” ፍርደ ገምድሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ !!” – በአቻምየለህ ታምሩ

“የኦሮሞ ብሔርተኞች የሚታገሉት የኦሮሞ አባ ገዳዎች ባለርቱን እያፈለሱና ማንነቱን በኃይል እየቀየሩ እንደ ዋርካ ተስፋፍተው በያዙት ለምለሙ የጋራ አገራች እምብርት ላይ ያበቀሉትን ኦሮምያ የሚባል እባጭ የኦሮሞ አገር ብቻ ለማድረግ ነው። አማራ ደግሞ የሚታግለው መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማንነቱ ተከብሮ በእኩልነት የሚኖርበት የጋራ አገር እንዲሆን ነው። ” የሚል መደምደሚያ አንብቤ አልመስልህ ስላለኝ ከሌሎች ጋር ልወያይበት አሰብኩኝ።

በመጀመሪያ ከበጎው የጋራ መነሻ ሃሳብ እንነሳ።

“አማራ የሚታገለው መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማንነቱ ተከብሮ በእኩልነት የሚኖርበት የጋራ አገር እንዲሆን ነው።”

ይህ ከባድ ሃቅ ነው። አማራው ሕብረተሰባችን በመላዋ ኢትዮጵያ በየአከባቢው ካሉ ማህበረሰቦች ጋር እንዴት በፍቅር ተከባብሮ መኖር እንዳለበት አውቆ በሰላም ተጋብቶና ተዋልዶ በመኖር ላይ ይገኛል። አቻም የገለጸውን ሃሳብ አማራ በሚለው ቦታ አብን የሚባለውን ፓርቲ ስናስገባበት ትርጉሙ ሙሉ በሙሉ ይቀየራል። እውነትነቱንም ያጣል።

አማራው ኢትዮጵያን የጋራ ሃገር ለማድረግ ሲታገል አንድ ከጉራጌ ማህበረሰብ የተወለደ ኢትዮጵያዊ የፖለትካ መሪ ከባህር ዳር ነዋሪዎች ጋር እንዴት አድርገን ኢትዮጵያችንን የጋራ አገር እንድትሆን እንታገል የሚል ውይይት ለማድረግ ቢመጣ ኢትዮጵያዊነትን ለእኛ መስበክ አቅም የለህም ተብሎ ሊገፋ ወይስ የተወሰኑ የአካሄድ ልዩነቶች ቢኖሩብንም ትልቁ ግባችን “የጋራ አገር” የሚለውን አተልቀን በመያዝ እንኳን ደህና መጣችሁ ተብሎ እንደ ዓላማ ጓድ ልንቀበለው ይገባ ነበር? ከዝህና ከበርካታ ሌሎች ነጥቦች ጋር አያይዘን አብን የተባለው ክልላዊ የፖለትካ ቡድንን የአማራው ነጸ ብራቅ አድርገን ካየነው አማራ የሚታገለው ለጋራ አገር ነው የሚለውን ያበላሽብናል።

ኢትዮጵያን የጋራ አገር የማድረግ ፍላጎቱ ያላቸው 84ቱም ብሄሮች ናቸው እንጂ አማራው ብቻ አይደለም። አቻም በተለይ በአጻጻፍህ ላይ የኦሮሞን ማህበረሰብ በሙሉ በአንድ ቅርጫት ውስጥ ከተህ ከዝህ ከጋራ አገር ከሚለው እሳቤ ያወጣህበት አካሄድ ያለውን እውነት አይገልጽም። ለምን መሰለህ? በኢትዮጵያዊነት ትግል ውስጥ እንኳን ኦሮሞ የሆኑ ወገኖቻችን በቆራጥነት ለጋራ ሃገር የሚታገሉ የኦሮሞ ልጆች አውቃለሁኝ። ዛሬ እነ ዶ/ር አብይ በልባቸው ውስጥ ስላለው ድብቅ ዓላማ ብለህ ልትከራከረኝ ብትችልም በዓለም አደባባይ ላለፉት 27 ዓመታት አንዴም ኢትዮጵያ የምትባል ቃል በኩራት ሳይገለጽባት የዘለቀችውን ሃገራችንን በ 30 ደቂቃ ንግግር ውስጥ 40 ጊዜ ስሟን የሚገልጹ መሪዎችን ከኦሮሞ ማህበረሰብ እያየን ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በግሎባል የምሁራን መድረክ ላይ የምዕራቡን ካፒታሊዝም የፖለቲካ አስተሳሰብና አካሄድ በሚመለከት በፕሮፌሰር መሳይ ከበድና በዶ/ር ዮናስ ብሩ ኢ-ሳይንሳዊ በሆነ  መልክ የተሰነዘረውን አስተሳስብ የሚቃወም ትችታዊ አቀራረብ!

በረዥሙ ሃተታዬ ውስጥ በፍጹም እንዳይዘነጋብኝ የምፈልገውና አብዛኞቻችን የምንስማማበት የጋራ ሃሳብ ‘ኢትዮጵያን የጋራ አገር” የማድረጉ ሃሳብ ነው። ይህ የአቻም ሃሳብ የእኔም ሃሳብ የብዙዎቻችን እንደሆነ ካልዘነጋን ከዝህ ቀደም በነበረን የታሪክ ዕይታ ወይም የታክቲክ መለያየት ተነስተን ሜዳውን የንትርክ እንድናደርገው አልመኝም። ይልቁንስ ትልቁ ራዕይ ላይ ኣተኩረን የጋራ አገር ለመመስረት ሃላፊነቱን በሙሉ ለአማራው ሕዝብ ልንተወው መታሰብ የለበትም በሚለው ብንመክር?

ለምን የጋራ አገር በአማራው ብቻ ሊገነባ አስፈለገው? አማአኣው ኢትዮጵያ የጋራ አገር መሆን አለባት ሲል ከኦሮሞ ከምባታ አፋር ጉራጌ ወዘተ ጋር ተጣምሮ ኢትዮጵያ ብሎ ቢነሳ ለምን ስህተት ይሆንበታል?

አቻም ኢዜማ ምስረታ ላይ አማሮች ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ኢትዮጵያን የጋራ አገራችን እናድርጋት ብለው መነሳታቸውን በሚገባ ተቃውመህ ጽፈሃል።

ከአማራው ውጪ ያለነው ኢትዮጵያዊያን እንዴት እጃችንን ኣጣምረን ተቀምጠን አመራው ሌሎቻችንን ኣግልሎ የመታገያ ድርጅቱንም በአማራ ስም ብቻ ሰይሞ መላዋን ኢትዮጵያ የጋራ አገር እንዲያደርግልን ተማምነን እንቀመጣለን? በዝህ መልኩ የጋራ አገር ናትና ተቀበሏት የምንባለውን ሃፈራችንን በምን ሂሳብ የጋራ አገር ናት ብለው ሊረከቡን ይችላሉ ተብሎስ ታሰበ?

ወንድሜ አቻም የጋራ አገር የምንገነባው በጋራ መክረን እንጂ በምን ዕዳው አማራው ለብቻው ተደራጅቶ በደሙ የጋራ አገር ሊሰጠን ይችላል? ድሮም አልሆነም ዘንድሮም ሊሆን ኣይችልም።

መላው ኢትዮጵያዊያን በጋራ በመደራጀት የጋራ አገራችንን በእኩልነት ተጠቅመንባት ተከብረንባት አክብረንባት የምንኖርባትን ድሞክራሲያዊት አገር እንገንባ።

Achamyeleh Tamiru ያስነበበን ሙሉ መልዕክት የሚከተለው ነው።

ፍርደ ገምድሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ

ተንታኝ ነኝ የሚል ሁሉ በያገኘው መድረክ እየወጣ የኢትዮጵያን ፖለቲካ የአማራና የኦሮሞ ልሂቃን ጫፍና ጫፍ ይዘው እየጎተቱ ዋልታ ረገጥ ያደረጉት አስመስሎ ሲያቀርበው ይውላል። ይገርማ! የኦሮሞ ብሔርተኞች የሚታገሉት የኦሮሞ አባ ገዳዎች ባለርቱን እያፈለሱና ማንነቱን በኃይል እየቀየሩ እንደ ዋርካ ተስፋፍተው በያዙት ለምለሙ የጋራ አገራች እምብርት ላይ ያበቀሉትን ኦሮምያ የሚባል እባጭ የኦሮሞ አገር ብቻ ለማድረግ ነው። አማራ ደግሞ የሚታግለው መላው የኢትዮጵያ ክፍል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ማንነቱ ተከብሮ በእኩልነት የሚኖርበት የጋራ አገር እንዲሆን ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ክልል ሲሉ ክልል ስንል! - አገሬ አዲስ

በኦሮሞ ብሔርተኞችና በአማራ ልሂቃን መካከል ያለው ልዩነት ምድሩንም ሰማዩንም የኦሮሞ ብቻ ነው በሚሉ አግላዮችና መላው ኢትዮጵያ የጋራችን ነው በሚሉ አካታቾች መካከል ያለ ልዩነት ነው። የኢትዮጵያን ፖለቲካ እንተነትናለን የሚሉ አፍ ነጠቆች ግን መላው ኢትዮጵያ የጋራ አገራችን ነው የሚሉትን አካታች የአማራ ልሂቃንና ሰማዩንም ምድሩንም የኛ ብቻ ነው የሚሉ አግላይ የኦሮሞ ብሔርተኞችን ጠርዝና ጠርዝ ላይ የቆሙ፤ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በመወጠር ወደ ግጭት እንዲያመራ እያደረጉ ያሉ እኩል አጥፊ ኃይሎች አድርገው ይከሷቸዋል። ይህ ግፉዓንንና ግፈኞችን እኩል የማውገዝ ፍርደ ገምድል ብያኔ የጭካኔ አስተሳሰብ ከማለት በስተቀር በሌላ ቃል ሊገልጸው አይችልም።

ለአቅመ ማሰብ የደረሰ ማንም ሰው የአባቶቻችን አገር ኢትዮጵያን በጋራና በእኩልነት የምንኖርባ የሁላችን ርስት ለማድረግ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ተሸክመው የሚታገሉንና ባለርስቱን ከቤቱና ካገሩ እያፈለሉ፤ ሀብትና ንብረቱን እየወረሱ ምድሩንም ሰማዩንም «የኦሮሞ ብቻ» ለማድረግ አገር ለመመስረት የፈጠሩትን አርማና ቆራጣ ካርታ አንጠልጥለው ሲዞሩ የሚውሉ ናዚዎችን በእኩል ሚዛን ሊያስቀምጥና እኩል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ችግሮች አድርጎ ሊያቀርባቸው አይችልም።

የኢትዮጵያ ብቸኛው ችግር የኦሮሞ ብሔርተኞች ናዚያዊና የትግራይ ብሔርተኞች ፋሽስታዊ ፖለቲካ ነው። አካፋውን አካፋ፤ ዶማውን ዶማ ለማለት የማይደፍሩ ተንታኝ ነን ባዮቻችን ግን ሰውን ከርስቱ እያፈለሱ ሰማዩንም ምድሩንም የኦሮሞ ብቻ ለማድረግ ቆራጣ ካርታ ይዘው የሚዞሩን ናዚዎች ፖለቲካ ሕጋዊ ለማድረግ [legtimacy ለመስጠት] ምናባዊ የአማራ ጽንፍ ፈጥረውላቸው false equivalce ሲሰሩ ይውላሉ።

ኢትዮጵያ የጋራ አገራችን ናት፤ ውስጣቸው የሌለችዋን ኢትዮጵያ እንመራለን የሚሉ የመንደር ብሔርተኞች ለኢትዮጵያ መንበረ መንግሥት አይመጥኑም፤ ዜጎች በአገራቸው እየኖሩ አገርህ ሂድ ተብለው መፈናቀላቸው ይቁም፤ አፓርታይድን ተቋማዊ ያደረጉት የጎሳ ክልሎች ይፍረሱ፣ ሕገ መንግሥት ተብዮው የቅሚያና የዘረፋ ደንብ ይሻር፣ ወዘተ የሚሉት ሰብዓዊና ፍትሐዊ ጥያቄዎች እንደ ግፍ ካልተቆጠሩ በስተቀር የአማራ ልሒቃን የሚያራምዱት አካታች ፖለቲካ የአግላዩ የኦሮሞ ብሔርተኞች ሌላ ጽንፍ ሊሆን አይችልም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሸኖ፣ አሌልቱ፣ ቤኪ፣ ሰንዳፋና ለገጣፎ - ከመርሐጽድቅ መኮንን አባይነህ

ስለሆነም ከፍርደ ገምድሉ የኢትዮጵያ ተንታኞች እይታ በስተቀር ኢትዮጵያ ምድር ላይ የአማራና የኦሮሞ የሚባል ፖለቲካ የለም! ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ፖለቲካ ምድሩንም ሰማዩንም ኬኛ የሚሉ ጽንፈኛ የኦሮሞ ብሔርተኞች የሚያራምዱት ናዚያዊ ፖለቲካና አማራውና ሌላው ኢትዮጵያዊ የተካተተበት ሁሉንም የኢትዮጵያ የማኅበረሰብ ክፍል የመላው ኢትዮጵያ ባለበት ለማድረግ የሚካሄድ ትግል ብቻ ነው። የኦሮሞ ብሔርተኞችን የወንጀል ፖለቲካ ቅቡል ለማድረግ በምናብ የተፈጠረው አይነት ሌላ ጽንፍ ላይ የቆመው አግላይ የአማራ ፖለቲካ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያ ውውጥ የለም። የአማራ ልሂቃን የሚታገሉ ኢትዮጵያ የሁሉም የፍትሕ አገር እንድትሆን እንጂ እንደ ኦሮሞ ብሔርተኞች አንዱ ብቻ ተለይቶ ባለቤት የሚሆንባት የግፍ ምድር እንድትሆን አይደለም።

«ኢትዮጵያ የጋራችን» የሚሉትን የአማራ ልሒቃንና ምድሩንም ሰማዩንም «ኬኛ» የሚሉት የኦሮሞ ብሔርተኞች ሁሉት ተቃራኒ ጫፎች አድርገው የሚያስቀምጡ ተንታኞች ግን እነሱ ኢትዮጵያውያን ማዕከል ያደረገ ብለው የሚያስቡት ፖለቲካ ምን አይነት ይሆን? ኢትዮጵያን የጋራ አገራችን ናት ብሎ ማሰብስ እንዴት ሆኖ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ማተባቸውን ከበጠሱ የኦሮሞ ብሔርተኞች እኩል ጽንፈኛት ይሆናል? ለጋራ አብሮነት የሚተጉት የአማራ ልሒቃን ለልዩነት የማይወዳጁት የኢትዮጵያ ጠላት ከሌላቸው የኦሮሞ ብሔርተኞች እኩል እኩል ስጋቶች ሊሆኑ ይችላሉ? ኢትዮጵያዊ ሆኖ ለመኖር የቆረጠስ አካታቹ የአማራ ልሒቃን ፖለቲካ ከአግላዩ የኦሮሞ ፖለቲከኞች እኩል እንዴት ስጋት ሊሆንበት ይችላል?

እንደ እውነቱ ከሆነ ምድሩንም ሰማዩንም «የኦሮሞ ብቻ ነው» የሚለውን ናዚያዊ እሳቤ ማዕከል ያደረገውን የኦሮሞ ብሕርተኞች ፖለቲካ «ኢትዮጵያ የጋራ አገራችን ናት» የሚለውን የአማራ ሊሒቃን አካታች ፖለቲካ ሌላ ጽንፍ አድርጎ ለማቅረብ መሞከር ለእኩልነትና ለጋራ አብሮነት እየታገሉ ያሉትን ሁሉ በማሸማቀቅ ሰማዩንም ምድሩንም ኬኛ የሚሉ ወሮበሎችን ከማፈርጠሙና አቻ አግኝተናል ብለው ናዚያዊ ፖለቲካቸውን የበለጠ እንዲገፉበት ከማድረግ የዘለለ ፋይዳ የለውም!

https://youtu.be/1Skp2UtnFjs

2 Comments

  1. Your writing reflects what is going  on  in your mind. You are desperately searching for compensation for your political bankruptcy. Rational thinking and democratic handling spring from a culture in which one grew up and stamped. But you have no such precious values. You are from a society which has no moral values. You are just from a very selfish society which behaves like a parasite.  Therefore, with your writing you have reflected exactly your culture and mind setups.

    The Oromo have been hosting and treating all ethinc groups from different  parts of Ethiopia all over Oromia equally with love and respect. The other Ethiopians are very thankful for the heartfelt hospitality and empathy of the  Oromo people But you have no the terminologies of thankfulness, appreciation, gratefulness, recognition and valuations in your culture and vocabulary. You are possessed by the spirit of greediness and egocentricity like tapeworms. In simple language you behave like wild animals. The racists are aways like snows. They can be dissolved with a minimum heat. That is why the ideologies of the Apartheid, Nazi and segregation were eradicated. Likewise the ideologies of the ultra nationalists in Ethiopia will be eroded soon. Watch out!

    There is nobody without national background and heritages in this planet. All human beings have ethnic backgrounds regardless of the composition of their ethnicity. Those who try to nullify their ethnic backgrounds are claiming Amhara ethnicity by default under the mask of Ethiopianism. They speak amharic and claim the cultures from north as their culture. They try to impose their default identity (Amaharaism as Ethiopianism) on the others. But it is not more acceptable! Therefore, the current Ethiopian nationalism is equivalent to the Amahara nationalism. Which will be voided soon. It will be replaced by the multinationalism of all Ethiopians. You should have to swallow this truth.

    Finally, there is no wonder that the Parasites cannot understand mutual understanding and benefits. They are very selfish and self-centered. They want to have everything alone. Their objectives are always dehydrating their hosts step by step and finally killing it if they can. That is what we have been witnessing in Ethiopia in the last 140 years. Human parasites.

    Narrow nationalists and racists are those who are against the democratic rights of the differet nations in Ethiopia. They have been using always derogatory terminologies in order to undermine the demands of the Oromo, the Sidama and all other nations. Such efforts are futile and a sign of desperation and hopelessness. No more business as a usual. You should have to swallow these naked realities.

    Here are the slogans of your neo-nazist organization NAMA, just to mention a few:

    – The Amahara  people will be back to its superiority!
    – Most part of Oromia belongs to  the Amahara people 
    – Amahara people must be worshiped as a creator of Ethiopia.
    – The Shewa Oromoo are not Oromo, they are Oromizied Amhara.
    – The Amahara are the best nation in the world.
    – All peoples in Amhara region (Oromo, Agawo, Kimanti, Wayito and Argoba) are Amahara weather they like it or not.
    – Amaharanism is like sprite.  Ever kids in Ethiopia goes to school, in order to behave like Amhara or to become Amhara.

    With such illusions they try to mislead the Amahara people. Their contempt for the other peoples of Ethiopia is enormous.

    • ante gemeda yemitbal denkoro egzer yikir yibelih. ande andu bota yesetehewun asteyayet bekopipest lehulum eyeletefik yihn chika rasihin adebabay lay tasetawaleh. anten yefeterech enat batfeter yishalat nebber. anten mesel Melesoch kaltefachihu Ethiopia selamuan atagegnim. nigigirh hulu endet ar ar endemil lemeredat bemejemeria sost sebat tebel tetemekina yaubih bemiliyon yemikoteru aganint siwotulih yane eyaferek besrahna benigigirih tibesachaleh. besmam, seytan’n beakal lemayet anetne magegnet new. worada.

Comments are closed.

Share