እሽሩሩ ኦነግ – ከአንተነህ መርዕድ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ለኦሮሞ ህዝብ መብት የተነሳሁ ነኝ ቢልም ባለፉ አርባ ዓመታት ለምን እንደቆመ ተግባሩ እያሳየን ነው። በተለይም በዚህ የለውጥ ጊዜ ኢትዮጵያን ወደየት ይዟት ሊሄድ እንደፈለገ በተግባር ያሳየን ስለሆነ ዛሬ ሁሉም በሚገባ ያውቀዋል። ሁሉን አካታች የሆነው የኦሮሞ ህዝብ በስሙ በሚካሄድ ወንጀል የአገሩ ህልውና አደጋ ላይ እየወደቀ ከሌላው ወገኑ ጋርም በፍቅር የሚኖርበትን ሁኔታ እየተበላሸ ነው።

ከሁሉም በላይ ስልጣን ላይ ያለው የለውጥ ሃይል ኦነግን እሽሩሩ የሚልበት ሁኔታ አሳሳቢ ነው። አምስት መቶ የማይሞላ ታጣቂ አለኝ ባለ በወሩ በአስር ሺዎች ታጣቂ አለኝ ሲልና ትጥቅ አልፈታም ብሎ ለያዥ ለገራዥ ሲያስቸግር ዝም ተባለ። ኦነግ ሲያልማት የኖራትን የተገነጠለች ኦሮምያ ሪፐብሊክ ለመመስረት ሁሉንም ለመዋጥ ሲያዛጋ እያየን ነው። አሁን ግን ከማዛጋት አልፎ እየነከሰም እያደማም ነው። ሶማልያ ለተፈፀመው እልቂትና ስደት ከአብዲ ኢሌ የበለጠ እንጂ ያነሰ ሚና አልነበረውም። ሃረርንና ድሬደዋን ለመሰልቀጥ በከባባ ነዋሪዎቹ ስቃይ ላይ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠር የጌድዮ ህዝብ ላይ የተፈፅመው ዘኛኝ ግፍ አይደለም በድርጊቱ የተሳተፉትን ስልጣን ላይ ሆነው በቸልታ የተመለከቱትን ነገ ማስጠየቁ የማይቀር ነው። ኦነግ በደቡብ ለሚገኙ ሌሎችም ማህበረሰቦች የስጋት ምንጭ ነው። ቡራዩ የተካሄደው ዘኛኝ ጭፍጨፋ በግልፅ ለመናገር የዘርማጥፋት ወንጀል በሚገባ በመረጃ ተደግፎ የተቀመጠ ወንጀል ስለሆነ ነገ የሚወጣ እውነት ነው። አዲስ አበባን በመዳፉ ለማድረግና ነዋሪዋን ቅኝ ለመግዛት የተሄደበት ግልፅና ስውር ደባ የሚሳካ ባይሆንም ብዙ የሚያስከፍለን አደጋ ነው። ሞያሌ እንዲሁም ምዕራብ ወለጋ በዜጎች ላይ የተደረገው ግድያ፣ ዘረፋና የንብረት ማውደም ለሌላው ብቻ ሳይሆን ቆሜለታለሁ ለሚለው ለኦሮሞው ህዝብም የማይመለስ አረመኔ ድርጂት መሆኑን በአደባባይ አስመስክሯል። አስራ ስምንት የህዝብ ባንክ ሲዘርፍ፣ የህዝብ መጠቀምያ የሆኑ ትምህርት ቤቶች፣ ክሊኒኮችና መስሪያ ቤቶች ሲያወድም፤ የአካባቢ ተወላጁን ኢንቨስተር ከውጭ ባለሙያዎቹ ጋር ገድሎ ሲያቃጥል ኦነግ ለኦሮሞ ህዝብ ቆሟል የሚል ካለ ጤነኛ አይደለም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  "… አላውቅም ! የወንድሜ ጠባቂው እኔ ነኝን … ? " ባዮቹ ፤ ቃየንአዊያን እና ባቢሎናዊያን አኛ  አይደለንምን? - መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

የቤንሻንጉል ባለስልጣናትን በመግደል በኦሮሞዎች ጉረሮ ላይ ቆሞ በመቶ ሺዎች እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሲሆን አሁን  ደግሞ ወደ አማራው ሰሜን ሸዋና ወሎ ዘልቆ ከመንግስት የውስጥ ደጋፊዎቹ ባስታጠቁት ከባድ መሳርያ ንፁህ ኢትዮጵያውያንን ሲገድል ኦሮሞው ከሌላው ወገኑ ጋር በሰላም እንዳይኖር እያዘጋጀው ያለው አደጋ የማይታየው ካለ የሞተ ብቻ ነው።

ባለፉት ሶስት የትንቅንቅ ዓመታት በወያኔ ስናይፐር ሺ ወጣቶች በአደባባይ ሲረፈረፉ አንዲት ጥይት መተኮስ ሳይችል በኢሳያስ ጉያ የነበረ ልፍስፍስ ድርጂት ዛሬ ሺ ንፁሃንን የሚገድልበት ጉልበትና ችሎታ የት አገኘ? መልሱ ቀላል ነው። ኦህዴድ ውስጥ ተጠልለው የኖሩ ዘራፊና ፈሪ ዘረኞች መሳርያውን፣ ገንዘቡን፣ መንግስታዊ ተቋሙንም ከፍተው አቅም ሰጥተውታል። ዴሞክራሲያዊ ለውጥ እነሱንም እንዳይጠራርግ ህወሃት ትቶት የሄደውን ስልጣንና የሃብት ምንጭ ተቆጣጥረው ተረኛ አምባገነን መሆን ያለሙ ለናቸው በእያንዳንዷ ክፍት ቦታ ራሳቸውን ሲሞሉ እያየን ነው።

ትናንት የአገር ጠላት ህወሃት መራሹ ጨካኝና ዘራፊ ቡድን ነበረ። በህዝብ ትግል ተወግዷል። ዛሬ ደግሞ ጎልቶ ያልወጣ ቢመስልም በኦነግ ዓላማ ዙርያ ኢትዮጵያን ቀፍዶ የሚይዝ ሌላ ዘረኛና ዘራፊ አምባገነን ስርዓት ለመትከል ቅርፅ እየያዘ የመጣ ሃይል በተረኛነት በኢትዮጵያ አድማስ ላይ ይታያል። ከዓመት በፊት የተለኮሰውን ተስፋ ሊያደበዝዝ ጥላውን ዕያጠላ ያለው አስፈሪ ዘረኝነት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመርና የፍቅር እንዲሁም የለማ መገርሳ ኢትዮጵያ ሱሴ አማላይ ሰበካ የሚወገድ አይደለም። ያዘናጋን እንደሆነ እንጂ።

መፍትሄው በህዝቡ እጅ ነው። መንግስት የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ እተሳነውና የተደራጀ ዘረኛ ቡድን ተስፋፊ ፍላጎቱን በመላ ኢትዮጵያውያን ላይ ለመጫን እድል እየሰጠው ስለሆነ ራሱን መጠበቅና ለውጡን ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ ማስኬድ የህዝቡ ሃላፊነት ነው። ስለሆነም

  • ህዝቡ መንግስት የአገሪቱን ፀጥታ እንዲያስከብር ጠንክሮ መጠየቅ፣ መታገልና ማስገደድ፤
  • ህዝቡ በየአካባቢው በመደራጀት የአካባቢውን ፀጥታ መጠበቅና ግጭቶች እንዳይነሱ መከላከል፣ ከአጎራባች ህዝብ ጋር መልካም ግንኙነት መቀጠል፣ ለጋራ ደህንነት መተባበር፤
  • በፖለቲካ አስተሳሰብ፣ በሃይማኖት፣ በባህልና በዘር ልዩነት የሚራገቡ ቅስቀሳዎችን ማስወገድ፤ ይህንን ልዩነት የሚሰብኩትን እንዲያቆሙ ማስገደድ፤
  • በተፈጠረው ቀውስ የተፈናቀሉትን ማቋቋም፣ ራሳቸውን እንዲችሉ ማድረግ፤
  • የአገሪቱ ኤኮኖሚ አደጋ ላይ ስለሆነ ምርት እንዲጠናከር፣ ገበያ እንዲስፋፋ፣ የህዝብ ግንኙነት እንዲሳለጥ ማድረግ። የምርት ቋማት ላይ የሚደረግን ጥቃት መከላከል፤
  • በባህላችንም፣ በእምነታችንም ያልነበረውን እየተለመደ የመጣውን ጭካኔ ማውገዝና መከላከል ያስፈልጋል
ተጨማሪ ያንብቡ:  አንድነት፤ አንድነት ስንል አምሳ ዓመት ሊሆን ነው---ለመተባበር ዘውጋዊ ፖለቲካን የማስወገድ ቆራጠኛነት ያስፈልጋል - አክሎግ ቢራራ (ዶር)

መንግስት ኦነግን እሽሩሩ የሚልበት እንቀልባ እስኪበጠስ በትዕግስት ስንጠብቅ አገራችንን እናጣታለን። ዛሬ መንግስት የምንለው ሃይል የጠራ አቋም ወይንም አቅም ያለው አይመስልም። አቋሙ ሆነ አቅሙ የህዝቡን ፍላጎት ማካተት የሚችለው ህዝባዊ ትግሉ ሲቀጥል ነው። አሁን “ፖለቲከኛ” ነኝ የሚለው አማተርም ሆነ ህዝቡ የለውጥ ሃይል ከሚባለው አካል ብዙ ይጠብቃል። ጨርሶ ስህተት ነው። እነዚህ ሰዎች በህዝብ ትግል ተገድደው አገልጋይነቱም ሰልችቷቸው ትግሉን ተቀላቀሉ እንጂ በተፈጥሮአቸው የለውጥ ሃይል አይደሉም። በህዝብ ሙቀትና ጭብጨባ የጀመሩት እስክስታ ከውስጣቸው የመነጨ አለመሆኑን ተግባራቸው እያሳየን ነው። ዋናውን ስራቸውን ትተው አሁንም ድቢ እየመታን እንድናጂባቸው እንጂ ስህተታቸውን እንድንነግራቸው ፍላጎት እያሳዩ አይደለም። ቀዝቀዝ ስናደርግ ሲቆጡና ሲደናገራቸው፣ እልፎ እልፎም የከፈሉትን መስዋዕትነት ሊሰብኩን ይዳዳቸዋል። ልጆቻቸው በስናይፐር ከተገደሉባቸው ወላጆች ወይንም ጥፍራቸው በፒንሳ፣ ብልታቸው በሃይላንደር ከተጎተቱት በላይ መስዋዕት ከፍለናል ሊሉን ምንም አልቀራቸውም። ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን እንደሚባለው የትናንቱን ረስተን ወደ ወደፊት እንሂድ ያለን ህዝብ የዛሬ ጥፋታቸውን እንዲያርሙ ሊነገራቸው ሲሞከር ትናንት የሰሩትን “ገድል” ሊሰብኩን ይዳዳቸዋል። ህወሃትም የአስራ ሰባት ዓመት ገድልና የስልሳ ሺህ መስዋዕት ለሃያ ሰባት ዓመት ሰብኮ አልጨረሰውም። አላሳመነንም። ከህዝብ የተደበቀ መስዋዕት ሆነ ወንጀል የለም። አንበሳ ጦጣን “ነይ ውረጅ አልበላሽም” ሲላት “አልበላሽምን ምን አመጣው?” ብላለች። “ትናንት ይህን አድርገናል” የሚል የውለታ ጥያቄ የዛሬን ስህተት አይሸፍንም።

አብይ ሆይ ያለምንም ዋስትና ከሰንሰለት የለቀቅከው ኦነግ ዛሬ ህዝብና አገር እያደማ ነው። አንተንና ጓዶችህን ለመብላት እንደማይመለስ ልቦናህ ያውቀዋል። የጊዜ ጉዳይ ነው። ትናንት በአንቀልባ እሹሩሩ የተባለው ኦነግ ዛሬ በመግዘፉ አንቀልባውን በጥሶ አዛዩን ሊያጠቃ ምንም አልቀረውም። አዝሎት ያመጣውን ያጠፋ እነደሆነ እንጂ ኢትዮጵያና ህዝቧ ራሳቸውን ለመጠበቅ ይገደዳሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:   የባለአደራ ግዚያዊ የአገር ጉባኤ ይቋቋም!

4 Comments

  1. Before accusing ODP and OLF why you don’t want to advise your new born ultranationalists like the members of  the National Movement of the Amahara (NAMA). This group and its associates have been driving the Amahara people in a ditch. It is a time to fight these uncivilized and racist gangs before it is too late for the Amahara people. Their acts and slogans will dissolve the bondage between the Amahara and the rest of Ethiopians.

    For all the recent chaos in Wollo and North  Shewa are only the racist  neo- nazist organization the Amahara the National  Movement of the Amahara (NAMA) and its associates responsible. The stubbornness and arrogance of these bunch of individuals will be punished soon all over Ethiopia.

    Here are the slogans of the neo-nazist organization NAMA, just to mention a few:

    – The Amahara  people will be back to its superiority!
    – Most part of Oromia belongs to  the Amahara people 
    – Amahara people must be worshiped as a creator of Ethiopia.
    – The Shewa Oromoo are not Oromo, they are Oromizied Amhara.
    – The Amahara are the best nation in the world.
    – All peoples in Amhara region (Oromo, Agawo, Kimanti, Wayito and Argoba) are Amahara weather they like it or not.
    – Amaharanism is like sprite.  Ever kids in Ethiopia goes to school, in order to behave like Amhara or to become Amhara.

    With such illusions they try to mislead the Amahara people. Their contempt for the other peoples of Ethiopia is enormous.

     

    • Gammada wake up!!!Are u still in false narration? If we have to live together you have to aknweledge all thé facts. NAMA’s agendas are thé claims of all Amhara people b/c they are facts

  2. The OLF thugs need to be put on a short leash, the same way they were being handled in the past under the yoke of tyranny and an iron fisted grips of the Woyane regime. The OLF seemed not to appreciate the freedom they were handed on a silver platter since their masters fled and hid in Mekele. It had become for them very difficult to get rid of their old habits they were accustomed to under the Woyane regime. They like to be treated like wild animals, where they will be hand cuffed, legs shackled, and got beat up with electric wire, and then thrown into a pitch dark, filthy, bone- chilled cold under ground prison cell.
    If the OLF wants to be member of the Ethiopian community it has to give up its narrow minded secessionist ideas and join the rest of peace loving Ethiopians and live in harmony and prosperity. Any thing less than that is not acceptable.
    Prime minister Dr. Abiy Ahmed ought to give a stern warning to the warmongers such as the likes of Jawar to refrain from spewing out his venom speeches to incite violence. If he refuses to talk with civility he ought to be canned like it happened to a US citizen by the name Michel P. Fay in Singapore in 1994, for spray painting cars as a sign of protest. Any one who carries a foreign passport should obey and live by the rules and regulations of the country’s they are visiting. Carrying a US passport doesn’t give the scum of the earth Jawar a carte blanche to incite violence and then run back to Minnesota when the violence breaks out to save his own life, with his tail tucked between his hind legs. In order to bring OLF crisis under control Prime Minister Dr Abiy must keep these thugs on a short leash. He has to use his long arm reach to wipe them out of their hideouts and teach them a lesson they will never forget again

  3. “The OLF seemed not to appreciate the freedom they were handed on a silver platter …” Ashagre Abebe. WOW!
    Let’s forget what transpired in the last 40 years. Where were you the last 3-4 years? The Qeerro movement, the brainchild of OLF, has cost the Oromo more than 5000 lives. It provided you and all the ungrateful Habeshas the freedom of expression & organisation on silver plate. That is the fact. At least acknowledge it and use this liberty come free wisely. Defamation of your liberators is not only arrogance but also stupidity!

Comments are closed.

Share