንድ ሕዝብ ናት። በውስጧ ግን እንደሚመች የአስተዳደር ክፍፍል ሊኖራት ይችላል። ለነዚያ የአስተዳደር ክልሎች እንደሕዝቡ ፍላጎት በጋራ ህገመንግስት ተንተርሶ ሊተዳደሩ ግድ ይላል። ለምሳሌ ቋንቋን በተመለከተ ከአንድ ቀበሌ ሌላው ቀበሌ የተለየ ቋንቋ ተናጋሪ ሊበዛ ይችላል። ትምህርትቤቶችም ተማሪወችን በአፍ መፍቻ ሊያስተምሩ ይገባል። ለምሳሌ እዚህ በምኖርበት የቴክሳስ ግዛት እና በዳላስ ከተማ ብቻ የተወሰኑ ትምህርትቤቶች መክሲኮ ቋንቋ ሲማሩ ሌላው የከተማ ክፍል በእንግሊዝኛ ይማራሉ። አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ላቲኖች እና እንግሊዝኛ ተናጋሪወች እኩል በሆኑባቸው ስርአተ ትምህርቱ በሁለቱም ይሰጣል ይህ ማለት የግድ ክልል ይፍጠሩ የሚያስብል መንገድ የለውም ማለት ነው። ፌደራሊዝም ስንል ከመብት እና ግዴታ ጋር የተያያዘ እኩል ሁሉንም የሚያስተናግድ ስርአት ማለታችን ነው።

References

Bansal, P. (2018, August 29). Federalism in India – Analysis of the Indian Constitution. Retrieved from https://blog.ipleaders.in/federalism-in-india/

Legassick, M., & Wolpe, H. (2007). The Bantustans and capital accumulation in South Africa: Journal Review of African Political Economy, 3(7), 87-107.

 

6 Comments

  1. እየቺ አገር በአማራ ካልተመራች ገደል ትግባ የሚል ስብስብ ዘር ከማጥፋት ወደኃላ የማይል ሰይጣን !

  2. What are you speaking about? Who was the creator and promoter of Apartheid among the Africans. Did you forget it. Your forefathers were the worst discriminatory gangs. They disposed the Oromo people and all other peoples in southern Ethiopia everything they had. Now you try to preach us about Apartheid? It is a ridiculous.

    Thanks to God, now the vicious circle of discrimination, latent segregation and forcefully assimilation policies have been broken by the sustainable struggle of the Oromo heroes and heroines. But it was never at the freewill of the suppressive and oppressive rulers. The struggle will go on until all our collective and individual rights will be fully restored. The Oromo Qubee generations are always ready to guard the legacies of their fathers and forefathers.

    The Oromo people accommodates with love and respect non-Oromo citizens in millions in Oromia. You will find allover Oromia all different ethinc groups from every corner of Ethiopia. We love and respect every human being and natures as far as they respect the rules of law and the the core values of OROMUUMA.

    Let me make it clear: The arrogance and stubbornness of the ultranationalists will not last long. They can bring out whatever they have in their backward and corrupted stores. This time is not like the era of Menelik. Every ethnic group knows its rights and responsibilities.

    The politics of one language, one culture and a single nation cannot be accepted any more in Ethiopia. Don’t forget that such demands have no room in today’s Ethiopian politics. But now temporally you can make noise here and there. That is all what you can do right now.

    De-Amharanisation of the whole Ethiopian politics is indispensable and absolutely necessary in order to reform and reshape Ethiopia as a country of multinational state. The politics of one language, one culture  and a single nation cannot be accepted any more. Also there is no Ethiopian identity as some idiotic individuals try preach us those like the chameleon Ermias Legesse. It is a fake identity and ridiculous. Dissociating Ethiopia from the politics of Menilik is indispensable for emancipation of all  the nations and natinalitis in Ethiopia.

  3. Gamada, the author is talking about federalism. If you agree on the system just make some corrections on the authors view and state yours. If you disagree in the general concept of federalism other than ethnic federalism the way it is now, I can asure you that it is not and needs revision otherwise we are living in one country and needs our common agreement.

    • Whether you believe it or not, you will never reshape Oromia in any negative form. But most probably we will get additional territories which were so far lost because of the stubbornness of the TPLF.

  4. The above non-sense narrative advocating for federalism favoring the domination of old styled Habesha supremacy will not work whatsoever the case might be. In the narratives, attempt was made to tell us that existence of Ethiopian state for the last three thousand years. I think this person doesn’t know history at all. Does he mean that the current day Ethiopian state existed 3,000 years ago? If so, the person must be fool himself than fooling others. All oppressed nations and nationalities clearly knows how and when the current dat Ethiopia was formed. We have never been under one rule for the last 3,00o years. It is after Minilik’s conquest from North Shawa, Menzi, which the old Abyssinian state in the north transformed to today’s Ethiopia. Minilk was advised by his French advisor to give Ethiopia to his occupied territory which more than four times greater than the old Abyssinian state as Abyssinia refers only to the northern part of today’s Ethiopia. Minilik got a good brand name that includes all the colonized people of the south, Oromia, Somali, Afar, Sidama, Hadiya, Kambata, Wolaitta, Gamo, Dawaro, kafa, Bench and others found within today’s Ethiopia. This clearly indicates that these different people used to live separately side by side with their neighbors before Minilik’s conquest.

    Secondly, the federalism that the person advocating above should not be as he likes where the rights of the settlers be respected. what should be noted is that the rights of the indigenous people need to be respected and settlers who know the language and culture of the people they live with may have the right to elect their representatives and can also be elected so long as they will be abode by the culture of the people they live with. Otherwise, the settlers should not be given the right to rule their subject people as in the past time when these people were under Abyssinian tyrannical rule.
    The USA federalism should not be thee appropriate one to be adopted in Ethiopia as USA is the country of settlers where thee indigenous people have no say at all, the language for all the states is English, the language of the settlers, and there is no historical claims of the country as thee indigenous people were already annihilated by the white settler. But, for Ethiopia, thanks to God, the settlers couldn’t totally exterminated the indigenous people and everyone is still living in his ancestral land/area. The Abyssinians have their own homeland in the north and wanted to claim all lands where they settled like Finfinne. This absurd and selfish moto will not be a good and wise way of planning to live together. Ethiopia can stay as a state so long as we respect the rights of ownership/entitlement of the given area to a given people. Waliatta cannot claim that Tigray is his homeland, Sidama cannot claim that Kaffa is his homeland. I wonder why the Amharas usually claim that all the place they live in is theirs. This a disease that need pure cure – telling them that every corner of the country belongs to a given people and the settlers have the right to live their so long as they respect the right of the people they live in.

  5. Badhoo, it appears to me you are not, neither Ethiopian, nor a modern human species that values the right of people and individual to be valued. What the author said is that in such ethnocentric the old and tplf rule of law will never work. I promise you that your types of thinking system lost all the credibility and most importantly, you guys now are in the minority don’t fool yourself. Do you know what democracy mean? While you observe the collective rights without merit denying the individual is something so backward and will never be practiced in our nation.
    Wake up if you are in sleep and look around, you do not fight with the people you hate the most (AMARAS). Your fight will be with the Somalies, the Afars, the Hadiyas, Kenbata you name the rest. When I state this not standing from your vulgar narration, rather from the very true democratic principles. The fact is, we deserve democracy and live together, because we are mixed up not as you imagine an easy phenomenon but as the smallest our food seed TEFF. Leave the hate aside and think forward for the betterment of our society. You know the Amara, Guragie, Hadiya, Kenbata everyone living the so-called Oromia (ethnic homeland) denied individual right for the last 28 years. I am not saying Derg and the medieval rulers of Ethiopia were democrats. I for one condemn the previous regimes, but your system is worse.
    Along the history part I do not want to read anything but please read Mohamed Hassan book, add to that Dr. Lapiso, Dr. Haile Laribo, and all other historians including the Ferenjis.

Comments are closed.

Share